• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የማይካድራ ጭፍጨፋ ለረጅም ጊዜ የሚቆይ ሰብዓዊ፣ ስነልቦናዊ ቀውስና ጥልቅ ሀዘን ያስከተለ ነው” – ዶ/ር ዳንኤል

December 2, 2020 02:42 am by Editor 1 Comment

በህወሓት ጁንታ ቡድን ላይ ህግ የማስከበር ዘመቻ መጀመርን ተከትሎ በማይካድራ በሰላማዊ ዜጎች ላይ የተፈጸመው እልቂት በነዋሪዎች እና በተመልካች ላይ አስከፊ የስነ ልቦና ቀወስ ሊያስከትል እንደሚችል የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነር (ኢሰመኮ) ዶ/ር ዳንኤል በቀለ አስታወቀዋል።

ዶክተር ዳንኤል የማይካድራ ጭፍጨፋ አስመልክቶ በተለይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳስታወቁት፣ በማይካድራ የተፈጸሙ ግፍ በቁጥር ከሚገለጸው ሪፖርት ባሻገር በነዋሪዎች ላይ ሰብዓዊ እና ስነልቦናዊ ቀውስ እንዲሁም ጥልቅ ሀዘን አስከትሏል።

በማይካድራ አማራ እና በወልቃይት ተወላጆች ላይ ያነጣጠረውን ጥቃት ተከትሎ ቤተሰቦች መበታተናቸውንና ሕፃናት ለስነልቦና ቀውስ መዳረጋቸውን የተናገሩት ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል፤ የጭፍጨፋው ሰለባ ቤተሰቦች ህይወታቸውን እንደቀድሞ ለማስቀጠል አዳጋች እንደሚሆንባቸው ተናግረዋል። በመሆኑም ኢኮኖሚያቸው እንዲያንሰራራ እና ስነ ልቦናዊ ቀውስን መቋቋም እንዲችሉ ብዙ ሊሰራ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

ተጎጂዎቹ አስቸኳይ ድጋፍና እንክብካቤ የሚፈልጉ መሆናቸውን የጠቆሙት ኮሚሽነሩ፣ መንግሥት እና ዓለም አቀፍ ግብረ ሰናይ ድርጅት በአካባቢው የሚገኙ ተጎጂዎችን መልሶ ለማቋቋም በሚደረገው ጥረት እገዛ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

የማይካድራ ጥቃት ቀላል የወንጀል ድርጊት አይደለም፣ አስቀድሞ የታቀደና በጥንቃቄ የተቀናጀ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ነው ያሉት ዶ/ር ዳንኤል፤ የአካባቢው የፀጥታ መዋቅር ለጥቃቱ ተጠያቂ ከሆነው ሳምሪ ከሚባለው ቡድን ጋር ተባብሮ ንጹሃንን ከጉዳት ከመጠበቅ ይልቅ ጥቃቱን መደገፉንና በጥቃቱ መሳተፉን አስረድተዋል።

ወንጀሉ በአካባቢው በነበረው ሚሊሻዎችና ፖሊሶች ድጋፍና ተሳትፎ የተፈጸመ ነው ያሉት ዶ/ር ዳንኤል፤ ለወንጀለኞች ድጋፍ ያደረጉ እና የተሳተፉ የአካባቢው የፖሊስ እና ሚሊሻ አባላት በሕግ ፊት ተጠያቂ መሆን አለባቸው ብለዋል።

ኮሚሽነሩ አክለውም፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ከዚህ ቀደም ተፈጽሞ የማይታወቅ አይነት ጭካኔ የተሞላበት የወንጀል ድርጊት እንዴት እንደተፈጸመና እንደተቀነባበረ ተጨማሪ ምርመራዎችን ማካሄድ እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል።

የቅድሚያ ሪፖርቱ በቁጥር እና በጉዳት መጠን ላይ ትኩረት ተደርጎ የተዘጋጀ መሆኑን ያብራሩት ዶክተር ዳንኤል፤ ጭፍጨፋው ያስከተለው የስነልቦና-ማህበራዊ ተፅእኖው እንዲሁም ወንድም ወንድም ላይ እንዴት እንዲህ አይነት ጭካኔ የተሞላበት ግፍ ሊፈጽም እንደቻለ የዘርፉን ባለሙያዎች ትንታኔ እና አካታች ጥናት እንደሚፈልግ ጠቁመዋል። (ኢፕድ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, Social Tagged With: mia cadra, my cadra, operation dismantle tplf, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    December 3, 2020 07:30 am at 7:30 am

    የጨነቀለት ጦሩ በወያኔ ካሃዲዎች ተከቦ ከበባውን ሰብረው ጦሩን እንዲተነፍስ ያደረጉት የአማራ ልዪ ሃይል፤ ሚሊሻና ፋኖዎች የማህል ሃገር ሚዲያዎች ስለ ጀግንነታቸው ዝም ይበሉ እንጂ ስራቸው ጎልቶ ታይቷል። እልፍ ህዝብ የጨረሰውና ነገርን ሁሉ ለራሱ ብቻ የሚያስበው የወያኔ የጥፋት ሃይል ዛሬም በተለያየ ስምና የፓለቲካ አባዜ ገና ከጅምሩ የትግራይ ህዝብ ተጎዳ በማለት ሲጮሁ መስማት ያማል። ማንም የአማራ ህዝብ የትግራይን ህዝብ በማይካድራ እንደተፈጸመው አይጨፈጭፍም። ወያኔና የእነርሱ ርዝራዦች አውሬዎች ናቸው። አንድ የሰራዊቱ አባል እንዳለው በሬሳችን ላይ ነው ታንክ የነድበት ብሎአል። የኢትዮጵያ መንግሥት ለወያኔ ትራፊዎችና የድብቅ አድናቂዎች በምክር ቤትም ሆነ በሌሎች የሃገሪቱ መድረኮች ምላሽ ለመስጠት ከመሞከር ይልቅ የሰሩትን ግፍ ለዓለምና ለኢትዮጵያ ህዝብ ማሳወቁ ተገቢ ነው። በቅርቡ ጠ/ሚሩ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር በነበራቸው ቆይታ የአረናው ተወካይ ያነሳውን ነጥብ መስማት ያማል። እነዚህ ሰዎች በምንም መልኩ ከዘራቸው ውጭ መተንፈስ አይችሉም። ተለክፈዋል። ስንት ህዝብ አልቆ፤ የሃገር መከላከያ ተክዶና ተገድሎ እሱ የአማራ ህዝብ ቆርቆሮ ነቀለ ይለናል። ደንቆሮ። ለምን በትግራይ የነበሩ የአረና አባላት የት ደረሱ ብሎ አልጠየቀም? እኔ መንግስትም ሆነ ቀሪው የኢትዮጵያ ህዝብ ትግራዋይ የሆኑትን ሁሉ በጡጦ ማባበል ቢቀር መልካም ይመስለኛል። 45 ዓመት ሙሉ የሃገሪቱን ንብረት ስዘርፍና ህዝባችን ሲገድል የነበረ ድርጅት ደጋፊና የስራ አስፈጻሚ የነበሩ ሁሉ ሊፈተሹ ይገባል። ስንቶች ናቸው ምድሪቱን ለጠላት አሳልፈው የሰጡት? ስንቶች ናቸው ከማህል ሃገር ታፍነው ትግራይ በርሃ ውስጥ ተገድለው የተጣሉ። የጠ/ሚሩ የመለማመጥ ፓለቲካ አይሰራም። ቆራጥ አመራር አስፈላጊ ነው። የወያኔ ትራፊዎች ከፈለጉ ተመልሰው በረሃ ይግቡ። ዛሬም ትላንትም ዝርፊያና ግድያ ነው ተግባራቸው። የተለወጠ እይታ የላቸውም። በተንኮል የተካኑ ናቸው። ምናቸውም አይታመንም። በሃይለስላሴ ዘመን፤ በደርግ ጊዜ ሁሉ ከሥር ሆነው ወገኖችን ሲያስገድሉና ሲገሉ የነበሩ ለመሆናቸው መረጃዎች አሉ። ሌላው ቀርቶ በስደት ዓለም እንኳን እሱ/እሷ አማራ ናት ኦሮሞ ነው ብለው ከሰፈር የሚያስባርሩ፤ የውሸት ወሬ በማናፈስ ግጭት የሚፈጥሩ፤ በደቦ ሰውን የሚደበድቡ፤ ሰዎች ከሥራ እንዲባረሩ የውሸት ሴራ የሚሸርቡ ናቸው። ጥላቻቸው ውስጥ ዘልቆ የገባ ከእውነት ጋር የተጋጨ በመሆኑ አሁን እንሆ እንደ ህጻን አስበው የሮም አወዳደቅ ወደቁ። ስለሆነም ጠ/ሚሩ የትግራይ ተወላጆችን ማባበል ቢቀርባቸው ይሻላል። ያኔም የእንደመር ልመናቸው ነው እዚህ ያደረሰን። እንዴት እልፍ ህዝብ ሲገል የነበረ የአጋዚ ጦር መሪ የሰሜን እዝ የመገናኛ የሬዲዪ ሃላፊ አድርጎ ይሾማል። የሚገርም ነው። የሚያሳዝን።
    ይህ የአረና ተወካይ ነኝ ባይ በማይካድራ ወያኔ የፈጸመውን ወንጀል፤ በሁመራ በየሆስፒታሉ ሞተው የተገኙ ወገኖች፤ በሁመራ አየር ማረፊያ ግቢ ተረሽነው ስለተገኙ አማራዎች፤ ተክደው ስለተገደሉ የሃገሪቱ ወታድሮች አይገደውም። ጭኾቱ አሁንም እቃ እቃ ጫወታ ነው። 45 ዓመት መርዝ ለመንቀል ገና ብዙ ረጅም ጊዜ ይጠይቃል። በውጭ ሃገር፤ በሰፈራ ጣቢያ በሃገሪቱ መ/ቤቶችና ወታደራዊ ተቋማት ወዘተ… የዘረጉት መረብ መመንጠር አለበት። ይህ ሴራ ታልሞ ከስራ እስከዋለበት ድረስ አንድም የወያኔ የሴራ ተካፋዪች ትንፍሽ አላሉም። ሃገር ወዳድ የሰው ልጅ ህይወት ቢገዳቸው ኑሮ ቀኑ ከመድረሱ በፊት አንዳቸው ለመንግስት ሹክ ባሉ ነበር። ለዚህ ነው በዘራቸውና በቋንቋቸው የሰከሩ የሰው ባህሪ የሌላቸው ጉዶች ናቸው የምንለው። አማራ ጠላትህ ነው እየተባለ ለዘመናት የተሰበከለት የትግራይ ህዝብ ሊነቃ ይገባል። አማራ የትግራይ ህዝብ ጠላት ሆኖ አያውቅም። ወያኔና ጭፍራዎቹ ግን ያኔም ዛሬም የአማራ ህዝብ አንድነትና ሰላም ጠላቶች ናቸው። የማይካድራው ግድያ የወያኔ የመጨረሻው ጭፍጨፋ እንደሆነ አርገው የሚመለከቱ ሁሉ ተሳስተዋል። አሁንም ጊዜ እና እድል ካጋጠማቸው የበለጠ ጉዳት ያደርሳሉ። የአጥር ፈረሰብኝ የአረና ተወካዪ ጥያቄም ከዚህ ደባ ጋር አብሮ ሊታይ ይገባል። ሁሌ ተበደልኩ እያሉ መጮህ ይቁም! እኛም ሰሚ እናግኝ! በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule