• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ትህነግና ኢትዮ 360 በአማራ ክልል ሰብል እንዲወድም በቅንጅት እየሠሩ ነው

October 3, 2022 08:15 am by Editor 2 Comments

ምዕራብ ጎንደርን ጨምሮ ሰፊ እርሻ መሬት ያላቸው አካባቢዎች ሰብል የሚሰበስብ ሰራተኛ ማስታወቂያ ሲያወጡ ይህ የመጀመርያቸው አይደለም። ማህበራዊ ሚዲያ በማይታወቅበት ጊዜ በኢቲቪና አማራ ቲቪ ጭምር በሚሊዮን የሚቆጠር ሰራተኛ እንፈልጋለን ብለው ማስታወቂያ ሲያስነግሩ ኖረዋል።

ባለፈው አመት በዛ ቃውጢ ጦርነት ወቅት በማህበራዊ ሚዲያ በርካታ ሰብል የሚሰበስብ ሰራተኛ በማስታወቂያ ጠርተዋል። በሌላ አካባቢ ያለው አርሶ አደር የራሱ ሰብል እስኪደርስ ለአንድና ሁለት ወር ሰርቶ እንደሚመለስ ይታወቃል። በቋሚነት በርሃ ወርዶ የሚሰራ፣ ካምፕ ተሰርቶለት በአካባቢው የሚከርም ሞልቷል። የሰብል ስብሰባን ብቻ ስራቸው አድርገው በቆላማ አካባቢዎቹ የሚኖሩ በርካታ ወጣቶች አሉ። ለረዥም አመታት ዩኒቨርሲቲዎች ከሚቀበሉት ወጣት በላይ የቋራ፣ የመተማ፣ አርማጭሆ፣ ወልቃይት ጠገዴ አካባቢዎች ሰብል የሚሰበስብ ወጣት ይቀበላሉ። በርካታ ህዘብ የሚሳተፍበት ስለሆነ አዲስ ገቢዎቹ ጎፈር፣ የለመዱት ሳሉግ እየተባሉ ይጠራሉ። በቆላማ አካባቢዎች በሰራተኞች የተመሰረቱ ከተሞች አሉ።

 ከ1950 በኋላ የትግራይ ወጣት ሳይቀር ተከዜን ዋኝቶ ተሻግሮ ሰርቶ ወደ ትግራይ ይመለስ ነበር። በዚህ ወቅትም ከደቡብ ኢትዮጵያ ድረስ ለሰብል ስብሰባ የሚመጡ ወጣቶች አሉ። አይደለም ሰብል ስብሰባው ሙጫና እጣን ለቀማው በሺህ ለሚቆጠር  ወጣት የስራ አድል ይፈጥራል። ሰብል ለመሰብሰብ ብቻ አይደለም እያንዳንዱ አራሽ አካባቢውን የሚጠብቁለት ሚሊሻዎች ይቀጥራል። ስራ አስኪያጅ ይቀጥራል። አንዳንዱ ካምፕ ከትንንሽ ሰፈሮች አይተናነስም። አንድ አርሶ አደር በርካታ ሰራተኞች ይዞ ይከርማል። አንድ አርሶ አደር ለስድስት  ወር ያህል ለአንድ የሰራተኞች አስተባባሪ  ከፍተኛው እስከ 120 ሺህ ብር  ድረስ እየከፈለው ነው።  በወር 20 ሺህ ብር ማለት ነው። ምግብና መጠለያ ተችሎት።

አንድ ሚሊሻ  ለስድስት ወር እስከ 80 ሺህ ብር እየተከፈለው ነው።  በወር ከ10 ሺህ ብር በላይ ነው። ምግብና መጠለያን አሰሪው ችሎ ጎን ለጎን የተወሰነ  ሄክታር ይታረስላቸዋል። ሚሊዮን ሰራተኛ ወደ አካባቢው የሚሄደው  እንዲህ አዋጭ ስለሆነ ነው።

ይህ ሆኖ እያለ ታዲያ ለሰብል ስብሰባ ማስታወቂያ ሲወጣ የመከላከያ ምልመላ አስመስሎ መጀመርያ ያቀረበው ትህነግ ነው። ከእሱ ጋር የሚሰሩና በሱዳን በኩል ሰርገው እየገቡ ህዝብን ለማጥቃት ሲጥሩ የከረሙ ተላላኪዎችም ቀስቅሰውበታል። እነዚህ አካላት ሰብል ሲያቃጥሉ፣ የአርሶ አደሩን ከብት ሲገድሉ የሚታወቁ ናቸው።

አሁንም የሰብል ስብሰባ ማስታወቂያውን ሆን ብለው በሀሰት ወታደራዊ ምልመላ አስመስለው የሰሩበት ህዝብ ሰብሉን እንዳይሰበስብ ነው። አካባቢውን ወርረው ሰብሉን ማቃጠል ባይችሉ ሳይሰበሰብ እንዲቀር የሀሰት ዘመቻ ከፍተዋል። ኢትዮ 360 የሚባል ሚዲያ ይህን የህወሓት አጀንዳ እያራገበ ይገኛል። ይህን ህዝብ ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ሆን ብሎ ካላስተላለፈ በአስቸኳይ ይቅርታ ሊጠይቅ ይገባል። ህወሓት የአማራን ባለሀብት የሰሊጥ ነጋዴ ወዘተ እያለ ሲፈርጅ ከርሟል። አሁን ሰሊጡ እንዳይሰበሰብ ሲቀሰቅስ 360 ተደርቦ በህዝብ ጥቅም ላይ ዘምቷል።

ለሰራዊት አፈሳ ቢፈለግ ወጣቱ ያለ በየከተማውና በየቤቱ ነው። ምዕራብ ጎንደር ድረስ መሄድ አይጠበቅበትም። ምዕራብ ጎንደር ማንንም አታልሎ ወደ ጦር ግንባር የሚያስገባ አይደለም። አርሶ አደሩ ብቻውን ሱዳንን ቀጥ አድርጎ የያዘ የእነ ባሻ ጥጋቡ ቀዬ ነው። ኢትዮጵያም አንድ ሚሊዮን ምልምል አያስፈልጋትም። 

ምዕራብ ጎንደርንና አካባቢውን የማያውቁ ይህን ያህል ሰራተኛ ምን ሊሰራ ነው ብለው ሊጠይቁ ይችላሉ። በህወሓት አላማ ወይንም በምቀኝነት ግን ሰብል እንዳይሰበሰብ ሊቀሰቅሱ ባልተገባ ነበር። ኢትዮ 360 በጦርነቱ ምክንያት መሬት ጦሙን አደረ ሲል ከርሞ፣ አሁን ለሰብል ስብሰባ የሰራተኛ ቅጥር ሲወጣ የህወሓትን አጀንዳ እያራገበ በህዝብ ላይ ሌላ ጦርነት ከፍቷል። በአንድ ዞን ሚሊዮን የስራ እድል ሲፈጠር እንዲስተጓጎል እየሰሩ ነው።  ይህን የተናገሩ ሰዎች  በግብታዊነት ከሆነ ይቅርታ ሊጠይቁ ይገባል። አርሶ አደር ሰብል እንዳይሰበስብ ቅስቀሳ ማድረግ በህዝብ ላይ ጦርነት መክፈት ነው። ሚሊዮን ወጣት ስራ እንዳይሰራ መቀስቀስ ወንጀል ነው። ያፈጠጠ የህዝብ ጠላትነት ነው። (ጌታቸው ሽፈራው)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: Ethio 360, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    October 4, 2022 06:48 pm at 6:48 pm

    ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በህዋላ ዓለም በሁለት የአስተሳሰብ ምልከታ ተገምሳ ይህም ያም ሲታመስ ከነበረው የቀዝቃዛው ጦርነት ይልቅ አሁን በምድር ላይ የሚደረገውና ሊሆነ የታሰበው አስፈሪ ነው። አንድ በኳስ ጫወታ ዙሪያ በተፈጠረ ግርግር ተጨፍልቆ ሲሞት ሌላው ለሃገርህ ለወገንህ ለዘርህ ነው እየተባለ ወደ ቄራ እንደሚወሰድ ከብቶች ያለ ልቡ ይጨፈጨፋል፤ ይጨፈጭፋል። አሁን ዪክሬንን አይዞአችሁ የሚሉ የምዕራባዊያን ሃገሮች ሁሉ ለራሳቸው ሥጋት እንጂ ለዪክሬን ህዝብና ምድር ደንታ የላቸውም። ያ ቢሆን ኑሮ በ 2014 በነጮች ክሬሚያ ስትያዝ ጦራቸውን ባሰለፉም ነበር። የሰሜን ኮሪያው እብድ በጃፓንና በደቡብ ኮሪያ ጭንቅላት ሚሳኤል አሳልፎ ባህር ላይ ሲጥል፤ የራሽያው መሪና ደጋፊዎቹ ታክቲካል የኒኩሌር መሳሪያ ጦር ሜዳ ላይ እንዲውል ሲወተውቱ ረጅም ድላ ባይመቱበት ያስፈራሩበት እንዲሉ ዋሽንግተን ደግሞ ዋ እንዳታረገው በማለት አስጠንቅቃለች። እውቁ የቲዎሮቲካል ፊዚክስ ምሁር Stephen Hawking ስለ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ባንድ መድረክ ተጠይቆ እንዲህ ብሎን ነበር። “I fear that AI may replace humans altogether. If people design computer viruses, someone will design AI that improves and replicates itself. This will be a new form of life that outperforms humans”. አሁን እሱ በህይወት የለም እየሆነ ያለው ያ ነው። ዛሬ በድሮን ውጊያ ከመግደል በፊትና ከተገደሉ በህዋላ እያዪ መጨፈር የተለመደ ሆኗል። ጀግና ተኳሽና አታኳሽ የሚባለውም እየከሰመ ይገኛል። ሁሉም በቴክኖሎጂ እየታገዘ ከሩቅና ከቅርብ ነገሮችን ያወድማል። Deep fake and doctored up Video and Audio የሰውን አስተሳሰብ ለማዛባት ያለ ልክ ይረጫሉ። በዚህ ላይ ረሃቡ፤ በሽታውና የተፈጥሮ ቸንፈር ባለጠጋና ድሃ ሳይል እያጠረገው ይገኛል። ባጭሩ ዓለማችን አረንቋ ውስጥ ለመግባት በመንደርደር ላይ ትገኛለች። ጫፉ ላይ ደርሳለች።
    ወደ አፍሪቃ ስንመለስ ይበልጡ ችግራችን ራሳችን በራሳችን ላይ የምናደርሰው ነው። ሰው በገንዘብ ታውሮ የህክምና ባለሙያው በችኮላ አንዷን ቀዶ ሳትነሳ ሌላ ሊቀድ የሚሄድ፤ የሚታዘዘው መድሃኒት በእጅ አዙር ከራሱ ወይም ከዘመድ የመድሃኒት መደበር እንዲገዛ የሚያዝ፤ ለዚያውም የማያድን የቻይና መድሃኒት! ቆመው ክሊኒክና ሆስፒታል ሊታከሙ ወይም ለወሊድ ገብተው አስከሬናቸው የወጣ እልፎች ናቸው። ብቻ ነገር ሁሉ አስረሽ ምቺው ሆኗል። ወያኔ የእህል ክምር የሚያቃጥል፤ የቁም ከብቶችን በጥይት ተኩሶ የሚገል የበድኖች ጥርቅም ስለሆነ ከወያኔ መልካም ነገር አይጠበቅም። ግን ሰው በሸፍጥና ሌላውን በማሰቃየት እስከ መቼ ነው የሚኖረው? ዘመናችን እኮ የተወሰነ ነው። እስከ መቼ ነው ለትግራይ ህዝብ ለአማራ ህዝብ እየተባለ ህዝቡ በስሙ የሚነገድበት? እንዴት ሰው ቤት እያቃጠለ፤ ሰው እያረደ፤ ሃገር እያፈረሰ፤ ምርት እያወደመ ተራብን ድረሱልን በማለት ይጣራል? ህዝባችን የሚያልፍለት መቼ ነው? የተመድና የአሜሪካ ተራዶ ድርጅቶች ተጠዋሪ ከመሆን መቼ ነው የሚድነው? ግን እብዶች ለብሰው ሰው ነን በሚሉበት ሃገር ማን ማንን ይሰማል? መጋደል መገዳደል ነው። በሁመራ፤ በመተማ፤ በሌሎችም ሰሊጥ፤ ጥጥ፤ ሌላም የተለያዪ አዝዕርቶችን በሚያበቅሉ ቦታዎች ሰዎች ለጉልበት ሥራ መጠራታቸው ዛሬ የተጀመረ አይደለም። በፊትም ነበር። ሰው ከሃገሪቱ ልዪ ልዪ ክፍሎች ወደዚያ በመጓዝ የቀን ሥራ አይነት (በጊዜአዊነት) ስርቶ ጠቀም ያለ ገንዘብ ይዞ ያኔም ይመለስ ነበር። አሁን ይህን ጥሪ እንደ ጦር መሳሪያ የሚጠቀሙበት ድርቡሾች ሁሉ ለሃገር የማያስቡ እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል የሚሉ ብቻ ናቸው። እኛም እናልፋለን። መቼ ነው ከእውነት ጎን የምንቆመው? ያ ጊዜ ይመጣ ይሆን? አላውቅም። ከስር ባለው የ19ኛ ክፍለዘመን የእንግሊዘኛ ግጥም ሃሳቤን እደመድማለሁ።
    To every man upon this Earth
    Death cometh soon or late.
    And how can man die better
    Than facing fearful odds
    For the ashes of his fathers
    And the temples of his gods? Thomas Babington Macaulay – Horatius

    Reply
  2. sintayhu says

    October 18, 2022 03:25 am at 3:25 am

    You have lost credibility big time.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule