• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከመንግሥት ግዢ ጋር በተያያዘ የሚፈጸመው ሌብነት ሊታነቅ ነው

October 24, 2022 02:26 am by Editor Leave a Comment

ሁሉም የፌዴራል ተቋማት የኤሌክትሮኒክስ የመንግሥት ግዥ ሥርዓትን ሊጠቀሙ ነው

በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ሁሉም የፌዴራል ተቋማት የኤሌክትሮኒክስ የመንግሥት ግዥ ሥርዓትን ይጠቀማሉ ሲል የመንግሥት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን አስታወቀ፡፡

የባለሥልጣኑ የኤሌክትሮኒክስ የመንግሥት ግዥ ሲስተም ፕሮጀክት ማናጀር አቶ ታደሰ ከበደ በተለይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ እስካሁን ባለው ጊዜ ውስጥ በሲስተሙ ከ25 በላይ የሚሆኑ ጫረታዎች ወጥተዋል፡፡ በቀጣይ ሁለት ዓመታት የፌዴራል መስሪያ ቤቶች ላይ ትኩረት ተደርጎ ይሰራል፡፡

በቀጣይ ሥርዓቱን ወደ ክልሎች በማውረድ ይሰራል ያሉት አቶ ታደሰ፤ በ2015ና 2016 በጀት ዓመት መጨረሻ ድረስ ሁሉም የፌዴራል ተቋማት ጨረታዎችን የሚያወጡትና ግዥዎችን የሚያከናውኑት ሲስተሙን በመጠቀም ይሆናል ብለዋል፡፡ በዚህም እንደ አገር ያለውን የተበላሸ የግዥ ሥርዓት ማስተካከል እና የአገርንም ሀብት ከስርቆትና ከብክነት ማዳን ይቻላል ብለዋል፡፡

እንደ ማናጀሩ ገለጻ፤ በ2014 በጀት ዓመት ብቻ የኤሌክትሮኒክስ የመንግሥት ግዥ ሲስተምን በመጠቀም 66 መስሪያ ቤቶች ዓመታዊ የግዥ እቅዳቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡ እንዲሁም በ2014 በጀት ዓመት ሰባት መስሪያ ቤቶች ሃያ ሁለት ጨረታዎችን በኦንላይን ሲስተም አውጥተው ለተጫራቾችይፋ አድርገዋል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ የመንግስት ግዥን በኤሌክትሮኒክስ መፈጸም የንግዱን ማህበረሰብ የሚጠቅምና ጤናማ ውድድር እንዲኖር በማድረግ ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን እንደሚያስድግ የመንግሥት ግዥና ንብረት ባለስልጣን አሰታወቀ።

የኤሌክትሮኒክስ የግዥ ሥርዓትን ተግባራዊ ለማድረግ በነገው ዕለት ከአቅራቢዎች ጋር የምክክር መድረክ ይካሄዳል፡፡

የምክክር መድረኩን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት የመንግሥት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሃጂ ኢብሳ እንደገለጹት፣ በነገው እለት ከግሉ ዘርፍ አቅራቢያዎች ጋር ውይይት ይካሄዳል። በምክክር መድረኩ ከአንድ ሺህ በላይ አቅራቢያዎች ይሳተፋሉ ብለዋል።

የንግዱን ማህበረሰብ የሚጠቅምና ጤናማ ውድድር እንዲኖር በማድረግ ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ያረጋግጣል።

የኤሌክትሮኒክስ የመንግስት ግዥን ያደጉ አገሮች መጠቀም ከጀመሩበት ጊዜ ጀምሮ ውጤት ሆነዋል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ በአሁኑ ጊዜ 72 የፌደራል ተቋማት የኤሌክትሮኒክስ የግዥ ስርአቱን መጠቀም ጀምረዋል።

የኤሌክትሮኒክስ የግዥ ሥርዓት ሙሉ ለሙሉ ስራ ላይ ሲውል ብልሹ አሰራርን በመቀነስ ለአገር እድገት ከፍተኛ ጥቅም ይኖረዋልም ብለዋል።

ነገ ከሚካሄደው የውይይት መድረክ በኋላ የንግዱ ማህበረሰብ የሚያወጡትን ግዥዎችን በግልጽ ያወጣሉ፣ ተጫራቾችም በግልጽ ይጫረታሉ፤ 24 ሰአት ሙሉ መጫረት ይችላሉ፣ ሁሉም ተጫራች ባለበት ቦታ መጫረት ስለሚችል ከፍተኛ የወጭ ቅነሳ ይኖረዋል።

እስከቀጣይ አምስት አመት ድረስ በሁሉም ክልሎች ያሉ ተቋማት፣ እስከወረዳ ድረስ ወደ ሲስተሙ ይገባሉ ብለዋል። (EPA)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: corruption, EPPA, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule