• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የትግራይ ተወላጅ የፖሊስ አባላት አፈሙዝ ወደ እኛ በማዞር የፈጸሙብን ክህደት በጣም አሳዝኖናል”

November 17, 2020 02:41 am by Editor Leave a Comment

በትግራይ ክልል መቀሌ ሀራ ገበያ ዓዲ ጉደም ምድር ባቡር ፕሮጀክት በሚጠብቁት ላይ ከተፈጸመ ጥቃት የተረፉት ሁለት የፌደራል ፖሊስ አባላት አዲስ አበባ ከተማ ገብተዋል።

የህዝብና መንግስት መሰረተ ልማቶችን በመጠበቅ ከ10 ዓመታት በላይ መቆየታቸውን የገለጸው ዋና ሳጅን ድረስ ስንሻው የተለመደዉን መደበኛ የጥበቃ ስራችን እያከናወን በነበርንበት ወቅት በፕሮጀክቱ ባሉ ሳይቶች ላይ የነበሩ የስራ ባልደረቦቻችንን ትጥቅ በማስፈታት፣ አፍነውና እጃቸውን በካቴና አስረው ወደ መቀሌ ሲወስዷቸው እጃችንን ከምንሰጥ ብለን ወደ ጫካ በመግባት ለሚተኮስብን ተኩስ ምላሽ በመስጠት ለማምለጥ ችለናል ብለዋል።

እኛ ለአንድ ብሔር የቆምን ሳይሆን ከሁሉም የኢትዮጵያ ሕዝብ የተውጣጣንና ሀገራችን ኢትዮጵያ በአንድነት ስንጠብቅ የኖርን በመሆኑ እንደዚህ አይነት የሀገር ክህደት ይፈጸምብናል ብለን አልጠበቅንም ነበር በማለት ገልጸዋል።

የታፈኑ አባሎቻችንን ለማስለቀቅ ብንሞክርም ከአቅማችን በላይ በመሆናቸውና እኛንም ለማስቀረት ከፍተኛ የሆነ ተኩስ ስለ ከፈቱብን ለጽንፈኛው ቡደኑ እጅ ከምንሰጥ በማለት ለሶስት ቀናት የሚበላና የሚጠጣ ባልነበረበት በበረሃ ጫካ ለጫካ እየተጓዘን አፋር ክልል ስንደርስ አባላ የሚባል አካባቢ የክልሉ ህዝብ ተቀብሎን ወደ መስመር አወጣን ሲሉ ተናግረዋል።

የህወሓት ጽንፈኛ ቡድኑ በእኛ በፌደራል ፖሊስ አባላትና በሀገር መከላከያ ሰራዊት የፈጸመው አረመናዊ ድርጊት በጣም አሳዝኖናል፣ በተለይ ከ10 ዓመታት በላይ አብሮን የሰሩና የኖሩ የትግራይ ተወላጅ የፖሊስ አባላት ወደ ክልሉ ልዩ ሀይል በመቀላቀል አፈሙዝ ወደ እኛ በማዞር የፈጸሙብን ክህደት በጣም አሳዝኖናል፣ አስከፍቶናልም ብለዋል።

ከዚህ ቀደም አባት አርበኞች ከፍተኛ መስዋትነት ከፍለው ኢትዮጵያን እንዳስረከቡን ሁሉ ዛሬም በርካታ የሀገር ተቆርቋሪ የሆኑ ጓዶች ስላሉን ሀገራችን ለማዳን እየተከናወኑ ያሉ የህግ ማስከበር ስራዎች ስኬታማ እንዲሆኑ እስከ መጨረሻ ከህዝብ ጋር በመቆም ለዚህ አስነዋሪ ድርጊት የተሰለፉትን የህወሓት ፅንፈኛ ቡድን ለህግ ለማቅረብ ለሚደረገው ርብርብ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

ሌላኛዉ የሰሜን ዲቪዥን፣ ሶስት፣ ሻለቃ 4፣ ሻምበል 1 አባል ኮንስታብል ድረስ ንጉሴ እኛ ሰላም ነው ብለን በተቀመጥንበትና ባላሰብነው ሰዓት የክልሉ ልዩ ሃይልና ሚሊሻ ተደራጅተው በመምጣት አንድ ዳቦ ለሁለት በመካፈል አብረውን ሲበሉ ከነበሩ ከትግራይ ተወላጅ የስራ ባልደረቦቻችን ጋር በመሆን ጥቃት ቢፈጽሙብንም የአፋር ህዝብ ላደረገልን አቀባበልና ድጋፍ ልባዊ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ብለዋል።

እኛ የትግራይ ህዝብን ከወንጀል በመከላከልና በክልሉ የሚገኙ መሰረተ ልማቶችን በመጠበቅ ብቻ ሳይሆን በሁሉም ማህበራዊ እንቅስቃሴ ስናግዝና ስንተባበር ነው የቆየነው፣ የትግራይ ህዝብ ይህንን ጽንፈኛ ቡድን በማጋለጥ ነጻነቱን ሊያረጋግጥ ይገባልም ብሏል። (ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ፌስቡክ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ፍፁም ብርሃኔና ታምራት የማነ በቁጥጥር ሥር ዋሉ April 16, 2021 10:06 am
  • “ለአንድ ፓርቲ የማደላ ከሆነ ሄጄ እዚያው ፓርቲ እገባለሁ” ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ April 16, 2021 08:45 am
  • “ተዋግተን አይደለም ስንተኛ ብንውል እንኳን መቀሌና አዲስ አበባ አይገቡም” ጄኔራል ባጫ April 14, 2021 09:06 am
  • የስኳር ፋብሪካዎች ተሽጠው ዕዳቸውን እንዲከፍሉ ተወሰነ April 14, 2021 08:53 am
  • “ኤርትራዊ ነን” በማለት የመኖሪያ ፈቃድ ሲቀበሉ የኖሩ የትግራይ ሰዎችን መለየት ተጀመረ April 1, 2021 02:01 am
  • ምርጫ ቦርድ የኦነግን ጥያቄ ውድቅ አደረገ April 1, 2021 01:15 am
  • “እርግጠኛ ሆኜ የምነግራችሁ መንግሥት ኮሮጆ አይሰርቅም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ April 1, 2021 01:09 am
  • መንግሥት ካልደረሰልን አሁንም ግድያ ይኖራል – ነዋሪዎች April 1, 2021 01:04 am
  • በትግራይ ሊዘረፍ የነበረ የእርዳታ እህል ተያዘ April 1, 2021 12:39 am
  • “በኢትዮጵያ ክብርና ጥቅም ከመጣችሁ አንገቴ ይቀላል እንጂ አልደራደርም” March 24, 2021 01:22 am
  • “ከዚህ በኋላ ህወሓት ማለት በነፋስ የተበተነ ዱቄት ነው” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ March 23, 2021 11:28 pm
  • እነ ስብሃት ነጋ ጥያቄያቸው ውድቅ ሆነ March 23, 2021 10:23 pm
  • በርግጥ ኢትዮጵያ ዝናብ አዝንባለች? March 23, 2021 10:15 pm
  • አሜሪካ በሴናተሯ አማካይነት “ለቅሶ” ደረሰች March 21, 2021 08:57 pm
  • ቪኦኤ በወለጋ ሆሮ ጉድሩ ለተጨፈጨፉ ኦነግ ሸኔን ከደሙ ንጹህ አደረገ March 19, 2021 04:32 pm
  • ባልደራስና የአብን የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ March 18, 2021 01:56 pm
  • ኤርሚያስ ለገሰ “የወያኔ የፕሮፖጋንዳ ሰራተኛ እያለ የለመደው የቁጥር ጫወታ አለቀቀውም” March 17, 2021 09:54 pm
  • በትግራይ ሰብዓዊ ድጋፍ በተቀላጠፈ ሁኔታ እየተካሄደ ነው – የተመድ የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት March 17, 2021 04:54 am
  • ምርጫ ቦርድ ከፈቀደለት ኦነግ በምርጫው እንደሚወዳደር አስታወቀ March 17, 2021 04:30 am
  • በዓለምአቀፍ ሚዲያ ዘጋቢዎች ላይ እርምጃ ሊወሰድ ነው March 15, 2021 11:25 am
  • በሲዳማ/ሀዋሳ 128 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጥ፤ 2 መትረየስ ከ8,129 ጥይት ጋር ተያዘ March 15, 2021 10:13 am
  • የአክሱም ጅምላ ጭፍጨፋ ተብሎ የተሰራጨው ፎቶ የሐሰት ሆነ March 15, 2021 09:26 am
  • በትግራይ ትምህርት ቤቶች በቅርቡ ሥራ ይጀምራሉ March 15, 2021 09:04 am
  • በማይካድራ የጅምላ መቃብር ተገኘ፤ በህወሓት የተገደሉት ቁጥር ከ1300 እንደሚበልጥ ተነገረ March 15, 2021 08:54 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule