ከዚህ በፊት ባልተለመደ መልኩ የጦር ኃይሎች ዋና አዛዡ ዐቢይ አህመድ ጄኔራሎቻቸውን በቅጽል ስም በመጥራት ለኢትዮጵያ የሰሩትን ውለታ በዚህ መልኩ አወድሰዋል፤ 1. ድል ቁርሱ ጀነራል ብርሃኑ ጁላ 2. ትንታጉ ሌ/ጀነራል አበባዉ ታደሰ 3. ነበልባሉ ሌ/ጀነራል ባጫ ደበሌ 4. ሀገር ወዳዱ ሌ/ጀነራል ዮሃንስ ገብረመስቀል 5. የወገን አቅም ገንቢዉ ሌ/ጀነራል ሀሰን ኢብራሂም 6. ግስላዉ ሌ/ጀነራል ጌታቸዉ ጉዲና 7. አነፍናፊዉ ሌ/ጀነራል አስራት ዲናሮ 8. የጦርነት ሊቁ ሜ/ጀነራል አለምሸት ደግፌ 9. ሰዉ ሀይል አመጋጋቢ ሜ/ጀነራል ሀጫሉ ሸለማ 10. አይበገሬዉ ሜ/ጀነራል ዘዉዱ በላይ 11. ሳተናዉ ሜ/ጀነራል በላይ ሥዩም 12. ልበ ቆራጡ ሜ/ጀነራል መሰለ መሰረት 13. ሎጂስቲክስ አሳላጩ ሜጀር ጀኔራል አብዱራህማን … [Read more...] about መለዮ ለባሾቹ የቁርጥ ቀን ልጆች
operation dismantle tplf
ህወሓት በማይካድራ በፈፀመው ወንጀል በሽብርተኝነት እንዲፈረጅ ተጠየቀ
የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ሕወሓት ዘርን መሠረት አድርጎ በማይካድራ በፈፀመው የንጹሐን ዜጎች የግድያ ወንጀል መንስዔ በሽብርተኝነት እንዲፈረጅ ጠየቁ። አባላቱ ይህንን እና ሌሎች መሰል ወቅታዊ ጥያቄዎችን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አቅርበዋል። የተደረገው ፍጹም ጭካኔያዊ እና አረመኔያዊ ድርጊት እጅግ እንዳሳዘናቸውም አያይዘው ገልጸዋል። ተግባሩም የጦር ወንጀለኝነት መሆኑንም አበክረው ተናግረዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት አክለውም፤ የሀገርን እና የህዝብን አደራ ተቀብለው ግዳጃቸውን እየተወጡ በነበሩት የሰሜን ዕዝ የሠራዊት አባላት ላይ የሕወሓት ጽንፈኛ ቡድን የወሰደው ኢ-ሰብዓዊ ድርጊትም እጅግ እንዳሳዘናቸው ገልጸዋል። በየትኛውም የህግ መመዘኛ ተቀባይነት እንደሌለውም አስረድተዋል። የፓርላማ አባላቱ በተጨማሪም፤ የኢፌዴሪ የሀገር … [Read more...] about ህወሓት በማይካድራ በፈፀመው ወንጀል በሽብርተኝነት እንዲፈረጅ ተጠየቀ
በጋምቤላ ክልል ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያ ይዘው ለማምለጥ በሞከሩ አዘዋዋሪዎች ላይ እርምጃ ተወሰደ
በጋምቤላ ክልል ኢታንግ ልዩ ወረዳ ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያ አዘዋዋሪዎች ከጸጥታ አካላት ለማምለጥ ባደረጉት የተኩስ ልውውጥ እርምጃ እንደተወሰደባቸው የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ኮማንደር ኡማን ኡጋላ ለኢዜአ እንዳሉት እርምጃው የተወሰደው ግለሰቦቹ ትናንት ምሽት አራት ስዓት ላይ ከኑዌር ዞን ወደ ኢታንግ ልዩ ወረዳ ጦር መሳሪያዎችን በሸክም ለማስገባት ሲሞከሩ ነው። እነሱን ለመያዝ በተደረገው የተኩስ ልውውጥም ሁለት ጦር መሳሪያ አዘዋዋሪዎች መሞታቸውንና አንዱ ደግሞ ቆስሎ መያዙን ተናግረዋል። በግለሰቦቹ እጅ የነበሩት 19 ታጣፊና ዘጠኝ ባለሰደፍ በድምሩ 28 የክላሽንኮቭ ጠመንጃዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልጸዋል። ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያ አዘዋዋሪዎች በእጃቸው ይዘዋቸው የነበሩትን ሌሎች መሳሪያዎች እየተታኩሱ ይዘው ማምለጣቸውን ጠቁመው "እነሱን … [Read more...] about በጋምቤላ ክልል ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያ ይዘው ለማምለጥ በሞከሩ አዘዋዋሪዎች ላይ እርምጃ ተወሰደ
በአገር ውስጥ እና በውጭ የወንበዴው ህወሓት አስፈጻሚዎች እንዲያዙ ትዕዛዝ ወጣ
የአገር ክህደት ወንጀል በፈፀሙና በተለያዩ እርከን በሚገኙ 27 ወታደራዊ ሹማምንት በፈፀሙት የዘረፋ ወንጀል ንብረታቸው የሚፈለግ የህወሃት ቡድን አባላት እና ዳንኤል ብርሃኔ፣ ዶክተር እዝቅኤል ገቢሳ፣ ዶክተር አወል አሎ ቃሲም እና ሌሎች አምስት ግለሰቦች በአገር ውስጥና ባህር ማዶ ሆነው የተለያዩ ሚዲያዎችን በመጠቀም አገር አፍራሽ መረጃ በሚያሰራጩ ግለሰቦች ላይ የመያዣ ትዕዛዝ መውጣቱን ፌዴራል ፖሊስ አስታውቋል። በመግለጫው መሠረት ቀደም ሲል በፈፀሙት የአገር ክህደት ወንጀል የመያዣ ትዕዛዝ ከወጣባቸው 117 ጄኔራል መኮንኖች፣ ከፍተኛ መኮንኖችና የበታች ሹማምንቶች በተጨማሪ ስማቸው ቀጥሎ የተገለፀው 7 በተለያየ እርከን ላይ የሚገኙ ወታደራዊ ሹማምንት ላይ የመያዣ ትዕዛዝ እንዲወጣ ተደርጓል። በዚህም መሠረት፡- 1/ሜጀር ጀነራል ዘውዱ ኪሮስ ገብረኪዳን 2/ኮሎኔል … [Read more...] about በአገር ውስጥ እና በውጭ የወንበዴው ህወሓት አስፈጻሚዎች እንዲያዙ ትዕዛዝ ወጣ
ነቀርሳው ህወሓት ተነቀለ!
በትግራይ ክልል ከጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም. ምሽት ጀምሮ ለ25 ቀናት በሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ቡድንና በመከላከያ ሠራዊቱ መካከል ሲደረግ የሰነበተው ውጊያ፣ ቅዳሜ ኅዳር 19 ቀን ከሰዓት በኋላ የመከላከያ ሠራዊቱ የክልሉ ዋና ከተማ መቀሌን ሙሉ በሙሉ በመቆጣጠር መጠናቀቁን ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ(ዶ/ር) እና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ አረጋግጠዋል። መከላከያ ሠራዊቱ ባካሄደው ዘመቻ ንጹኃን ዜጎች ዒላማ ሳይሆኑና ቅርሶች ሳይጎዱ መቀሌ ለመግባት መቻሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አስታውቀዋል። ሠራዊቱ የመቀሌ ከተማ ነዋሪ ላይ ጉዳት ሳይደርስ እንዴት ከተማዋን መቆጣጠር ይቻላል በሚለው ላይ ኅዳር 18 ቀን ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱን በመግለጫቸው ያስታወሱት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ፣ … [Read more...] about ነቀርሳው ህወሓት ተነቀለ!
ዐቃቤ ሕግ በ167 የህወሃት ሰዎች ላይ የእስር ትዕዛዝ ማውጣቱን አስታወቀ
በትግራይ ክልል ከተከሰተው ቀውስ ጋር በተያያዘ የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ በ167 ሰዎች ላይ የእስር ትዕዛዝ ማውጣቱን ይፋ አደረገ። ይህ የተባለው የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) እና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ፍሰት ቃል አቀባይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲኤታ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ትናንት በጋራ በሰጡት መግለጫ ነው። ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጉ በመግለጫው ላይ በህውሓት ኃይሎች የተፈጸሙት ተግባራት በአገሪቱ የወንጀል ሕግ አንጻር በከፍተኛ ወንጀል የሚያስጠይቁ ናቸው ብለዋል። በአገር መከላከያ ሠራዊት ላይ የተፈጸመው ጥቃት 'የመንግሥትን አገሪቱን የመከላከል ኃይል ለማዳከም' በተፈጸመ ወንጀል በሚል የሚያስጠይቅ መሆኑን ጠቁመዋል። በባሕር ዳር እና ጎንደር ከተሞች ላይ የተፈጸሙትን የሮኬት ጥቃቶች በተመለከተም፤ ድርጊቱ በሽብር ወንጀል … [Read more...] about ዐቃቤ ሕግ በ167 የህወሃት ሰዎች ላይ የእስር ትዕዛዝ ማውጣቱን አስታወቀ
ህወሃት እንደአጀማመሩ እየተጠናቀቀ ነው
ድልድይ በማፍረስ፤ መሠረተ ልማቶችን በማውደም ከየቦታው በተለቃቀሙ ወንበዴዎች መሪነት ኢትዮጵያን በነጻ አውጪ ስም በግፍ ሲገዛ የነበረው ህወሃት/ትህነግ እንደ አጀማመሩ አፈጻጸሙም እየሆነ እንዳለ ተጠቆመ። ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት/ትህነግ) በማለት የሚጠራውና በኢትዮጵያ እጅግ አስከፊ የሚባልና ትውልድን ያወደመ ርዕዮት በመከተል አገር ያፈረሰው የወንበዴዎች ጥርቅም፤ እስካሁንም በዓለምአቀፍ የአሸባሪዎች የመረጃ ቋት በአሸባሪነት ተመዝግቦ የሚገኝ ድርጅት መሆኑ ይታወቃል። አባላቱና ደጋፊዎችም በዚሁ ሁኔታ የሚታዩ መሆናቸውን ብዙዎች የሚስማሙበት ነው። ከዚህ በታች የሚገኘው መረጃ በዓለምአቀፉ የአሸባሪዎች ቋት ተመዝግቦ የሚገኝ የህወሃት ወንጀል ዝርዝር ነው። በበረሃ ዘመኑ ህወሃት ካወደማቸው በጥቂቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ ትላንት … [Read more...] about ህወሃት እንደአጀማመሩ እየተጠናቀቀ ነው
“እየደበደቡ፤ በሳንጃ አንገታቸውን እየቀሉ ሲገሏቸው ተመልክቻለሁ” – የማይካድራው ጭፍጨፋ የዓይን እማኝ
መላ ሰውነቱ ይንቀጠቀጣል፤ ከንፈሩ ደርቋል። ለሁለት ቀናት ምግብ አላገኘም። ድንጋጤ አለቀቀውም። ከማይካድራ ግድያ አምልጦ ሁመራ ከተማ መከላከያ ሠራዊት ካምፕ በር ላይ ያገኘነው ወጣት ዳንኤል ማሚን። የደቡብ ክልል የቴፒ ተወላጅ ነው፤ አገር ሰላም ብሎ በማይካድራ ልብስ እየነገደ መኖር ከጀመረ 13 ዓመት ሆኖታል። በዚች ከተማ ይህን ያህል ሲኖር የከፋ አይደለም፤ ቀለል ያለ ችግርም አጋጥሞት አያውቅም። በሚኖርባትና ህይወቱን ለማሻሻል በሚደክምባት ከተማ ቤትና ንብረትም አፍርቷል። ከሰባት ቀናት በፊት ከቀኑ 9 ሰዓት አካባቢ በማይካድራ ከተማ በአማራና በሌሎች ብሄሮች ተወላጆች ላይ ያልታሰበ፣ አስደንጋጭና ዘግናኝ ግድያ ሲፈጸም በዓይኑ ተመልክቷል፤ እሱም ከዚህ ዘግናኝ ጭፍጨፋ አምልጦ በመከላከያ ሠራዊት ቁጥጥር ስር ወደ ዋለችው ሁመራ ከተማ መምጣቱን ይናገራል። የትግራይ ልዩ … [Read more...] about “እየደበደቡ፤ በሳንጃ አንገታቸውን እየቀሉ ሲገሏቸው ተመልክቻለሁ” – የማይካድራው ጭፍጨፋ የዓይን እማኝ
የትግራይ ክልል መዋቅር ዳግም ይደራጃል
የትግራይ ጊዜአዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ሙሉ ነጋ በጊዜአዊ አስተዳደሩ የሚሰሩ ስራዎችን በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል። ዶ/ር ሙሉ በመግለጫቸው የትግራይ ክልል መዋቅር ዳግም እንደሚደራጅ ተናግረዋል። የክልሉ ካቢኔና የዞን አስተዳደርም እንደአዲስ እንደሚዋቀርም የተናገሩት ዶ/ር ሙሉ የወረዳና የቀበሌ ምክር ቤቶች እንዳሉ ይቀጥላሉ ብለዋል። መንግስት የጀመረውን የህግ ማስከበር እርምጃ እንደመልካም አጋጣሚ በመጠቀም የህዝቡን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ይሰራልም ብለዋል። ከፅንፈኛው ህወሓት ቡድን ነፃ የወጡ አካባቢዎች ላይ መዋቅሮችን በመዘርጋት ህዝቡ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴው እንዲመለስ እንደሚሰራም ተናግረዋል። የህወሓት ፅንፈኛ ቡድን ላለፉት ሁለት ዓመታት ተኩል በክልሉ ምንም አይነት የልማት ስራ አልተሰራም ያሉት ዶክተር ሙሉ ህግ የማስከበሩ ስራ … [Read more...] about የትግራይ ክልል መዋቅር ዳግም ይደራጃል
“በዚህ ውጊያ አላምንበትም” አብረኸት
አብረኸት የጁንታው ታጣቂ የነበረችና እጃቸውን ለመከላከያ ሰራዊት ከሰጡ ውስጥ አንዷ ነች። ገና የ21 ዓመት ወጣት ናት። ወጣቷ በ2011 ዓ.ም የሀገር መከላከያ ሰራዊትን ለመቀላቀል በብርሸለቆ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ስልጠና ወስዳለች። የኢትዮጵያ መካላከያ ሰራዊት አባል ሁና ነገሌ ቦረና ተመድባም ግዳጇን እየተወጣች ሳለ በጠና ታምማ ከውትድርናው ዓለም ተሰናብታ ወደ ቤተሰቦቿ መመለሷን በስፍራው ተገኝቶ ላነጋገራት የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅይ ዘጋቢ ገልጻለች። የአብረኸት ህመም መጥናት ከምትወደው መከላከያ ቢለያትም ከጁንታው ዕይታ ግን መሰወር አልቻለችም። በጠላ ንግድ የሚተዳደሩትን እናቷን እያገዘች ኑሮን ብትቀጥልም፤ የጁንታው አባላት የአብረኸትን ወታደርነት ያውቁ ነበርና የጁንታውን ታጣቂ እንድትቀላቀል በእናቷ በኩል ግፊት ማድረግ ጀመሩ። ጁንታው የአብረኸትን እናት ሌት ተቀን … [Read more...] about “በዚህ ውጊያ አላምንበትም” አብረኸት










