• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የራያ ህዝብ ወደ ወሎ እንዲጠቃለል ሃሳብ ቀረበ

November 30, 2020 12:37 pm by Editor 1 Comment

የትግራይ ህዝብ ነጻነት ግንባር (ትህነግ) ቡድን ድል በተደረገበት ማግስት የራያ ህዝብ እጣ ፋንታ ምን መሆን አለበት በሚል ሃሳብ የአካባቢው ተወላጆች እና ሙህራን እሁድሕዳር 20 ቀን 2013 ዓ.ም በአዲስ አበባ መክረዋል።

በዚህ ውይይት ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ እና የአገልግሎት ዘርፎች ክላስተር አስተባባሪ አቶ ጃንጥራር አባይ የራያ ህዝብ ውብ ባህሉ እና ማንነቱ ተከብሮ ወደ ሚፈልገው እና ወደ ሚመስለው የወሎ ህዝብ እንዲጠቃለል የምሁራን ውይይት አስፈላጊ ነው ብለዋል።

ጊዜው ችግሮችን በውይይት የምንፈታበት እንደመሆኑ ህዝቡ ምን ይላል የሚለውን አዳምጦ በትህነግ ጭቆና ውስጥ የነበረውን ማህበረሰብ የነጻነት አየር የሚተነፍስበት ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚገባ አሳስበዋል።

በመድረኩ የመወያያ ሃሳብ ያቀረቡት ምህራን ትህነግ የአማርኛ ስም መጠሪያ ያላቸውን ስፍራዎች ወደ ትግርኛ ቀይሮ መቆየቱን እና ህጻናት በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው እንዳይማሩ ተደርገው ስለመቆየታቸው አውስተዋል።

ማህበረሰቡ ላይ የተፈጸመውን በኢኮኖሚያ አሻጥር አስመልክቶም ተጽእኖ ለግዙፍ ፋብሪካ የተዘጋጁ ማሽነሪዎች ተነቅለው ወደ ትግራይ እንዲወሰዱ መደረጉ ምን ያህል የአካባቢ ነዋሪ ከምጣኔ ሃብት እድገት ተነጥሎ እንደኖረ ማሳያ ነውም ይላሉ ምሁራኑ።

ለገበሬው የተቆረፉ የውሃ ጉድጓዶች እንዲደፈኑ መደረግና  በኢንቨስትመንት ስም ከፍተኛ የሆነ የመሬት ወረራ መፈጸም ሌላኛው የራያ አካባቢዎች ላይ በትህነግ የተፈጸመ ድርጊት ነው የሚሉት ምሁራኑ ለትህነግ ፋብሪካዎች ግብዓት እንዲሆን ከፍተኛ የሆነ የደን ጭፍጨፋ መፈጸሙንም አንስተዋል።

በዚህም በአካባቢው ከፍተኛ የሆነ በረሃማነት እንዲስፋፋ ሆኗል ብለዋል።

የአካባቢው ተወላጃም በትህነግ የተነጠቀውን ማንነቱን ለማስጠበቅ በግፍ ተገድሏል ተብሏል።

አካባቢውንም ለቆ እንዲሰደድ ተደርጓል ብለዋል።

ዛሬም ድረስ የት እንዳሉ በማይታወቅበት ሁኔታ ታፍነው የተወሰዱ የአካባቢው ተወላጆች እንዳሉም ተነስቷል።

የራያ ህዝብ በትግራይ እና በአማራ ክልሎች ያለፍላጎቱ ተከፋፍሎ እንዲኖር ያደረገው የትህነግ ሃይል መወገዱን ተከትሎ ዛሬም በፖለቲከኞች ጉተታ አሁን ያገኘውን እድል እንዳያጣ በጥንቃቄ መሰራት እንዳለበት አሳስበዋል። (መቅደላዊት ደረጀ፤ ኢትዮ ኤፍኤም 107.8)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Left Column, Social Tagged With: operation dismantle tplf, raya

Reader Interactions

Comments

  1. yuya Jemal says

    December 2, 2020 07:56 am at 7:56 am

    Raya-Wollo-Oromo.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule