• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የራያ ህዝብ ወደ ወሎ እንዲጠቃለል ሃሳብ ቀረበ

November 30, 2020 12:37 pm by Editor 1 Comment

የትግራይ ህዝብ ነጻነት ግንባር (ትህነግ) ቡድን ድል በተደረገበት ማግስት የራያ ህዝብ እጣ ፋንታ ምን መሆን አለበት በሚል ሃሳብ የአካባቢው ተወላጆች እና ሙህራን እሁድሕዳር 20 ቀን 2013 ዓ.ም በአዲስ አበባ መክረዋል።

በዚህ ውይይት ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ እና የአገልግሎት ዘርፎች ክላስተር አስተባባሪ አቶ ጃንጥራር አባይ የራያ ህዝብ ውብ ባህሉ እና ማንነቱ ተከብሮ ወደ ሚፈልገው እና ወደ ሚመስለው የወሎ ህዝብ እንዲጠቃለል የምሁራን ውይይት አስፈላጊ ነው ብለዋል።

ጊዜው ችግሮችን በውይይት የምንፈታበት እንደመሆኑ ህዝቡ ምን ይላል የሚለውን አዳምጦ በትህነግ ጭቆና ውስጥ የነበረውን ማህበረሰብ የነጻነት አየር የሚተነፍስበት ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚገባ አሳስበዋል።

በመድረኩ የመወያያ ሃሳብ ያቀረቡት ምህራን ትህነግ የአማርኛ ስም መጠሪያ ያላቸውን ስፍራዎች ወደ ትግርኛ ቀይሮ መቆየቱን እና ህጻናት በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው እንዳይማሩ ተደርገው ስለመቆየታቸው አውስተዋል።

ማህበረሰቡ ላይ የተፈጸመውን በኢኮኖሚያ አሻጥር አስመልክቶም ተጽእኖ ለግዙፍ ፋብሪካ የተዘጋጁ ማሽነሪዎች ተነቅለው ወደ ትግራይ እንዲወሰዱ መደረጉ ምን ያህል የአካባቢ ነዋሪ ከምጣኔ ሃብት እድገት ተነጥሎ እንደኖረ ማሳያ ነውም ይላሉ ምሁራኑ።

ለገበሬው የተቆረፉ የውሃ ጉድጓዶች እንዲደፈኑ መደረግና  በኢንቨስትመንት ስም ከፍተኛ የሆነ የመሬት ወረራ መፈጸም ሌላኛው የራያ አካባቢዎች ላይ በትህነግ የተፈጸመ ድርጊት ነው የሚሉት ምሁራኑ ለትህነግ ፋብሪካዎች ግብዓት እንዲሆን ከፍተኛ የሆነ የደን ጭፍጨፋ መፈጸሙንም አንስተዋል።

በዚህም በአካባቢው ከፍተኛ የሆነ በረሃማነት እንዲስፋፋ ሆኗል ብለዋል።

የአካባቢው ተወላጃም በትህነግ የተነጠቀውን ማንነቱን ለማስጠበቅ በግፍ ተገድሏል ተብሏል።

አካባቢውንም ለቆ እንዲሰደድ ተደርጓል ብለዋል።

ዛሬም ድረስ የት እንዳሉ በማይታወቅበት ሁኔታ ታፍነው የተወሰዱ የአካባቢው ተወላጆች እንዳሉም ተነስቷል።

የራያ ህዝብ በትግራይ እና በአማራ ክልሎች ያለፍላጎቱ ተከፋፍሎ እንዲኖር ያደረገው የትህነግ ሃይል መወገዱን ተከትሎ ዛሬም በፖለቲከኞች ጉተታ አሁን ያገኘውን እድል እንዳያጣ በጥንቃቄ መሰራት እንዳለበት አሳስበዋል። (መቅደላዊት ደረጀ፤ ኢትዮ ኤፍኤም 107.8)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Left Column, Social Tagged With: operation dismantle tplf, raya

Reader Interactions

Comments

  1. yuya Jemal says

    December 2, 2020 07:56 am at 7:56 am

    Raya-Wollo-Oromo.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule