• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የትህነግና የሸኔ ተላላኪዎች በናዝሬት እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል

October 1, 2022 07:48 am by Editor Leave a Comment

በአዳማ ከተማ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን ጨምሮ 82 የሸኔና የህወሃት ተላላኪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገለጸ::

ሐሙስ መስከረም 19 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) በአዳማ ከተማ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን ጨምሮ 82 የሸኔና አሸባሪው ህወሃት ተላላኪዎች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የከተማዋ ፀጥታና አስተዳደር ጽሕፈት ቤት ገልጿል።

የአዳማ ከተማ ፀጥታና አስተዳደር ጽሕፈት ቤት ሀላፊ መኩሪያ ድንቁ ለኢዜአ እንደገለጹት አሸባሪው ሸኔና የህወሃት ተላላኪዎች በከተማዋ መስቀልና ኢሬቻን ጨምሮ ህዝባዊ በዓላትን ለማወክ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ  ነበር።

በዚህም 33 የሸኔና አባ ቶርቤ አባላት እንዲሁም 49 የህወሃት ሴሎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ገልጸዋል።

በመጪው ቅዳሜና እሁድ በሆራ ፊንፊኔና ቢሾፍቱ ሆራ አርሰዲ የሚከበረው የኢሬቻ በዓል ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲጠናቀቅ መስተዳደሩ ከምስራቅ ሸዋ ዞንና አጎራባች ከተሞች ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይ የተቀናጀ የፀጥታ አካላት ስምሪት በመስጠት የፀጥታ ሃይላትን በአንድ ላይ በከተማዋ በአራቱም መግቢያና መውጫ ቦታዎች ላይ በቅንጅት የፍተሻ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በተለይ የኢሬቻ በዓል ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍተሻ ሥራው ሙያዊ እንዲሆን የፌዴራልና የኦሮሚያ ልዩ ሃይልን ጨምሮ መደበኛ ፖሊሶችን በማሰማራት ውጤታማ ሆነናል ብለዋል።

በዚህም 19 ሽጉጦች፣ 6 ክላሽና ከ3ሺህ በላይ የተለያዩ ተተኳሽ ጥይቶች መያዛቸውን አመልክተዋል።

እንግዶች አዳማ ከተማ አርፈው ወደ አዲስ አበባና ቢሾፍቱ የሚሄዱ በመሆኑ የፀጥታ ስራውን ከምስራቅ ሸዋ ጋር ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ ሰርጎ ገቦችን የመከታተል እና የፍተሻ ስራዎችን በጋራ በመስራታችን ውጤታማ ሆነናል ብለዋል።

በከተማ ደረጃ ያለውን የፀጥታ ምክር ቤት እስከ ቀበሌ ድረስ በማጠናከር በየሳምንቱም ግምገማ እያከናወኑ መሆኑም ጠቅሰዋል።

አባ ቶርቤ ተብሎ ወደ ከተማዋ የገባውና በቁጥጥር ሥር የዋለው ግለሰብ ከኢትዮጵያ ውጭ  በአሸባሪው ሸኔ ወታደራዊ ስልጠና ወስዶ ከሌሎች ግብረ አበሮቹ ጋር የመጣ መሆኑን ሀላፊው ጠቅሰው በአዳማም ሆነ በዙሪያዋ የሰርጎገቦችን እንቅስቃሴ ለማምከን ጠንክረን እንሰራለን ብለዋል። (አዲስ ማለዳ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule