በመግለጫው ትህነግ የሚያዋጣው የብልጽግና መንገድ ነው አለ ለትግራይ ህጻናት ዕልቂት ተጠያቂው ማን ነው? ብልጽግናን እንደማይቀላቀል አስታውቆ ወደ ትግራይ ያፈገፈገው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር (ትህነግ) “በአዲሱ ዓመት ግጭቱን አቁመን ለሰላም ዕድል በመስጠት የሰላም እና ብልጽግና መንገድ እንጀምር” ሲል በይፋ የተናጠል ተኩስ አቁም ማወጁን አስታወቀ። መግለጫውን ተከትሎ “ላለቁት የትግራይ ህጻናት ተጠያቂ ማን ሊሆን ነው? ለዚህ ለዚህ ለምን ውጊያ ውስጥ ገባን?” በሚል ደጋፊዎቹ ንዴት አዘል ጥያቄ እያነሱ ነው። ጦርነቱ ከመጀመሩ በፊት “አፍንጫቸውን ይዘን ቅድመ ሁኔታችንን ተቀብለው ወደ ድርድር እናመጣቸዋለን። ካልሆነም እንወጋቸዋለን” በማለት የወንበዴው ቡድን መሪ ደብረጽዮን መግለጫ ሰጥቶ ነበር። መንግሥት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በየትኛውም ቦታ ለመደራደር ፈቃደኛ … [Read more...] about ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ እደራደራለሁ ያለው ትህነግ ውጊያ ከፍቷል
News
ዜና
የአዲስ አበባዎቹ አሸባሪ የትህነግ ወንበዴዎች (“ሰላማዊ ነዋሪዎች”) በቁጥጥር ሥር ዋሉ
ባለፈው ሳምንት ባወጣነው ዘገባ ከአዲስ አበባ ሆነው የትህነግን ሥራ የሚያስፈጽሙ ወንበዴዎች መኖራቸውንና መንግሥት በጉዳዩ ምላሽ እንዲሰጥ ጠቁመን ነበር። በወጣው ዘገባ መሠረት ከአዲስ አበባ ሆነው የት ህነግን ሥራ የሚያስፈጽሙ በተለይም በትዊተር በተለቀቀው መልዕክት 88% የተላከው ከአዲስ አበባ መሆኑን በማስረጃ የተደገፈ መረጃ ነበር የቀረበው። የአዲስ አበባ “ሰላማዊ” ነዋሪዎች – አፍቃሪ ትህነጎች ማንነት በማስረጃ የኢትዮጵያ የጋራ የጸጥታ ግብረኃይል ሲከታተላቸው የነበሩና እጅግ ውስብስብ በሆነና ሕዝብን በሚያሸብር ተግባር ላይ ተሰማርተው የነበሩ 19 የሽብር ቡድን አባላትና የትህነግ አስፈጽሚ ወንበዴዎች በቁጥጥር ሥር ውለዋል። ከፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ያወጣው መግለጫ እንዲህ ይነበባል፤ ጠላቶቻችን አዲስ አበባን የሽብር ማዕከል እናደርጋለን ብለው … [Read more...] about የአዲስ አበባዎቹ አሸባሪ የትህነግ ወንበዴዎች (“ሰላማዊ ነዋሪዎች”) በቁጥጥር ሥር ዋሉ
ኢትዮጵያን “በእኛ ትውልድ ማንም ተነስቶ እንዲፈነጭባት አልፈልግም” ምክትል ፲ አለቃ በዝናሽ ወዳጆ
ኢትዮጵያ ታፍራ እና ተከብራ እንድትኖር የተሠጠኝን ግዳጅ በጀግንነት እወጣለሁ ትላለች ምክትል ፲ አለቃ በዝናሽ ወዳጆ። በሰቆጣ ግንባር የአሸባሪውን የህወሓት ታጣቂ ዶግ አመድ ካደረጉት ጀግኖች መካከል አንዷ ናት ምክትል አስር አለቃ በዝናሽ ወዳጆ። ምክትል አስር አለቃ በዝናሽ ወዳጆ እንደተናገረችው ኢትዮጵያን ተላላኪ የሽብር ቡድን ሰላሟን እንዳያደፈረስ ላፍታም ቢሆን ሳልዘናጋ የተሠጠኝን ግዳጅ በጀግንነት እወጣለሁ። አባቶች በመስዋትነታቸው ያስረከቡንን ሀገር በእኛ ትውልድ ማንም ተነስቶ እንዲፈነጭባት አልፈልግም። በተሰለፍኩበት ግንባር የሀገሬን ጠላት እስከ መስዋዕትነት ከፍዬ ግዳጄን በቁርጠኝነት እወጣለሁ ብላለች። (መከላከያ ሠራዊት) ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about ኢትዮጵያን “በእኛ ትውልድ ማንም ተነስቶ እንዲፈነጭባት አልፈልግም” ምክትል ፲ አለቃ በዝናሽ ወዳጆ
ደስታ ጌታሁን – የደጀንነት ጀብዱ
ወይዘሮ ደስታ ጌታሁን ነው የምትባለው፡፡ ይህች እህታችን በሰቆጣ ከተማ በትንሽዬ የዳስ ውስጥ ቡና እና ሻይ በመስራት ሁለት ልጆችዋን ታስተዳድራለች፡፡ ወይዘሮ ደስታ ለእናት ሃገሩ ኢትዮጵያ ለሚፋለመው ጀግናው የመከላከያ ሰራዊታችን የምታደርገው ነገር ግራ ቢገባትም ከልጆችዋ እና ከራስዋ የእለት ጉርስ ቀንሳ በግዳጅ ቀጠናው ለሚፋለሙ የሰራዊት አባላት ቡና እና ሻይ ይዛ ተገኝታለች፡፡ ወይዘሮ ደስታ ጌታሁን ሰራዊቱ በግዳጅ ላይ ፋታ ሲያገኝ ቡና እና ሻይ በማቅረብ ደጀንነቷን በጀግንነት አስመስክራለች፡፡ (ዘግባና ፎቶግራፍ፤ ልመነህ ሻወል የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት) ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about ደስታ ጌታሁን – የደጀንነት ጀብዱ
“ውረሩ፣ ያገኛችሁትን ግደሉ እየተባልን ነው የምንመጣው” እጃቸውን የሠጡ የትህነግ ታጣቂዎች
በኢትዮጵያ እና በኢትዮጵያውያን ላይ የተነሳው የሽብር ቡድን በሕዝብ ላይ አያሌ በደሎችን አድርሷል። ከእኩይ ቡድን አቅራቢያ የሚገኙ የአማራና የአፋር ክልል ነዋሪዎች ደግሞ የሽብር ቡድኑ ግፍና ወረራ ገፈት ቀማሾች ናቸው። ለሦስተኛ ጊዜ ጦርነት ያነሳው የትህነግ የሽብር ቡድን የትግራይ ተወላጆችን ከሕፃናት እስከ አዛውንት ድረስ እየመለመለ ለጦርነት እየላካቸው ነው። የሽብር ቡድኑ በአማራና አፋር ክልል በወረራ በያዛቸው አካባቢዎች ንፁሐንን በጅምላ ረሽኗል፣ ሃብትና ንብፈታቸውን ዘረፏል አውድሟል። የሽብር ቡድኑ የሚልካቸው ታጣቂዎች ሀገሩን እየተከላከለ በሚገኘው ጥምር ጦር እየተመቱ ብዙዎች ይረግፋሉ። እድል የቀናቸው እጃቸውን ሰጥተው ሕይወታቸውን ያተርፋሉ። የሽብር ቡድኑ ታጣቂዎች በወልቃት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ዞን ለሚገኘው ጀግናው የሀገር መከላከያ በርካቶች እጃቸውን እየሰጡ … [Read more...] about “ውረሩ፣ ያገኛችሁትን ግደሉ እየተባልን ነው የምንመጣው” እጃቸውን የሠጡ የትህነግ ታጣቂዎች
“ህወሃት የበሰበሰች ናት፤ አትጠቅምም” የህወሃት ምርኮኛ
አሸባሪው ህወሓት የቀረበለትን የሰላም አማራጭ ረግጦ ዳግም ጦርነት መክፈቱ በትግራይ ህዝብ ጫንቃ ላይ ቆሞ የስልጣን እድሜውን ለማራዘም ነው ሲሉ በተለያዩ ግንባሮች እጃቸውን ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊት የሰጡ ምርኮኞች አጋለጡ። ምርኮኞቹ እንደተናገሩትም የትግራይን ህጻናት ሳይቀር ወደ ጦር ግንባር እየማገደ የሚገኘው አሸባሪው ህወሃት በሃሰተኛ ትርክት የትግራይን ወጣት ራሱ ወደለኮሰው ጦርነት እየማገደ ክልሉን ትውልድ አልባ የማድረግ እኩይ አላማውን ገፍቶበታል። ይህም ተግባሩ የሽብር ቡድኑን የባንዳነት ትክክለኛ ባህሪ በተጨባጭ እያረጋገጠ መሆኑንም ነው ምርኮኞቹ የተናገሩት። https://www.youtube.com/watch?v=z_adOLMwufQ ምርኮኞቹ አሸባሪው የህወሃት ቡድን በትግራይ ህዝብና ህፃናት ላይ እየፈፀመ ያለውን ስቃይና እንግልት በመቃወም … [Read more...] about “ህወሃት የበሰበሰች ናት፤ አትጠቅምም” የህወሃት ምርኮኛ
መፍትሔ የራቀው የአሸባሪው ሕወሓት የዘረፋ ሱስ
ባሳለፍነው ሳምንት አሸባሪው የሕወሓት ቡድን ሰብዓዊ ርዳታዎችን ለሚያመላልሱ ተሽከርካሪዎች አገልግሎት የሚውልና በዓለም ምግብ ፕሮግራም መቀሌ መጋዘን የተከማቸ ነዳጅ መዝረፉ ይፋ መሆኑ አይዘነጋም። በወጣው መረጃም ቡድኑ 12 የነዳጅ ቦቴዎችን በአጠቃላይ 570 ሺህ ሊትር ነዳጅ መዝረፉ ነው የተመላከተው። የፖለቲካና ፌዴራሊዝም ምሁሩ ሀይለየሱስ (ዶ/ር) አዲስ ልሳን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ አሸባሪው ሕወሓት ከጅምሩ አንስቶ የተለያዩ የስርቆት ወንጀሎችን ሲፈፅም የኖረ መሆኑን አውስተው፤ በተለይ በከፍተኛ የዕለት ደራሽ ድጋፍ ላይ ሲፈፅም የነበረው ዝርፊያ ህዝቡ በረሀብ እንዲያልቅ ከመፍረድ ለይተው እንደማያዩት ነው የገለፁት። አንድ ፓርቲ፤ አንድ ህዝብ የሚል አስተሳሰብ የቆየና ኮሚኒስታዊ አመለካከት እንደሆነ የሚያስረዱት ምሁሩ አክለው እንዳስገነዘቡት፤ አሸባሪ ቡድኑ አሁን ላይ … [Read more...] about መፍትሔ የራቀው የአሸባሪው ሕወሓት የዘረፋ ሱስ
ለአሸባሪው ህወሓት ሊተላለፍ የነበረ ከ1 ሚሊየን ብር በላይ ተያዘ
ከበየዳ ወደ ስሃላ ወረዳ በቅብብሎሽ ለሽብርተኛው ህወሓት ሊደርስ የነበረ 1 ሚሊየን 253 ሺህ ብር መያዙን በአማራ ክልል ልዩ ኃይል የተከዜ ክፍለ ጦር 3ኛ ሻለቃ አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር ጀጃው ፈረደ ገልጸዋል። አሸባሪው ቡድን ሰርጎ ገቦችን በማዘጋጀት ገንዘብና ቁሳቁስ እንዲሻገርለት ቢፈልግም በአማራ ክልል ልዩ ኃይልና በህብረተሰቡ ጥብቅ ክትትል ዕቅዱ ከሽፏል ብለዋል። ቡድኑ ሊጠቀምበት የነበረ 600 ሊትር አረቂ፣ 10 ጣቃ አቡጀዲ፣ 15 ሺህ 9 የሶላር መብራትና ከአምስት ኩንታል በላይ ጨው እና መሰል ቁሳቁስ ከእነተጠርጣሪዎቹ መያዙን የበየዳ ወረዳ ኮሙኒኬሽን መረጃ አመላክቷል። (Fana) ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about ለአሸባሪው ህወሓት ሊተላለፍ የነበረ ከ1 ሚሊየን ብር በላይ ተያዘ
የትህነግ ፍቅር ያከነፈው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ከኢትዮጵያ ጀርባ ከአሸባሪው ትህነግ ጋር በመደራደር የራሱን ህግ ጥሷል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ከኢትዮጵያ ጀርባ ከአሸባሪው ትህነግ አመራር ጋር በቀጥታ በመደራደር የራሱን ሕግ መጣሱ ታውቋል። የድርጅቱ ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ባለፈው ሳምንት ከአሸባሪው የህወሓት ቡድን ሊቀመንበር ከሆነው ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ጋር ውይይት ማድረጋቸውን አስታውቀዋል። ዋና ጸሀፊው ይህንን ከአሸባሪው ድርጅት መሪ ጋር የመነጋገራቸው መረጃ የታወቀውም፤ የድርጅቱ ቃል አቀባይ ስታፌን ዱጃሪች ለተመድ ጉዳይ ዘጋቢ ጋዜጠኞች ጽፈውት ሾልኮ ከወጣው ኢሜይል ነው። የዋና ጸሀፊው ድርጊትን ተከትሎ በርካቶች ጉዳዩን በማንሳት ተገቢነት የጎደለው መሆኑን እየገለጹ ነው። ትህነግ በዓለም አቀፍ የሽብር መረጃ ቋት (Global Terrorism … [Read more...] about የትህነግ ፍቅር ያከነፈው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት
በምትኩ ካሳና ግብረአበሮቹ ላይ የሌብነት ክስ ተመሠረተ
የብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር የነበሩት አቶ ምትኩ ካሳ እና ቤተሰቦቻቸው እንዲሁም ግብራበሮቹ ላይ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዐቃቤ ህግ በዛሬው እለት ክስ መስርቷል፡፡ ተከሳሾች 1ኛ አቶ ምትኩ ካሳ ጉትሌ (የብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር የነበሩ) ፣2ኛአቶ አራጋው ለማ (የብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የፋይናንስ ዳይሬክተር)፣ 3ኛ አቶ የማነ ወ/ማሪያም (የኤልሻዳይ ሪሊፍ ኤንደ ዴቭሎፕመንት አሶሴሸን ዋና ዳይሬክተር የነበሩ)፣ 4ኛ ዶ/ር ዮናስ ወ/ትንሳይ (የኤልሻዳይ ሪሊፍ ኤንደ ዴቭሎፕመንት አሶሴሸን የኦፕሬሽን ዘርፍ ም/ስራ አስኪያጅ ናቸው፡፡ በተጨማሪም 5ኛ አቶ ደመውዝ ኃይሉ (ኤልሻዳይ ሪሊፍ ኤንደ ዴቭሎፕመንት አሶሴሸን የፋይናንስ ዘርፍ ም/ስራ አስኪያጅ) ፣6ኛ ወ/ሮ ሶፊያ ጀማል ሰላሙ (የ1ኛ ተከሳሽ የትዳር አጋር) … [Read more...] about በምትኩ ካሳና ግብረአበሮቹ ላይ የሌብነት ክስ ተመሠረተ










