• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

34 የወንበዴው ትህነግ የፋይናንስ ተቋማት ታገዱ

November 17, 2020 03:25 am by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ወንበዴው ህወሃት/ትህነግ አገር ለማፍረስ ዓላማ ሲጠቀምባቸው የነበሩት 34 የፋይናንስ ተቋቱን ማገዱን ይፋ አድርጓል።

እንደ ኢቲቪ ዘገባ ከታገዱት የበረኻ ወንበዴዎቹ ድርጅቶች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፤

ሜጋ ማተሚያ፣

ሱር ኮንስትራክሽን፣

ጉና የንግድ ሥራዎች፣

ኢፈርት ኤሌክትሪካል ቢዝነስ፣

ትራንስ ኢትዮጵያ፣

መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ፣

ሠላም የህዝብ ማመላለሻ ማህበር፣

ኢፈርት ኃ/የተ/የግ ማህበር እገዳው ከተላለፈባቸው መካከል ናቸው።

ጎልጉልን ጨምሮ የተለያዩ የሚዲያ አውታሮች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ ወዘተ ለትህነግ የፋይናንስ ምንጭ የሆነው ኤፈርት ወደ ሕዝብ ሃብትነት እንዲመለስ ሲወተውቱ መቆየታቸው ይታወሳል።

ስብሃት ነጋና ቤተሰቡ የተቆጣጠረው ኤፈርት ግብር የማይከፍል፣ የአገር ሃብት ወደፈለገው ፈሰስ የሚያደርግ፣ ኦዲት የማይደረግ፣ በኃላፊነት የማይጠየቅ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ሃብት በመዝረፍ የተቋቋመውን ድርጅት ስብሃት ነጋ ራሴና ጥቂቶች ሆነን ገንዘባችን አዋጥተን የመሠረትነው በማለት በተደጋጋሚ ሲናገር ተደምጧል።

በወንበዴዎቹ ላይ በተከፈተው ሕግን የማስከበር እርምጃ ሱር ኮንስትራክሽን በርካታ ምሽጎችን በመሥራት ለትህነግ የላቀ አገልግሎት ሲሰጥ እንደነበር የሚታወቅ ነው።

ተጨማሪ መረጃ

ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ በፌስቡክ ገጹ ያወጣው መረጃ እንዲህ ይነበባል፤

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የዘር ተኮር ጥቃት እና የሽብር ድርጊት እንዲፈጸም የገንዘብ ድጋፍ በማቅረብ፣ ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ ከሚንቀሳቀሰው የትህነት/ ህወሃት ሀይል ጋር ግንኙነት በመፍጠር፤ በመመሳጠር እንዲሁም የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ የተሳተፉ ስለመሆናቸው እና በግብር ስወራ እና የሙስና ወንጀል ድርጊቶች ውስጥ ስለመሳተፋቸው ምርመራ ለመጀመር የሚያበቃ በቂ ማስረጃ የተገኘባቸውን ከታች ስማቸው የተጠቀሱትን ድርጅቶች የሚንቀሳቀሱ እና የማይንቀሳቀሱ ንብረቶችን በባንክ ያለቸውን ገንዘብ ጨምሮ ከህዳር 07 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ እንዲታገዱ አድርጓል።

ዕግዱ አስፈላጊ የሆነበት ምክንያት ድርጅቶቹ ሀብታቸውን ለማሸሽ ጥረት በማድረግ ላይ እንደሆኑ በቂ ማስረጃ የቀረበ በመሆኑ ንበረቶቹ ሳይሸሹ ተገቢውን ቁጥጥር በማድረግ ውሳኔ እስኪሰጥባቸው ማቆየት ተገቢ መሆኑ ስለታመነበት ነው።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ በወንጀል የተገኘ ሀብት ማስመለስ ዳይሬክቶሬት ጄኔራል የመመርመር እና ሀብትን የማስመለስ ስራውን እስኪያጠናቅቅ ድረስ የታገዱት ንብረቶች እንዳይጎዱ እና እንዳይባክኑ ጠብቆ የሚያቆይ የንብረት አስተዳዳሪ የሚሾም ሲሆን አስተዳዳሪው ስራውን ተቀብሎ ማስተዳደር እስኪጀምር ድረስ የድርጅቶቹ አስተዳዳሪዎች ንበረቱን በሚገባ የመጠበቅ ኃላፊነት አለባቸው።

በቀጣይ የምርመራ እና ክስ ሂደቱን ተከታትለን ለህዝቡ የምናሳውቅ ሆኖ የታገዱት ድርጅቶች ከዚህ በታች ስማቸው የተዘረዘሩት መሆናቸውን እንገልጻለን።

1. ሱር ኮንስትራክሽን

2. ጉና የንግድ ስራዎች ኃ/የተ/የግ/ማህበር

3. ትራንስ ኢትዮጵያ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

4. መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

5. ሰላም የህዝብ ማመላለሻ አክሲዮን ማህበር

6. ሜጋ ማተሚያ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

7. ኤፈርት ኃ/የተ/የግ/ማህበር

8. ኤፈርት ኤሌክትሪካል ቢዝነስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

9. ኤፈርት ዲዛይን እና ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር

10. ኢዛና ማዕድን ልማት ኃ/የተ/የግ/ማህበር

11. ቬሎሲቲ አፖራልዝ ካምፓኒስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

12. መሰቦ ቢውልዲንግ ማቴሪያል ፕሮዳክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር

13. ሳባ ዳይሜንሺናል ስቶን ኃ/የተ/የግ/ማህበር

14. መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ

15. ሼባ ታነሪ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

16. ኤ.ፒ ኤፍ

17. ሜጋ ኔት ኮርፖሬሽን

18. እክስፕረስ ትራንዚት ሰርቪስ

19. ደሳለኝ ካትሪናሪ

20. ሼባ ታነሪ ፋክተሪ አክሲዮን ማህበር

21. ህይወት አግሪካልቸር መካናይዜሽን

22. ህይወት እርሻ ሜካናይዜሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር

23. አልመዳ ጋርመንት ፋክተሪ

24. መሶቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ

25. ደደቢት ብድርና ቁጠባ አክሲዮን ማህበር

26. አዲስ ፋርማሲቲካልስ ፕሮዳክሽን

27. ትግራይ ዴቨሎፕመንት ኃ/የተ/የግ/ማህበር

28. ስታር ፓርማሲቲካልስ ኢፖርተርስ

29. ሳባ እምነበረድ አክሲዮን ማህበር

30. አድዋ ፍሎር ፋክተሪ

31. ትካል እግሪ ምትካል/ ትግራይ/ ት.እ.ም.ት/

32. ብሩህ ተስፋ ፕላስቲክ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

33. ደሳለኝ የእንስሳ መድኃኒት አስመጪና አከፋፋይ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

34. ማይጨው ፓርትክል ቦርድ ፋክተሪ

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ  

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: effort, operation dismantle tplf, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule