• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የማይካድራ ዕልቂት

November 12, 2020 04:03 am by Editor 1 Comment

በምዕራባዊ ትግራይ ሁመራ አቅራቢያ «ማይካድራ» በተባለው አካባቢ የትግራይ ልዩ ኃይል ባልታጠቁ የአማራ ተወላጆች ላይ በሌሊት አሰቃቂ ግድያ መፈፀሙን ከሞት ያመለጠ የዐይን እማኝ ገለፀ። ጥቃቱ የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው ሲል ደግሞ የአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ዐስታውቋል።

በምዕራባዊ ትግራይ ሁመራ አቅራቢያ «ማይካድራ» በተባለው አካባቢ የትግራይ ልዩ ኃይል ባልታጠቁ የአማራ ተወላጆች ላይ በሌሊት አሰቃቂ ግድያ መፈፀሙን ከሞት ያመለጠ የዐይን እማኝ ገለፀ። ጥቃቱ የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው ሲል ደግሞ የአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ዐስታውቋል። ድርጊቱ የተጀመረውን ሕግ የማስከበር ሂደት ህወሓት ወደ የእርስ በእርስ ጦርነት እንዲቀየር የዘየደው መላ ነውም ብሎታል። አንዳንድ የአማራ ክልል ነዋሪዎች የህወሓት የተስፋ መቊረጥ ስሜት ነው፤ ኅብረተሰቡ ህወሓት በዘየደው የብቀላ ሂደት እንዳይገባ አሳስበዋል። 

የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት ሰሞኑን ሁመራን ከተቆጣጠረ በኋላ ግስጋሴውን ወደ ማይካድራ ባደረገበት ወቅት ህዳር 1 ቀን፣ 2013 ዓ.ም አነጋጉ ላይ የትግራይ ልዩ ኃይል አካባቢውን በኃይል ተገፍቶ ለአገር መከላከያ ሰራዊት ከመልቀቁ በፊት በአካባቢው የነበሩ የአማራ ተወላጅ በሆኑ ነዋሪዎችንና የቀን ሠራተኞችን በእለቱ ከሌሊቱ 9 ሰዓት ጀምሮ በየቤታቸው እየገባ በግፍ መጨፍጨፉን ከጥቃቱ አምልጦ አሁን አብደራፊ በተባለ ቦታ የሚገኝ የዓይን እማኝ ለዶይቼ ቬለ (DW) በስልክ ተናግሯል፡፡ 

ጥቃቱን ተከትሎ «እየሞትንም ቢሆን እናሸንፋለ» በሚል መግለጫ ያወጣው የአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ እንዳለው «በማይካድራ የተፈፀመው ጭፍጨፋ አማራን መሰረት ያደረገ የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው» ብሎታል፡፡ 

ድርጊቱ አሁን በትግራይ ክልል ሕግ ለማስከበር የሚደረገውን ትግል የእርስ በርስ ለማስመሰል ያደረገው ስልት ነው ሲልም ከስሷል፡፡ ፓርቲው ለአማራ ክልል ህዝብ ባስተላለፈው መልዕክት «…በተለመደው አስተዋይ ባህሪህ ምስኪኑ የትግራይን ህዝብ እንደ ትላንቱ ሁሉ ዛሬም ከየትኛውም ጥቃት ጥላ ከለላ ሆነህ ይህን ጊዜ እንድታሳልፈው ይሁን» ብሏል፡፡ 

አንድ የደብረማርቆስ ነዋሪ እንዳሉት ህወሓት ድርጊቱን የፈፀመው በአማራ ክልል በሚኖሩ የትግራይ ወንድሞችና እህቶች ላይ በቀል እርምጃ እንዲወሰድ ያዘጋጀው «ወጥመድ» እንደሆነና የእርስበርስ ግጭት ለመፍጠር እንደሆነ አብራርተዋል፡፡ 

የእንጅባራ ከተማ ነዋሪውም ቢሆኑ ጥቃቱ የህግ ማስከበሩን ተግባር ወደ የእርስ በርስ ግጭት ለመግፋት የተደረገ ሴራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡  የደሴ ከተማ ነዋሪ እንዳሉት ደግሞ ህብረተሰቡ ራሱን ከስሜት ነፃ አድርጎ ህግ የማስከበሩን ሂደት በጥንቃቄ መከታተል አንዳለበት ጠቁመው ከበቀልና ከጥላቻ እንዲቆጠብ ጠይቀዋል፡፡ 

ከወንበዴዎቹ ጥቂቶቹ – አስመላሽ፣ ስብሃት እና አዲስአለም

የደቡብ ጎንደር ዞን ብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ጥላሁን ደጀኔ በስልክ ለዶይቼ ቬለ እንደተናገሩት ህብረተሰቡን ወደ ብስጭት በማስገባት አንዱ በሌላው ላይ እንዲነሳ ለማድረግ ነው ብለዋል፡፡ 

«የአማራና የትግራ ህዝብ ታሪክ የሰራ የተዋለደና ተመሳሳይ ስነልቦና ያለው ህብረተሰብ ነው» ያሉት አቶ ጥላሁን «ትግሉ ህገወጥ ቡድን» ካሉት አካል ጋር እንደሆነ አሰተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ በስፍራው የሚገኘው የአማራ ቴሌቪዝን ዘጋቢ ከ100 በላይ የተገደሉ ሰዎችን አስከሬን መመልከቱን ለቴሌቪዥን ጣቢያው ዘግቧል፡፡ (ዶይቼ ቬለ (DW) 

የትህነግ ሰው በላ ቡድን በማይካድራ በንጹኀን ሰዎች ላይ ጭፍጨፋ ፈጽሟል።

የአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት ከሃዲው የትህነግ ቡድን ጦርነት ባወጀባቸው አካባቢዎች አቅንቶ ህግ የማስከበሩን እርምጃ ተመልክቷል።

ጦርነቱ ህገመንግስታዊ ስርዓቱን አደጋ ላይ የጣለ እና የሃገር ክህደት በፈፀመው የትህነግ ቡድን ላይ ያነጣጠረ እንደሆነም ከትህነግ ቡድን ነፃ የወጣው ማህበረሰብ አረጋግጧል።

ነገር ግን ማይካድራ በመከላከያ ሰራዊት፣ በአማራ ልዩ ሀይልና ሚሊሻ በቁጥጥ ስር ከመዋሏ በፊት ጥቅምት 30/2013 ዓም ሌሊት በማይካድራ ህገወጥ ቡድኑ የፈፀመው የዘር ማጥፋት ወንጀል የቡድኑን በአማራ ህዝብ ላይ የለየለትን ጠላትነትና የድርጊቱን አስከፊነት ያሳየ ነበር።

በነበረው የተጠናከረ ጥቃት ሌሎች ይዞታወችን ለቆ ወደ ማይካድራ የገባው የትህነግ ጦር ይደርስበት የነበረውን ከፍተኛ ጥቃት ባለመቋቋሙ መሽጎበት የነበረውን የማይካድራ ይዞታ እንዲለቅም ተገዷል። ማይካድራም ከህገወጥ ቡድኑ ነፃ ሆናለች።

ይሁንና ቡድኑ ከዚህ ቀደም በተለያዩ የሃገሪቱ አካባቢዎች ይፈፅመው የነበረውን የተቀነባበር የሴራ ግጭትና የዜጎች ጭፍጨፋ በማይካደራም ፈፅሞታል። ሰው በላነቱን በአማራ እና በኢትዮጵያዊያን ላይ በተግባር አሳይቷል።

የትህነግ ዘራፊ ቡድን ዓላማ ማስፈጸሚያ የሆኑት ልዩ ሃይል እና ሳምሪ የተባለው ገዳይ ቡድን በማይካድራ ከተማ የሚገኙ ንጹኀን ሰላማዊ ዜጎችን በጂምላ ጨፍጭፏል።

አብመድ በቦታው በመገኘትም በሰው በላው  ትህነግ በርካታ ንጹኀን አማራዎች የጥቃቱ ሰለባ መሆናቸውን አረጋግጧል። በጥቃቱ  የሌሎች ብሔር ተወላጆችም ሰለባ እንደሆኑ የአካባቢው ነዋሪዎች  ተናግረዋል። (አብመድ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Religion, Right Column Tagged With: operation dismantle tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Gi Haile says

    November 15, 2020 12:23 am at 12:23 am

    የሕወኣት የወንጀል ጣራ በየትኛውም ኣለሞ ከተደረገው በዘመናት መካከል ከተፈፀመው ወንጀል ይበልጣል። ሂትለር፣ሞሱሊንና ስታሊን በጣም ኣነሳ ነው።
    ሕወኣት የተመረቁቱ ከኣለም አቀፍ የወንጀል ኮሌጅ (ካለ ) ማለት ወወይ ከሲሺሊያ ወይ ከኮሎምቢያ መሆን ኣለበት።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule