• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መፍትሔ የራቀው የአሸባሪው ሕወሓት የዘረፋ ሱስ

August 30, 2022 04:44 pm by Editor Leave a Comment

ባሳለፍነው ሳምንት አሸባሪው የሕወሓት ቡድን ሰብዓዊ ርዳታዎችን ለሚያመላልሱ ተሽከርካሪዎች አገልግሎት የሚውልና በዓለም ምግብ ፕሮግራም መቀሌ መጋዘን የተከማቸ ነዳጅ መዝረፉ ይፋ መሆኑ አይዘነጋም። በወጣው መረጃም ቡድኑ 12 የነዳጅ ቦቴዎችን በአጠቃላይ 570 ሺህ ሊትር ነዳጅ መዝረፉ ነው የተመላከተው።

የፖለቲካና ፌዴራሊዝም ምሁሩ ሀይለየሱስ (ዶ/ር) አዲስ ልሳን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ አሸባሪው ሕወሓት ከጅምሩ አንስቶ የተለያዩ የስርቆት ወንጀሎችን ሲፈፅም የኖረ መሆኑን አውስተው፤ በተለይ በከፍተኛ የዕለት ደራሽ ድጋፍ ላይ ሲፈፅም የነበረው ዝርፊያ ህዝቡ በረሀብ እንዲያልቅ ከመፍረድ ለይተው እንደማያዩት ነው የገለፁት።

አንድ ፓርቲ፤ አንድ ህዝብ የሚል አስተሳሰብ የቆየና ኮሚኒስታዊ አመለካከት እንደሆነ የሚያስረዱት ምሁሩ አክለው እንዳስገነዘቡት፤ አሸባሪ ቡድኑ አሁን ላይ እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ በየትኛውም አግባብ ህዝባዊ ውግንና የሌለውና ስልጣንና ስልጣንን ብቻ ያስቀደመ ነው። ይህንንም “እኛ ስልጣን ካልያዝን ሁሉም ይውደም” የሚል ዓይነት እኩይ ተግባራቸው ማሳያ ነው ይላሉ ምሁሩ።

የሽብር ቡድኑ ከሰሞኑ የፈፀመው የነዳጅ ስርቆት ተግባር አስቀድሞም ሲፈፅመው የነበረ የእኩይ ባህይሪው መገለጫና የነውረኛነቱ ማስታወሻ መሆኑን ያነሱት ሀይለየሱስ (ዶ/ር) የውጭ መንግስታት ተግባሩን ለማውገዝ የሄዱበት ርቀት ግን ለትችት የሚዳርግ ነው ይላሉ። በእርግጥ ዘግይተውም ቢሆን በራሳቸው ላይ ሲደርስ የተወሰኑ እንቅስቃሴዎችን እያደረጉ ቢሆንም ከጉዳዩ ክብደት አንፃር በቂ አይደለም ነው የሚሉት።

በመቀሌ ለሰብዓዊ ድጋፍ ተከማችቶ የነበረ ነዳጅ በሽብር ቡድኑ መዘረፉን አስመልክቶ የዓለም ምግብ ፕሮግራም መረጃውን ይፋ ከማድረጉ ጋር ተያይዞ የተለያዩ አስተያየቶች እየተሰጡ ቢሆንም በትክክል የዚህ ጥፋት ተጠያቂው አሸባሪዉ ሕወሓት ነውና ከድርጊቱ ሊቆጠብ ይገባል የሚል መልዕክት በሁሉም የውጭ አካላት አልተላለፈበትም፤ ይህ መሆኑ ደግሞ ምን ያህል የውጭ ጣልቃ ገብነት እንዳለበት የሚያስገነዝብ ነው ይላሉ።

ያም ሆነ ይህ ግን በአሁኑ ሰዓት ሕወሓት ላይ እየደረሰበት ያለው ውግዘት የመጣውም በቀጥታ በተራድኦ ድርጅቶች አማካኝነት በመሆኑ ተሰሚነቱ ከፍ ይላልና የኢትዮጵያ መንግስት አጋጣሚውን ቸል ሊለው እንደማይገባም መክረዋል። በእንግሊዝኛ ቋንቋ በስፋት እየተሰራጨ ያለውን የቡድኑን የዘረፋ መረጃ በተለያዩ ቋንቋዎች በማስተጋባት የዓለም ማህበረሰብ እንዲረዳ ማድረግ ይገባል ሲሉም መክረዋል።

ህዝቡም ቢሆን ለሀገር መዳን ቅድሚያ ሰጥቶ አሸባሪውን ቡድን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ አደብ ለማስገዛት የሚደረገውን ርብርብ ሊደግፍ ይገባልም ሲሉ ነው ምክራቸውን የለገሱት።

ይህ አሸባሪ ቡድን የትግራይ ህዝብን መበደል ከጀመረ ረጅም አመታትን አስቆጥሯል። ገና ወደስልጣን ለመምጣት ሲያልም ጀምሮ ጦሩን ሊደግፍልኝ ይችላል ያለውን ወንጀል ሁሉ ሲፈፅም እንደነበር ነው ዶ/ር ሀይለየሱስ ያስታወሱት።

ህይወትን ያለምግብና ውሃ ለማቆየት ትግል በሚደረግበት በ1977 ዓ.ም በሕወሓት ታጣቂ ቡድንና በወቅቱ የኢትዮጵያ መንግስት መካከል ከፍተኛ ውጊያ መካሄዱ የሚታወስ ነው። ይህ ወቅት ለበርካቶች የስቃይ ወቅትም ነበር። ሀገሪቷም ምድር ላይ ያለች ሲዖል የሚል ስያሜ ተሰጥቷት እንደነበር ታሪክ ያወሳል። ይህንን የተረዱት አለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅቶችም የህይወት አድን ስራን አንድ ብለው ቢጀምሩም መልካም ምግባራቸው ለፅንፈኞች ሲሳይ ነበር የሆነው። የሕወሓት የሽብር ቡድን ተላላኪ የሆኑ ሰዎች ረሀብተኛ አርሶ አደር መስለው በመቅረብ ለትግራይ ህዝብ የዕለት ደራሽ መግዣ እንዲውል የታቀደውን አንድ መቶ ሚሊዮን ዶላር ወደ ህወሓት ካዝና እንዲገባ አድርገዋል።

የፖለቲካ ተንታኝ አንድሪው ቆሪብኮ እኤአ ሰኔ 9 ቀን 2022 ለኢዜአ በሰጡት ማብራሪያ ላይ እንዳመለከቱት፤ አሸባሪው ህወሓት ወደ ቀድሞ የተንኮል ተግባሩ የተመለሰበትን ለሰብአዊ እርዳታ የቀረበን ንብረት ለጦርነት ማዋል ነው። በ1985 በኢትዮጵያ በተከሰተው ረሃብ ወቅት በሰሜን ኢትዮጵያ የተከሰተውን ረሃብ ለመዋጋት ከተሰበሰበው 100 ሚሊዮን ዶላር 95 በመቶውን የጦር መሳሪያ መግዛቱን አስታውሰዋል።

በድርቅ ለተጎዱና ለረሀብ ለተጋለጡ ኢትዮጵያውያን የተሰጠው ይህ ገንዘብ ለዚያን ጊዜ አማፂው ህወሓት የጦር መሳሪያ መግዣ መዋሉን የተለያዩ የፅሁፍና የድምፅ ማስረጃዎች ያመላክታሉ። በመረጃዎቹ መሰረትም አሸባሪው ሕወሓት በረሀብ ለተጎዱና በሞት አፋፍ ላይ ላለዉ የትግራይ ህዝብ ከመጣው የነፍስ አድን እህል መግዣ ውስጥ 95 በመቶ ያህሉን ለጦር መሳሪያ መግዣነት አውሎታል። በዚህ ሳቢያም በርካታ ህፃናትና አዋቂዎች እንደቅጠል እንዲረግፉ ሆነዋል። ይኸን ድርጊት ከፈፀመው 37 ዓመት ቢያልፉትም የተጣባው የዘረፋና ለዜጎች ቅንጣት ታህል አለማሰብ አባዜውን ዛሬም ደግሞታል።

የሽብር ቡድኑ የትግራይ ህዝቦች ይህንና ሌሎች በርካታ የሰቆቃ ጊዜያትን እንዲያሳልፉ ፈርዶባቸዋል። እየፈፀማቸው የመጡ የግፍ ተግባራትም በታሪክ ተከትበዋል።

የዛሬ ዓመት ገደማ የተፈፀመ ሌላ የእለት ደራሽ እህል ምዝበራ የቅርብ የአሸባሪው ህወሓት ነውራዊ ተግባር ማሳያ ነው። አሸባሪው ቡድን ከተሞችን አውድሞና የነዋሪዎችን ሀብት ከዘረፈ በኋላ የዩኤስ ኤይድ የእርዳታ እህል ማከማቻን በመስበር የእለት ደራሽ እርዳታን ዘርፎ ወስዷል።

ባሳለፍነው ሳምንት ረቡዕ ደግሞ ሰብዓዊ ርዳታዎችን ለሚያመላልሱ ተሸከርካሪዎች አገልግሎት የሚውልና በዓለም ምግብ ፕሮግራም መቀሌ መጋዘን የተከማቸ ነዳጅ መዝረፉም ይፋ መሆኑ አይዘነጋም። ዳግም ከተቀሰቀሰው ውጊያ ጋር በተያያዘ ነሀሴ 18 ቀን 2014 ዓ.ም ማለዳ ላይ መቀሌ የሚገኘው የዓለም ምግብ ፕሮግራም መጋዘን በትግራይ ኃይሎች ዘረፋ መፈፀሙንም ያመላከተው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ነው።

የተመድ የሰብአዊ ጉዳዮች ምክትል ዋና ጸሃፊና የአስቸኳይ ድጋፍ አስተባባሪው ማርቲን ግሪፊዝም፤ በመቀሌ በሚገኘው የዓለም የምግብ ፕሮግራም መጋዘን ላይ የተፈፀመውን የነዳጅ ዝርፊያ አውግዘዋል።

ዋና ፀሀፊው በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት ሃሳብ፤ በትግራይ ክልል መቀሌ በሚገኘው የዓለም ምግብ ፕሮግራም መጋዘን ውስጥ የነበረው ነዳጅ በችግር ውስጥ ላሉ ዜጎች የሰብዓዊ ድጋፍ አገልግሎት ለማድረስ የሚያስችል ነበር ብለዋል። የነዳጁ መዘረፍ የምግብ ዋስትና እጦት እየጨመረ ባለበት በዚህ ወቅት መዘዙ አስከፊ ሊሆን እንደሚችል አመላክተዋል።

በወቅቱ በወጣው መረጃም ቡድኑ 12 የነዳጅ ቦቴዎችን በአጠቃላይ 570 ሺህ ሊትር ነዳጅ መዝረፉ ነው የተመላከተው። ቡድኑ ድርጊቱን የፈፀመው በኃይል በመሆኑ በስፍራው ያሉ አካላት ለመከላከል እንዳልቻሉ ነው መረጃዎች የሚያመላክቱት።

ይህ ሁሉ ሲሆን ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የሚመለከታቸው ሃላፊዎቻቸው ድርጊቱ አሳስቦናል ከሚል መግለጫ በስተቀር አንዳች ርምጃ ሲወስዱ አልታዩም። አሸባሪው ሕወሓት አሁን ከፈፀመው ኢሰብአዊ ድርጊት አንጻር አለም አቀፋዊ ጫናዎች እንደሚደረጉ የሚጠበቅ ቢሆንም እስከአሁን በዚያ ደረጃ የተወሰዱ ርምጃዎች የሉም። በዘረፋ ሱስ የተጠመደዉ አሸባሪዉ ሕወሓትም ከኢትዮጵያ መንግስት የቀረበለትን የሰላም አማራጭ በመተዉ በመንግስት ላይ ጦርነት ከፍቷል። (አዲስ ሚዲያ-በየሺ ወልዴ)



Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule