• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

34 የወንበዴው ትህነግ የፋይናንስ ተቋማት ታገዱ

November 17, 2020 03:25 am by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ወንበዴው ህወሃት/ትህነግ አገር ለማፍረስ ዓላማ ሲጠቀምባቸው የነበሩት 34 የፋይናንስ ተቋቱን ማገዱን ይፋ አድርጓል።

እንደ ኢቲቪ ዘገባ ከታገዱት የበረኻ ወንበዴዎቹ ድርጅቶች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፤

ሜጋ ማተሚያ፣

ሱር ኮንስትራክሽን፣

ጉና የንግድ ሥራዎች፣

ኢፈርት ኤሌክትሪካል ቢዝነስ፣

ትራንስ ኢትዮጵያ፣

መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ፣

ሠላም የህዝብ ማመላለሻ ማህበር፣

ኢፈርት ኃ/የተ/የግ ማህበር እገዳው ከተላለፈባቸው መካከል ናቸው።

ጎልጉልን ጨምሮ የተለያዩ የሚዲያ አውታሮች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ ወዘተ ለትህነግ የፋይናንስ ምንጭ የሆነው ኤፈርት ወደ ሕዝብ ሃብትነት እንዲመለስ ሲወተውቱ መቆየታቸው ይታወሳል።

ስብሃት ነጋና ቤተሰቡ የተቆጣጠረው ኤፈርት ግብር የማይከፍል፣ የአገር ሃብት ወደፈለገው ፈሰስ የሚያደርግ፣ ኦዲት የማይደረግ፣ በኃላፊነት የማይጠየቅ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ሃብት በመዝረፍ የተቋቋመውን ድርጅት ስብሃት ነጋ ራሴና ጥቂቶች ሆነን ገንዘባችን አዋጥተን የመሠረትነው በማለት በተደጋጋሚ ሲናገር ተደምጧል።

በወንበዴዎቹ ላይ በተከፈተው ሕግን የማስከበር እርምጃ ሱር ኮንስትራክሽን በርካታ ምሽጎችን በመሥራት ለትህነግ የላቀ አገልግሎት ሲሰጥ እንደነበር የሚታወቅ ነው።

ተጨማሪ መረጃ

ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ በፌስቡክ ገጹ ያወጣው መረጃ እንዲህ ይነበባል፤

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የዘር ተኮር ጥቃት እና የሽብር ድርጊት እንዲፈጸም የገንዘብ ድጋፍ በማቅረብ፣ ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ ከሚንቀሳቀሰው የትህነት/ ህወሃት ሀይል ጋር ግንኙነት በመፍጠር፤ በመመሳጠር እንዲሁም የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ የተሳተፉ ስለመሆናቸው እና በግብር ስወራ እና የሙስና ወንጀል ድርጊቶች ውስጥ ስለመሳተፋቸው ምርመራ ለመጀመር የሚያበቃ በቂ ማስረጃ የተገኘባቸውን ከታች ስማቸው የተጠቀሱትን ድርጅቶች የሚንቀሳቀሱ እና የማይንቀሳቀሱ ንብረቶችን በባንክ ያለቸውን ገንዘብ ጨምሮ ከህዳር 07 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ እንዲታገዱ አድርጓል።

ዕግዱ አስፈላጊ የሆነበት ምክንያት ድርጅቶቹ ሀብታቸውን ለማሸሽ ጥረት በማድረግ ላይ እንደሆኑ በቂ ማስረጃ የቀረበ በመሆኑ ንበረቶቹ ሳይሸሹ ተገቢውን ቁጥጥር በማድረግ ውሳኔ እስኪሰጥባቸው ማቆየት ተገቢ መሆኑ ስለታመነበት ነው።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ በወንጀል የተገኘ ሀብት ማስመለስ ዳይሬክቶሬት ጄኔራል የመመርመር እና ሀብትን የማስመለስ ስራውን እስኪያጠናቅቅ ድረስ የታገዱት ንብረቶች እንዳይጎዱ እና እንዳይባክኑ ጠብቆ የሚያቆይ የንብረት አስተዳዳሪ የሚሾም ሲሆን አስተዳዳሪው ስራውን ተቀብሎ ማስተዳደር እስኪጀምር ድረስ የድርጅቶቹ አስተዳዳሪዎች ንበረቱን በሚገባ የመጠበቅ ኃላፊነት አለባቸው።

በቀጣይ የምርመራ እና ክስ ሂደቱን ተከታትለን ለህዝቡ የምናሳውቅ ሆኖ የታገዱት ድርጅቶች ከዚህ በታች ስማቸው የተዘረዘሩት መሆናቸውን እንገልጻለን።

1. ሱር ኮንስትራክሽን

2. ጉና የንግድ ስራዎች ኃ/የተ/የግ/ማህበር

3. ትራንስ ኢትዮጵያ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

4. መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

5. ሰላም የህዝብ ማመላለሻ አክሲዮን ማህበር

6. ሜጋ ማተሚያ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

7. ኤፈርት ኃ/የተ/የግ/ማህበር

8. ኤፈርት ኤሌክትሪካል ቢዝነስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

9. ኤፈርት ዲዛይን እና ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር

10. ኢዛና ማዕድን ልማት ኃ/የተ/የግ/ማህበር

11. ቬሎሲቲ አፖራልዝ ካምፓኒስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

12. መሰቦ ቢውልዲንግ ማቴሪያል ፕሮዳክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር

13. ሳባ ዳይሜንሺናል ስቶን ኃ/የተ/የግ/ማህበር

14. መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ

15. ሼባ ታነሪ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

16. ኤ.ፒ ኤፍ

17. ሜጋ ኔት ኮርፖሬሽን

18. እክስፕረስ ትራንዚት ሰርቪስ

19. ደሳለኝ ካትሪናሪ

20. ሼባ ታነሪ ፋክተሪ አክሲዮን ማህበር

21. ህይወት አግሪካልቸር መካናይዜሽን

22. ህይወት እርሻ ሜካናይዜሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር

23. አልመዳ ጋርመንት ፋክተሪ

24. መሶቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ

25. ደደቢት ብድርና ቁጠባ አክሲዮን ማህበር

26. አዲስ ፋርማሲቲካልስ ፕሮዳክሽን

27. ትግራይ ዴቨሎፕመንት ኃ/የተ/የግ/ማህበር

28. ስታር ፓርማሲቲካልስ ኢፖርተርስ

29. ሳባ እምነበረድ አክሲዮን ማህበር

30. አድዋ ፍሎር ፋክተሪ

31. ትካል እግሪ ምትካል/ ትግራይ/ ት.እ.ም.ት/

32. ብሩህ ተስፋ ፕላስቲክ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

33. ደሳለኝ የእንስሳ መድኃኒት አስመጪና አከፋፋይ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

34. ማይጨው ፓርትክል ቦርድ ፋክተሪ

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ  

Filed Under: Left Column, News Tagged With: effort, operation dismantle tplf, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule