• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የማይካድራ ዕልቂት

November 12, 2020 04:03 am by Editor 1 Comment

በምዕራባዊ ትግራይ ሁመራ አቅራቢያ «ማይካድራ» በተባለው አካባቢ የትግራይ ልዩ ኃይል ባልታጠቁ የአማራ ተወላጆች ላይ በሌሊት አሰቃቂ ግድያ መፈፀሙን ከሞት ያመለጠ የዐይን እማኝ ገለፀ። ጥቃቱ የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው ሲል ደግሞ የአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ዐስታውቋል።

በምዕራባዊ ትግራይ ሁመራ አቅራቢያ «ማይካድራ» በተባለው አካባቢ የትግራይ ልዩ ኃይል ባልታጠቁ የአማራ ተወላጆች ላይ በሌሊት አሰቃቂ ግድያ መፈፀሙን ከሞት ያመለጠ የዐይን እማኝ ገለፀ። ጥቃቱ የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው ሲል ደግሞ የአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ዐስታውቋል። ድርጊቱ የተጀመረውን ሕግ የማስከበር ሂደት ህወሓት ወደ የእርስ በእርስ ጦርነት እንዲቀየር የዘየደው መላ ነውም ብሎታል። አንዳንድ የአማራ ክልል ነዋሪዎች የህወሓት የተስፋ መቊረጥ ስሜት ነው፤ ኅብረተሰቡ ህወሓት በዘየደው የብቀላ ሂደት እንዳይገባ አሳስበዋል። 

የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት ሰሞኑን ሁመራን ከተቆጣጠረ በኋላ ግስጋሴውን ወደ ማይካድራ ባደረገበት ወቅት ህዳር 1 ቀን፣ 2013 ዓ.ም አነጋጉ ላይ የትግራይ ልዩ ኃይል አካባቢውን በኃይል ተገፍቶ ለአገር መከላከያ ሰራዊት ከመልቀቁ በፊት በአካባቢው የነበሩ የአማራ ተወላጅ በሆኑ ነዋሪዎችንና የቀን ሠራተኞችን በእለቱ ከሌሊቱ 9 ሰዓት ጀምሮ በየቤታቸው እየገባ በግፍ መጨፍጨፉን ከጥቃቱ አምልጦ አሁን አብደራፊ በተባለ ቦታ የሚገኝ የዓይን እማኝ ለዶይቼ ቬለ (DW) በስልክ ተናግሯል፡፡ 

ጥቃቱን ተከትሎ «እየሞትንም ቢሆን እናሸንፋለ» በሚል መግለጫ ያወጣው የአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ እንዳለው «በማይካድራ የተፈፀመው ጭፍጨፋ አማራን መሰረት ያደረገ የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው» ብሎታል፡፡ 

ድርጊቱ አሁን በትግራይ ክልል ሕግ ለማስከበር የሚደረገውን ትግል የእርስ በርስ ለማስመሰል ያደረገው ስልት ነው ሲልም ከስሷል፡፡ ፓርቲው ለአማራ ክልል ህዝብ ባስተላለፈው መልዕክት «…በተለመደው አስተዋይ ባህሪህ ምስኪኑ የትግራይን ህዝብ እንደ ትላንቱ ሁሉ ዛሬም ከየትኛውም ጥቃት ጥላ ከለላ ሆነህ ይህን ጊዜ እንድታሳልፈው ይሁን» ብሏል፡፡ 

አንድ የደብረማርቆስ ነዋሪ እንዳሉት ህወሓት ድርጊቱን የፈፀመው በአማራ ክልል በሚኖሩ የትግራይ ወንድሞችና እህቶች ላይ በቀል እርምጃ እንዲወሰድ ያዘጋጀው «ወጥመድ» እንደሆነና የእርስበርስ ግጭት ለመፍጠር እንደሆነ አብራርተዋል፡፡ 

የእንጅባራ ከተማ ነዋሪውም ቢሆኑ ጥቃቱ የህግ ማስከበሩን ተግባር ወደ የእርስ በርስ ግጭት ለመግፋት የተደረገ ሴራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡  የደሴ ከተማ ነዋሪ እንዳሉት ደግሞ ህብረተሰቡ ራሱን ከስሜት ነፃ አድርጎ ህግ የማስከበሩን ሂደት በጥንቃቄ መከታተል አንዳለበት ጠቁመው ከበቀልና ከጥላቻ እንዲቆጠብ ጠይቀዋል፡፡ 

ከወንበዴዎቹ ጥቂቶቹ – አስመላሽ፣ ስብሃት እና አዲስአለም

የደቡብ ጎንደር ዞን ብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ጥላሁን ደጀኔ በስልክ ለዶይቼ ቬለ እንደተናገሩት ህብረተሰቡን ወደ ብስጭት በማስገባት አንዱ በሌላው ላይ እንዲነሳ ለማድረግ ነው ብለዋል፡፡ 

«የአማራና የትግራ ህዝብ ታሪክ የሰራ የተዋለደና ተመሳሳይ ስነልቦና ያለው ህብረተሰብ ነው» ያሉት አቶ ጥላሁን «ትግሉ ህገወጥ ቡድን» ካሉት አካል ጋር እንደሆነ አሰተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ በስፍራው የሚገኘው የአማራ ቴሌቪዝን ዘጋቢ ከ100 በላይ የተገደሉ ሰዎችን አስከሬን መመልከቱን ለቴሌቪዥን ጣቢያው ዘግቧል፡፡ (ዶይቼ ቬለ (DW) 

የትህነግ ሰው በላ ቡድን በማይካድራ በንጹኀን ሰዎች ላይ ጭፍጨፋ ፈጽሟል።

የአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት ከሃዲው የትህነግ ቡድን ጦርነት ባወጀባቸው አካባቢዎች አቅንቶ ህግ የማስከበሩን እርምጃ ተመልክቷል።

ጦርነቱ ህገመንግስታዊ ስርዓቱን አደጋ ላይ የጣለ እና የሃገር ክህደት በፈፀመው የትህነግ ቡድን ላይ ያነጣጠረ እንደሆነም ከትህነግ ቡድን ነፃ የወጣው ማህበረሰብ አረጋግጧል።

ነገር ግን ማይካድራ በመከላከያ ሰራዊት፣ በአማራ ልዩ ሀይልና ሚሊሻ በቁጥጥ ስር ከመዋሏ በፊት ጥቅምት 30/2013 ዓም ሌሊት በማይካድራ ህገወጥ ቡድኑ የፈፀመው የዘር ማጥፋት ወንጀል የቡድኑን በአማራ ህዝብ ላይ የለየለትን ጠላትነትና የድርጊቱን አስከፊነት ያሳየ ነበር።

በነበረው የተጠናከረ ጥቃት ሌሎች ይዞታወችን ለቆ ወደ ማይካድራ የገባው የትህነግ ጦር ይደርስበት የነበረውን ከፍተኛ ጥቃት ባለመቋቋሙ መሽጎበት የነበረውን የማይካድራ ይዞታ እንዲለቅም ተገዷል። ማይካድራም ከህገወጥ ቡድኑ ነፃ ሆናለች።

ይሁንና ቡድኑ ከዚህ ቀደም በተለያዩ የሃገሪቱ አካባቢዎች ይፈፅመው የነበረውን የተቀነባበር የሴራ ግጭትና የዜጎች ጭፍጨፋ በማይካደራም ፈፅሞታል። ሰው በላነቱን በአማራ እና በኢትዮጵያዊያን ላይ በተግባር አሳይቷል።

የትህነግ ዘራፊ ቡድን ዓላማ ማስፈጸሚያ የሆኑት ልዩ ሃይል እና ሳምሪ የተባለው ገዳይ ቡድን በማይካድራ ከተማ የሚገኙ ንጹኀን ሰላማዊ ዜጎችን በጂምላ ጨፍጭፏል።

አብመድ በቦታው በመገኘትም በሰው በላው  ትህነግ በርካታ ንጹኀን አማራዎች የጥቃቱ ሰለባ መሆናቸውን አረጋግጧል። በጥቃቱ  የሌሎች ብሔር ተወላጆችም ሰለባ እንደሆኑ የአካባቢው ነዋሪዎች  ተናግረዋል። (አብመድ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Religion, Right Column Tagged With: operation dismantle tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Gi Haile says

    November 15, 2020 12:23 am at 12:23 am

    የሕወኣት የወንጀል ጣራ በየትኛውም ኣለሞ ከተደረገው በዘመናት መካከል ከተፈፀመው ወንጀል ይበልጣል። ሂትለር፣ሞሱሊንና ስታሊን በጣም ኣነሳ ነው።
    ሕወኣት የተመረቁቱ ከኣለም አቀፍ የወንጀል ኮሌጅ (ካለ ) ማለት ወወይ ከሲሺሊያ ወይ ከኮሎምቢያ መሆን ኣለበት።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule