• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የትግራይ ተወላጅ የፖሊስ አባላት አፈሙዝ ወደ እኛ በማዞር የፈጸሙብን ክህደት በጣም አሳዝኖናል”

November 17, 2020 02:41 am by Editor Leave a Comment

በትግራይ ክልል መቀሌ ሀራ ገበያ ዓዲ ጉደም ምድር ባቡር ፕሮጀክት በሚጠብቁት ላይ ከተፈጸመ ጥቃት የተረፉት ሁለት የፌደራል ፖሊስ አባላት አዲስ አበባ ከተማ ገብተዋል።

የህዝብና መንግስት መሰረተ ልማቶችን በመጠበቅ ከ10 ዓመታት በላይ መቆየታቸውን የገለጸው ዋና ሳጅን ድረስ ስንሻው የተለመደዉን መደበኛ የጥበቃ ስራችን እያከናወን በነበርንበት ወቅት በፕሮጀክቱ ባሉ ሳይቶች ላይ የነበሩ የስራ ባልደረቦቻችንን ትጥቅ በማስፈታት፣ አፍነውና እጃቸውን በካቴና አስረው ወደ መቀሌ ሲወስዷቸው እጃችንን ከምንሰጥ ብለን ወደ ጫካ በመግባት ለሚተኮስብን ተኩስ ምላሽ በመስጠት ለማምለጥ ችለናል ብለዋል።

እኛ ለአንድ ብሔር የቆምን ሳይሆን ከሁሉም የኢትዮጵያ ሕዝብ የተውጣጣንና ሀገራችን ኢትዮጵያ በአንድነት ስንጠብቅ የኖርን በመሆኑ እንደዚህ አይነት የሀገር ክህደት ይፈጸምብናል ብለን አልጠበቅንም ነበር በማለት ገልጸዋል።

የታፈኑ አባሎቻችንን ለማስለቀቅ ብንሞክርም ከአቅማችን በላይ በመሆናቸውና እኛንም ለማስቀረት ከፍተኛ የሆነ ተኩስ ስለ ከፈቱብን ለጽንፈኛው ቡደኑ እጅ ከምንሰጥ በማለት ለሶስት ቀናት የሚበላና የሚጠጣ ባልነበረበት በበረሃ ጫካ ለጫካ እየተጓዘን አፋር ክልል ስንደርስ አባላ የሚባል አካባቢ የክልሉ ህዝብ ተቀብሎን ወደ መስመር አወጣን ሲሉ ተናግረዋል።

የህወሓት ጽንፈኛ ቡድኑ በእኛ በፌደራል ፖሊስ አባላትና በሀገር መከላከያ ሰራዊት የፈጸመው አረመናዊ ድርጊት በጣም አሳዝኖናል፣ በተለይ ከ10 ዓመታት በላይ አብሮን የሰሩና የኖሩ የትግራይ ተወላጅ የፖሊስ አባላት ወደ ክልሉ ልዩ ሀይል በመቀላቀል አፈሙዝ ወደ እኛ በማዞር የፈጸሙብን ክህደት በጣም አሳዝኖናል፣ አስከፍቶናልም ብለዋል።

ከዚህ ቀደም አባት አርበኞች ከፍተኛ መስዋትነት ከፍለው ኢትዮጵያን እንዳስረከቡን ሁሉ ዛሬም በርካታ የሀገር ተቆርቋሪ የሆኑ ጓዶች ስላሉን ሀገራችን ለማዳን እየተከናወኑ ያሉ የህግ ማስከበር ስራዎች ስኬታማ እንዲሆኑ እስከ መጨረሻ ከህዝብ ጋር በመቆም ለዚህ አስነዋሪ ድርጊት የተሰለፉትን የህወሓት ፅንፈኛ ቡድን ለህግ ለማቅረብ ለሚደረገው ርብርብ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

ሌላኛዉ የሰሜን ዲቪዥን፣ ሶስት፣ ሻለቃ 4፣ ሻምበል 1 አባል ኮንስታብል ድረስ ንጉሴ እኛ ሰላም ነው ብለን በተቀመጥንበትና ባላሰብነው ሰዓት የክልሉ ልዩ ሃይልና ሚሊሻ ተደራጅተው በመምጣት አንድ ዳቦ ለሁለት በመካፈል አብረውን ሲበሉ ከነበሩ ከትግራይ ተወላጅ የስራ ባልደረቦቻችን ጋር በመሆን ጥቃት ቢፈጽሙብንም የአፋር ህዝብ ላደረገልን አቀባበልና ድጋፍ ልባዊ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ብለዋል።

እኛ የትግራይ ህዝብን ከወንጀል በመከላከልና በክልሉ የሚገኙ መሰረተ ልማቶችን በመጠበቅ ብቻ ሳይሆን በሁሉም ማህበራዊ እንቅስቃሴ ስናግዝና ስንተባበር ነው የቆየነው፣ የትግራይ ህዝብ ይህንን ጽንፈኛ ቡድን በማጋለጥ ነጻነቱን ሊያረጋግጥ ይገባልም ብሏል። (ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ፌስቡክ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule