• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

34 የወንበዴው ትህነግ የፋይናንስ ተቋማት ታገዱ

November 17, 2020 03:25 am by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ወንበዴው ህወሃት/ትህነግ አገር ለማፍረስ ዓላማ ሲጠቀምባቸው የነበሩት 34 የፋይናንስ ተቋቱን ማገዱን ይፋ አድርጓል።

እንደ ኢቲቪ ዘገባ ከታገዱት የበረኻ ወንበዴዎቹ ድርጅቶች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፤

ሜጋ ማተሚያ፣

ሱር ኮንስትራክሽን፣

ጉና የንግድ ሥራዎች፣

ኢፈርት ኤሌክትሪካል ቢዝነስ፣

ትራንስ ኢትዮጵያ፣

መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ፣

ሠላም የህዝብ ማመላለሻ ማህበር፣

ኢፈርት ኃ/የተ/የግ ማህበር እገዳው ከተላለፈባቸው መካከል ናቸው።

ጎልጉልን ጨምሮ የተለያዩ የሚዲያ አውታሮች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ ወዘተ ለትህነግ የፋይናንስ ምንጭ የሆነው ኤፈርት ወደ ሕዝብ ሃብትነት እንዲመለስ ሲወተውቱ መቆየታቸው ይታወሳል።

ስብሃት ነጋና ቤተሰቡ የተቆጣጠረው ኤፈርት ግብር የማይከፍል፣ የአገር ሃብት ወደፈለገው ፈሰስ የሚያደርግ፣ ኦዲት የማይደረግ፣ በኃላፊነት የማይጠየቅ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ሃብት በመዝረፍ የተቋቋመውን ድርጅት ስብሃት ነጋ ራሴና ጥቂቶች ሆነን ገንዘባችን አዋጥተን የመሠረትነው በማለት በተደጋጋሚ ሲናገር ተደምጧል።

በወንበዴዎቹ ላይ በተከፈተው ሕግን የማስከበር እርምጃ ሱር ኮንስትራክሽን በርካታ ምሽጎችን በመሥራት ለትህነግ የላቀ አገልግሎት ሲሰጥ እንደነበር የሚታወቅ ነው።

ተጨማሪ መረጃ

ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ በፌስቡክ ገጹ ያወጣው መረጃ እንዲህ ይነበባል፤

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የዘር ተኮር ጥቃት እና የሽብር ድርጊት እንዲፈጸም የገንዘብ ድጋፍ በማቅረብ፣ ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ ከሚንቀሳቀሰው የትህነት/ ህወሃት ሀይል ጋር ግንኙነት በመፍጠር፤ በመመሳጠር እንዲሁም የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ የተሳተፉ ስለመሆናቸው እና በግብር ስወራ እና የሙስና ወንጀል ድርጊቶች ውስጥ ስለመሳተፋቸው ምርመራ ለመጀመር የሚያበቃ በቂ ማስረጃ የተገኘባቸውን ከታች ስማቸው የተጠቀሱትን ድርጅቶች የሚንቀሳቀሱ እና የማይንቀሳቀሱ ንብረቶችን በባንክ ያለቸውን ገንዘብ ጨምሮ ከህዳር 07 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ እንዲታገዱ አድርጓል።

ዕግዱ አስፈላጊ የሆነበት ምክንያት ድርጅቶቹ ሀብታቸውን ለማሸሽ ጥረት በማድረግ ላይ እንደሆኑ በቂ ማስረጃ የቀረበ በመሆኑ ንበረቶቹ ሳይሸሹ ተገቢውን ቁጥጥር በማድረግ ውሳኔ እስኪሰጥባቸው ማቆየት ተገቢ መሆኑ ስለታመነበት ነው።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ በወንጀል የተገኘ ሀብት ማስመለስ ዳይሬክቶሬት ጄኔራል የመመርመር እና ሀብትን የማስመለስ ስራውን እስኪያጠናቅቅ ድረስ የታገዱት ንብረቶች እንዳይጎዱ እና እንዳይባክኑ ጠብቆ የሚያቆይ የንብረት አስተዳዳሪ የሚሾም ሲሆን አስተዳዳሪው ስራውን ተቀብሎ ማስተዳደር እስኪጀምር ድረስ የድርጅቶቹ አስተዳዳሪዎች ንበረቱን በሚገባ የመጠበቅ ኃላፊነት አለባቸው።

በቀጣይ የምርመራ እና ክስ ሂደቱን ተከታትለን ለህዝቡ የምናሳውቅ ሆኖ የታገዱት ድርጅቶች ከዚህ በታች ስማቸው የተዘረዘሩት መሆናቸውን እንገልጻለን።

1. ሱር ኮንስትራክሽን

2. ጉና የንግድ ስራዎች ኃ/የተ/የግ/ማህበር

3. ትራንስ ኢትዮጵያ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

4. መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

5. ሰላም የህዝብ ማመላለሻ አክሲዮን ማህበር

6. ሜጋ ማተሚያ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

7. ኤፈርት ኃ/የተ/የግ/ማህበር

8. ኤፈርት ኤሌክትሪካል ቢዝነስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

9. ኤፈርት ዲዛይን እና ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር

10. ኢዛና ማዕድን ልማት ኃ/የተ/የግ/ማህበር

11. ቬሎሲቲ አፖራልዝ ካምፓኒስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

12. መሰቦ ቢውልዲንግ ማቴሪያል ፕሮዳክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር

13. ሳባ ዳይሜንሺናል ስቶን ኃ/የተ/የግ/ማህበር

14. መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ

15. ሼባ ታነሪ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

16. ኤ.ፒ ኤፍ

17. ሜጋ ኔት ኮርፖሬሽን

18. እክስፕረስ ትራንዚት ሰርቪስ

19. ደሳለኝ ካትሪናሪ

20. ሼባ ታነሪ ፋክተሪ አክሲዮን ማህበር

21. ህይወት አግሪካልቸር መካናይዜሽን

22. ህይወት እርሻ ሜካናይዜሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር

23. አልመዳ ጋርመንት ፋክተሪ

24. መሶቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ

25. ደደቢት ብድርና ቁጠባ አክሲዮን ማህበር

26. አዲስ ፋርማሲቲካልስ ፕሮዳክሽን

27. ትግራይ ዴቨሎፕመንት ኃ/የተ/የግ/ማህበር

28. ስታር ፓርማሲቲካልስ ኢፖርተርስ

29. ሳባ እምነበረድ አክሲዮን ማህበር

30. አድዋ ፍሎር ፋክተሪ

31. ትካል እግሪ ምትካል/ ትግራይ/ ት.እ.ም.ት/

32. ብሩህ ተስፋ ፕላስቲክ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

33. ደሳለኝ የእንስሳ መድኃኒት አስመጪና አከፋፋይ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

34. ማይጨው ፓርትክል ቦርድ ፋክተሪ

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ  

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Left Column, News Tagged With: effort, operation dismantle tplf, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule