• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የትህነግና የሸኔ ተላላኪዎች በናዝሬት እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል

October 1, 2022 07:48 am by Editor Leave a Comment

በአዳማ ከተማ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን ጨምሮ 82 የሸኔና የህወሃት ተላላኪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገለጸ::

ሐሙስ መስከረም 19 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) በአዳማ ከተማ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን ጨምሮ 82 የሸኔና አሸባሪው ህወሃት ተላላኪዎች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የከተማዋ ፀጥታና አስተዳደር ጽሕፈት ቤት ገልጿል።

የአዳማ ከተማ ፀጥታና አስተዳደር ጽሕፈት ቤት ሀላፊ መኩሪያ ድንቁ ለኢዜአ እንደገለጹት አሸባሪው ሸኔና የህወሃት ተላላኪዎች በከተማዋ መስቀልና ኢሬቻን ጨምሮ ህዝባዊ በዓላትን ለማወክ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ  ነበር።

በዚህም 33 የሸኔና አባ ቶርቤ አባላት እንዲሁም 49 የህወሃት ሴሎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ገልጸዋል።

በመጪው ቅዳሜና እሁድ በሆራ ፊንፊኔና ቢሾፍቱ ሆራ አርሰዲ የሚከበረው የኢሬቻ በዓል ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲጠናቀቅ መስተዳደሩ ከምስራቅ ሸዋ ዞንና አጎራባች ከተሞች ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይ የተቀናጀ የፀጥታ አካላት ስምሪት በመስጠት የፀጥታ ሃይላትን በአንድ ላይ በከተማዋ በአራቱም መግቢያና መውጫ ቦታዎች ላይ በቅንጅት የፍተሻ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በተለይ የኢሬቻ በዓል ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍተሻ ሥራው ሙያዊ እንዲሆን የፌዴራልና የኦሮሚያ ልዩ ሃይልን ጨምሮ መደበኛ ፖሊሶችን በማሰማራት ውጤታማ ሆነናል ብለዋል።

በዚህም 19 ሽጉጦች፣ 6 ክላሽና ከ3ሺህ በላይ የተለያዩ ተተኳሽ ጥይቶች መያዛቸውን አመልክተዋል።

እንግዶች አዳማ ከተማ አርፈው ወደ አዲስ አበባና ቢሾፍቱ የሚሄዱ በመሆኑ የፀጥታ ስራውን ከምስራቅ ሸዋ ጋር ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ ሰርጎ ገቦችን የመከታተል እና የፍተሻ ስራዎችን በጋራ በመስራታችን ውጤታማ ሆነናል ብለዋል።

በከተማ ደረጃ ያለውን የፀጥታ ምክር ቤት እስከ ቀበሌ ድረስ በማጠናከር በየሳምንቱም ግምገማ እያከናወኑ መሆኑም ጠቅሰዋል።

አባ ቶርቤ ተብሎ ወደ ከተማዋ የገባውና በቁጥጥር ሥር የዋለው ግለሰብ ከኢትዮጵያ ውጭ  በአሸባሪው ሸኔ ወታደራዊ ስልጠና ወስዶ ከሌሎች ግብረ አበሮቹ ጋር የመጣ መሆኑን ሀላፊው ጠቅሰው በአዳማም ሆነ በዙሪያዋ የሰርጎገቦችን እንቅስቃሴ ለማምከን ጠንክረን እንሰራለን ብለዋል። (አዲስ ማለዳ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule