• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

operation dismantle tplf

ጃዋር “የአንድነት ኃይሎች ከዱኝ”

November 17, 2020 03:36 am by Editor 5 Comments

ጃዋር “የአንድነት ኃይሎች ከዱኝ”

በቅርቡ ጃዋር መሐመድን ማረሚያ ቤት ድረስ ሄደው ከጎበኙ መካከል አንደኛው ከጃዋር አንደበት የሰሙትን ማመን እንዳቃታቸው ይገልጻሉ። ጃዋር ያለፈበትን መንገድ እያሰላ በጸጸት ውስጥ ያለ ይመስላል። በአጭር ጉብኝታቸው “የአንድነት ኃይሎች ከዱኝ” በማለት ቅዝዝ ብሎ የነገራቸው ጠያቂው እሱን ከተሰናበቱ በኋላ ነበር ለጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ሁኔታውን ያጫወቱት። ለተለያዩ ሚዲያዎችና በጃዋር ዙሪያ ለነበሩ እንቅስቃሴዎች እንግዳ ያልሆኑት እኚሁ ሰው ለጎልጉል ዘጋቢ መነሻ ሃሳብ ከሰጡ በኋላ ዘጋቢያችን በርካታ መረጃዎችን አሰባስቦ የሚከተለውን ሪፖርት አዘጋጅቷል። በሪፖርቱ አስቀድሞ የተሰባሰቡና ጊዜ ሲጠብቁ የነበሩ መረጃዎች ተካተዋል። ሪፖርቱ አንባቢያን የራሳቸውን ስሌት እንዲያሰሉና አቅም ያላቸው ይበልጥ ጉዳዩን እንዲያጠኑት የሚያነሳሳ ይሆናል። ጃዋርና “የአንድነት ኃይሎች” የት፣ … [Read more...] about ጃዋር “የአንድነት ኃይሎች ከዱኝ”

Filed Under: Middle Column, Politics Tagged With: eskinder, jawar, jawar massacre, lidetu ayalew, operation dismantle tplf, tplf, yilikal

34 የወንበዴው ትህነግ የፋይናንስ ተቋማት ታገዱ

November 17, 2020 03:25 am by Editor Leave a Comment

34 የወንበዴው ትህነግ የፋይናንስ ተቋማት ታገዱ

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ወንበዴው ህወሃት/ትህነግ አገር ለማፍረስ ዓላማ ሲጠቀምባቸው የነበሩት 34 የፋይናንስ ተቋቱን ማገዱን ይፋ አድርጓል። እንደ ኢቲቪ ዘገባ ከታገዱት የበረኻ ወንበዴዎቹ ድርጅቶች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፤ ሜጋ ማተሚያ፣ ሱር ኮንስትራክሽን፣ ጉና የንግድ ሥራዎች፣ ኢፈርት ኤሌክትሪካል ቢዝነስ፣ ትራንስ ኢትዮጵያ፣ መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ፣ ሠላም የህዝብ ማመላለሻ ማህበር፣ ኢፈርት ኃ/የተ/የግ ማህበር እገዳው ከተላለፈባቸው መካከል ናቸው። ጎልጉልን ጨምሮ የተለያዩ የሚዲያ አውታሮች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ ወዘተ ለትህነግ የፋይናንስ ምንጭ የሆነው ኤፈርት ወደ ሕዝብ ሃብትነት እንዲመለስ ሲወተውቱ መቆየታቸው ይታወሳል። ስብሃት ነጋና ቤተሰቡ የተቆጣጠረው ኤፈርት ግብር … [Read more...] about 34 የወንበዴው ትህነግ የፋይናንስ ተቋማት ታገዱ

Filed Under: Left Column, News Tagged With: effort, operation dismantle tplf, tplf

መጠኑ ያልታወቀ ገንዘብ በበርሜል ወድቆ ተገኘ

November 17, 2020 03:15 am by Editor 1 Comment

መጠኑ ያልታወቀ ገንዘብ በበርሜል ወድቆ ተገኘ

በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ልዩ ስሙ ኢንፎኔት ኮሌጅ አካባቢ አንድ በርሜል ገንዘብ ወድቆ ተገኘ። በዚህ ስፍራ በአንድ በርሜል ተጠቅጥቆ መገኘቱን የኢትዮ ኤፍ ኤም ሪፖርተር በአካል ተገኝቶ አረጋግጧል። የተገኘው ገንዘብ የኢትዮጵያ ብር እና ዶላር ሲሆን ገንዘቡን ማን እንደጣለው ያልተተረጋገጠ ሲሆን የአካባቢው ፖሊስ በመኪና ጭኖ ወደ ፖሊስ ጣቢያ እንደወሰደውም ሪፖርተራችን አረጋግጧል። በተያያዘ ዜና በዚሁ ወረዳ ጣልያን ሰፈር ልዩ ስሙ ጉሊት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ አንድ አዛውንት ቤት ቁጥሩ እስካሁን ያልተረጋገጠ ገንዘብ በማዳበሪያ እና በመዘፍዘፊያ አስቀምጠው ተይዘዋል። አዛውንቷ ለረጅም አመታት በልመና ስራ የሚተዳደሩ ናቸው የተባለ ሲሆን የገንዘቡን መጠን ለማወቅ የአካባቢው ወጣቶች እና ፖሊስ በጋራ ቆጠራ እየተካሄደ መሆኑን ሰምተናል። አዛውንቷ … [Read more...] about መጠኑ ያልታወቀ ገንዘብ በበርሜል ወድቆ ተገኘ

Filed Under: News, Right Column Tagged With: operation dismantle tplf

“የትግራይ ተወላጅ የፖሊስ አባላት አፈሙዝ ወደ እኛ በማዞር የፈጸሙብን ክህደት በጣም አሳዝኖናል”

November 17, 2020 02:41 am by Editor Leave a Comment

“የትግራይ ተወላጅ የፖሊስ አባላት አፈሙዝ ወደ እኛ በማዞር የፈጸሙብን ክህደት በጣም አሳዝኖናል”

በትግራይ ክልል መቀሌ ሀራ ገበያ ዓዲ ጉደም ምድር ባቡር ፕሮጀክት በሚጠብቁት ላይ ከተፈጸመ ጥቃት የተረፉት ሁለት የፌደራል ፖሊስ አባላት አዲስ አበባ ከተማ ገብተዋል። የህዝብና መንግስት መሰረተ ልማቶችን በመጠበቅ ከ10 ዓመታት በላይ መቆየታቸውን የገለጸው ዋና ሳጅን ድረስ ስንሻው የተለመደዉን መደበኛ የጥበቃ ስራችን እያከናወን በነበርንበት ወቅት በፕሮጀክቱ ባሉ ሳይቶች ላይ የነበሩ የስራ ባልደረቦቻችንን ትጥቅ በማስፈታት፣ አፍነውና እጃቸውን በካቴና አስረው ወደ መቀሌ ሲወስዷቸው እጃችንን ከምንሰጥ ብለን ወደ ጫካ በመግባት ለሚተኮስብን ተኩስ ምላሽ በመስጠት ለማምለጥ ችለናል ብለዋል። እኛ ለአንድ ብሔር የቆምን ሳይሆን ከሁሉም የኢትዮጵያ ሕዝብ የተውጣጣንና ሀገራችን ኢትዮጵያ በአንድነት ስንጠብቅ የኖርን በመሆኑ እንደዚህ አይነት የሀገር ክህደት ይፈጸምብናል ብለን አልጠበቅንም … [Read more...] about “የትግራይ ተወላጅ የፖሊስ አባላት አፈሙዝ ወደ እኛ በማዞር የፈጸሙብን ክህደት በጣም አሳዝኖናል”

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: operation dismantle tplf

በርካታ ቁጥር ያለው የህወሓት የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ሥር ዋለ

November 17, 2020 02:00 am by Editor Leave a Comment

በርካታ ቁጥር ያለው የህወሓት የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ሥር ዋለ

ታጣቂው ህወሓት ልዩ ኃይል በሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ በአማራ ልዩ ኃይልና በሚሊሻ አባላት እየተደመሰሰ ይገኛል። በዚህ ታላቅ ጀብድ ሰራዊቱ የህወሓት ስግብግብ ኃይል ለጦርነት እየተጠቀመባቸው የነበሩ ከ230 በላይ ክላሽንኮቭ፣ ከ1 ሺህ በላይ የእጅ ቦምብና ሌሎች ተተኳሽ መሳሪያዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የደቡብ ዕዝ የሰው ሐብት ልማትና የሚዲያ አስተባባሪ ኮሎኔል ደጀኔ ጸጋዬ ተናግረዋል። እየተካሄደ ባለው ህግ የማስከበር ለህልውና ዘመቻ የአማራ ልዩ ኃይልና የሚሊሻ አባላት በተሰጣቸው ቀጣና በጠላት ላይ ከባድ ወታደራዊ ጥቃት በመፈጸምና በመደምስስ ግዳጃቸውን በብቃት እየፈጸሙ መሆኑንም ማመላከታቸውን ፋና ዘግቧል። በሌላ በኩል በጋምቤላ ከልል ዲማ ወረዳ በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 5 ክላሽንኮቭ የጦር መሳሪያና አንድ F1 የእጅ ቦንብ ከስድስት ተጠርጣሪ ጋር መያዙን … [Read more...] about በርካታ ቁጥር ያለው የህወሓት የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ሥር ዋለ

Filed Under: News, Right Column Tagged With: operation dismantle tplf

ህወሃትን ያገለግሉ የነበሩ የግል ጥበቃ ኤጀንሲዎች እንዲታገዱ ተወሰነ!

November 13, 2020 02:02 am by Editor Leave a Comment

ህወሃትን ያገለግሉ የነበሩ የግል ጥበቃ ኤጀንሲዎች እንዲታገዱ ተወሰነ!

በሕገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበሩ ያላቸውን የግል ጥበቃ ኤጀንሲዎች እንዲታገዱ መወሰኑን ፌዴራል ፖሊስ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ የግል ጥበቃ ኤጀንሲዎቹ በቀጠሯቸው የጥበቃ አባላትና ተባባሪዎቻቸው ባንኮችንና የተለያዩ ድርጅቶችን ሲዘርፉ እና ሲያዘርፉ ነበርም ብሏል። በተጨማሪም 'የህወሓትን ተልዕኮ ለመፈፀም የተለያዩ ግለሰቦችን ወደ ኤጀንሲዎቹ አስርገው በማስገባት እና የጦር መሣሪያ በማስታጠቅ በኅብረተሰቡ ሰላማዊ እንቅስቃሴ ላይ ጥቃት ለመፈፀም እያሴሩ ነበር' ሲል አስታውቋል። በዚህም:- 1. ንስር የሰው ሃይል እና የጥበቃ አገ/ሃ/የተ/የግ/ማ 2. አጋር የጥበቃ አገልግሎት ኃ/የተ/የግ/ማ 3. ስብኃቱና ልጆቹ የንብረት አስ/ጥበቃ አገልግሎት ኃ/የተ/የግ/ማ 4. ሰላም ሴኩሪቲ ሶሉሽን ኃ/የተ/የግ/ማ 5. ኃይሌ ተክላይ … [Read more...] about ህወሃትን ያገለግሉ የነበሩ የግል ጥበቃ ኤጀንሲዎች እንዲታገዱ ተወሰነ!

Filed Under: Left Column, News Tagged With: operation dismantle tplf

በወጋገን ባንክ በርካታ የጦር መሠሪያ፤ በሱር ኮንስትራክሽን ደግሞ የሬዲዮ መገናኛ ተገኘ

November 13, 2020 01:51 am by Editor Leave a Comment

በወጋገን ባንክ በርካታ የጦር መሠሪያ፤ በሱር ኮንስትራክሽን ደግሞ የሬዲዮ መገናኛ ተገኘ

በወጋገን ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት ለጥበቃ አገልግሎት ከሚያስፈልገው ውጭ የጦር መሠሪያ ተከማችቶ መገኘቱን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው ለሸገር ኤፍ ኤም ተናግረዋል፡፡ ከተገኙት መሣሪያዎች አንዳንዱ በፀጥታ ኃይሉ እጅ የሌሉ ጭምር መሆናቸውን ነው የገለጹት፡፡ በተያያዘ ዜናም 97 የእጅ ሬድዮ 23 የረጅም እርቀት የትከሻ መገናኛ ሬድዮ ከሱር ኮንስትራክሽን በብርበራ መያዙን ትላንት በተሰጠ መግለጫ ተጠቅሷል፡፡ በከተማው የተያዙ ባለሀብቶችም እንዳሉ ይሰማል ይህስ በምን መስፈርት ነው ሲል ሸገር ላቀረበላቸው ጥያቄ ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው የሕወሓትን ቡድን በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ የደገፉ ባለሀብቶች በማስረጃ ስለመያዛቸው ለጣቢያው ገልጸዋል፡፡ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about በወጋገን ባንክ በርካታ የጦር መሠሪያ፤ በሱር ኮንስትራክሽን ደግሞ የሬዲዮ መገናኛ ተገኘ

Filed Under: News, Right Column Tagged With: operation dismantle tplf

በ96 የህወሃት ወንበዴዎች ላይ የፍርድ ቤት ማዘዣ ወጣባቸው

November 12, 2020 01:50 pm by Editor 1 Comment

በ96 የህወሃት ወንበዴዎች ላይ የፍርድ ቤት ማዘዣ ወጣባቸው

የአገር ክህደት ወንጀል በፈፀሙ የጁንታው ሕወሓት ቡድን ላይ የፍርድ ቤት የመያዣ ትዕዛዝ እንደወጣባቸው የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። የጥፋት ቡድኑ አባላት ከኦነግ ሸኔ እና ከሌሎች ፀረ-ሰላም ሃይሎች ጋር በመቀናጀትም ከተለያዩ ክልሎች አገርን የማፍረስ ተልዕኮ ያላቸውን ኃይሎች በመመልመል ትግራይ ክልል ድረስ በመውሰድ ለእኩይ ተልዕኮቸው ስኬት የተለያዩ ስልጠናዎችን በመስጠት እንዲሁም የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፎችን በማድረግ በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች ብሄርን ከብሄር በማጋጨት እና በሃይማኖት ሽፋን ሁከትና ብጥብጥ እንዲፈጠር በማድረግ በርካታ ንፅሁን ዜጎች እንዲገደሉ፣ በአካልና በንብረት ላይም ከባድ ጉዳት እንዲደርስ ማድረጋቸውን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በላከው መግለጫ አመልክቷል፡፡ እነዚህ የሀገር ህልውናን አደጋ ላይ በመጣል እንዲሁም ህገ-መንግስቱንና … [Read more...] about በ96 የህወሃት ወንበዴዎች ላይ የፍርድ ቤት ማዘዣ ወጣባቸው

Filed Under: Left Column, News, Politics Tagged With: operation dismantle tplf

የማይካድራ ዕልቂት

November 12, 2020 04:03 am by Editor 1 Comment

የማይካድራ ዕልቂት

በምዕራባዊ ትግራይ ሁመራ አቅራቢያ «ማይካድራ» በተባለው አካባቢ የትግራይ ልዩ ኃይል ባልታጠቁ የአማራ ተወላጆች ላይ በሌሊት አሰቃቂ ግድያ መፈፀሙን ከሞት ያመለጠ የዐይን እማኝ ገለፀ። ጥቃቱ የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው ሲል ደግሞ የአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ዐስታውቋል። በምዕራባዊ ትግራይ ሁመራ አቅራቢያ «ማይካድራ» በተባለው አካባቢ የትግራይ ልዩ ኃይል ባልታጠቁ የአማራ ተወላጆች ላይ በሌሊት አሰቃቂ ግድያ መፈፀሙን ከሞት ያመለጠ የዐይን እማኝ ገለፀ። ጥቃቱ የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው ሲል ደግሞ የአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ዐስታውቋል። ድርጊቱ የተጀመረውን ሕግ የማስከበር ሂደት ህወሓት ወደ የእርስ በእርስ ጦርነት እንዲቀየር የዘየደው መላ ነውም ብሎታል። አንዳንድ የአማራ ክልል ነዋሪዎች የህወሓት የተስፋ መቊረጥ ስሜት ነው፤ ኅብረተሰቡ ህወሓት በዘየደው የብቀላ ሂደት … [Read more...] about የማይካድራ ዕልቂት

Filed Under: News, Religion, Right Column Tagged With: operation dismantle tplf

የበረኻ ወንበዴዎቹ ያለከመከሰስ መብት ተነሳ

November 12, 2020 03:35 am by Editor Leave a Comment

የበረኻ ወንበዴዎቹ ያለከመከሰስ መብት ተነሳ

ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት/ትህነግ) በማለት የሚጠራውና በኢትዮጵያ እጅግ አስከፊ የሚባልና ትውልድን ያወደመ ርዕዮት በመከተል አገር ያፈረሰው የወንበዴዎች ጥርቅም፤ እስካሁንም በዓለምአቀፍ የአሸባሪዎች የመረጃ ቋት በአሸባሪነት ተመዝግቦ የሚገኝ ድርጅት መሆኑ ይታወቃል። አባላቱና ደጋፊዎችም በዚሁ ሁኔታ የሚታዩ መሆናቸውን ብዙዎች የሚስማሙበት ነው። ዛሬ የተሰበሰበው የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ አቃቤ ህግ በተለያዩ ወንጀሎች የጠረጠራቸውን ግለሰቦች ያለመከሰስ መብታቸው እንዲነሳ ያቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ በሙሉ ድምጽ አፀደቀ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 4ኛ መደበኛ ስብሰባው በወንጀል የተጠረጠሩ የምክር ቤት አባላትን ያለመከሰስ መብት አንስቷል። በዚህም መሰረት፦ 1. ደብረጸዮን ገብረሚካኤል 2. አስመላሽ … [Read more...] about የበረኻ ወንበዴዎቹ ያለከመከሰስ መብት ተነሳ

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: operation dismantle tplf

  • « Previous Page
  • Page 1
  • …
  • Page 45
  • Page 46
  • Page 47
  • Page 48
  • Page 49
  • Next Page »

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule