የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የህውሓት ቡድን ከጠላት ጋር ጥምረት በመፍጠር ለእኩይ አላማ ሊጠቀምበት የነበረውን አውሮፕላን ማረፊያን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥሯል። በርካታ ህወሓት ያደራጃቸው የልዩ ኃይል፣ የፖሊስ እና የሚሊሻ አባላት ለመከላከያ ሠራዊት እጃቸውን እየሰጡ መሆናቸውም ታውቋል። ሠራዊቱ ዘራፊው የህወሓት ቡድን ያደረሰበትን ድንገተኛ ጥቃት በመመከት የመልሶ ማጥቃት ስራ እየሰራ መሆኑ ይታወቃል። በዚህም የኢፌዴሪ የመከላከያ ሰራዊት እስካሁን ማይዳሊ፣ ዳንሻ፣ ባዕከር፣ ልጉዲ እንዲሁም የሁመራ ሱዳን መንገድን እንደተቆጣጠረ መቆጣጠሩ ይታወቃል። (ፋና) ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about መከላከያ ሠራዊት የአማራ ክልል ሁመራ ኤርፖርት ተቆጣጣረ
operation dismantle tplf
በስግብግቡ የህወሃት ጁንታ ኃይል ላይ የተወሰደው የመጀመሪያው ዙር ኦፕሬሽን በስኬት ተጠናቋል
በስግብግቡ የሕወሓት ጁንታ ኃይል ላይ የተደረገው የመጀመሪያው ዙር ኦፕሬሽን በስኬት እንደተጠናቀቀ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታውቀዋል። የአየር ኃይሉ በወሰደው እርምጃም በተለያዩ ስፍራዎች ላይ የነበሩ ሮኬቶችን ጨምሮ ሌሎች የተለያዩ ከባድ የጦር መሳሪያዎችን ሙሉ በሙሉ ለማውደም መቻሉንም ገልፀዋል። "የአየር ኃይሉ በወሰደው እርምጃ በተለያዩ ስፍራዎች ላይ የነበሩ ሮኬቶችን ጨምሮ ሌሎች የተለያዩ ከባድ የጦር መሳሪያዎችን ሙሉ በሙሉ ለማውደም ተችሏል። እነዚህ ሮኬቶች እስከ 300 ኪሎ ሜትሮች መወንጨፍ የሚችሉ በመሆናቸው እና በወንጀለኛው ቡድን ሮኬቶቹን የመጠቀም ፍላጎት በመኖሩ በመቐለ እና አካባቢዋ በነበረው የከባድ መሣሪያ ማስቀመጫ ላይ የአየር ኃይሉ እርምጃ እንዲወስድ ተደርጓል" ጠ/ሚ/ር ዐቢይ። አምባገነኑን እና ዘራፊውን የጁንታ ቡድን በአጭር ግዜ ውስጥ ይዘን … [Read more...] about በስግብግቡ የህወሃት ጁንታ ኃይል ላይ የተወሰደው የመጀመሪያው ዙር ኦፕሬሽን በስኬት ተጠናቋል


