• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ

January 7, 2021 01:16 pm by Editor 1 Comment

የመከላከያ ሀይል ሰምሪት መምሪያ ኃላፊ ብ/ጄኔራል ተስፋዬ አያሌው እንዳረጋገጡት 9 የጁንታው ከፍተኛ አመራሮች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን 4 የቡድኑ አባላት ደግሞ እርምጃም ተወስዶባቸዋል።

የሰሜን ዕዝን በ45 ደቂቃ ውስጥ መብረቃዊ ጥቃት በመፈጸም ከጥቅም ውጭ አድርገነዋል ብሎ የገለፀውን የጁንታው አፈቀላጤ ጨምሮ 4 ከፍተኛ የጁንታው ቡድን አመራሮች ከነአጃቢዎቻቸውና ጠባቂዎቻቸው ተደምስሰዋል።

የመከላከያ ሠራዊት ኃይል ስምሪት መምሪያ ሃላፊ ብርጋዴል ጀኔራል ተስፋዬ አያሌው ለኢዜአ እንደገለፁት ሴኩቱሬ ጌታቸውና ዘርአይ አስገዶምን ጨምሮ በርካቶች ሲደመሰሱ ወይዘሮ ቅዱሳን ነጋ እና ዶክተር ሰለሞን ኪዳኔና ሌሎች በቁጥጥር ሥር ውለዋል።

በዚህም መሰረት፣

ዳንኤል አሰፋ (የጌታቸው አሰፋ ወንድም)

1. የጁንታው ቃል አቀባይ ሴኩቱሬ ጌታቸው፣

2. ዘርአይ አስገዶም የቀድሞው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ስራ አስኪያጅና የብሮድካስት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር የነበረ፣

3. አበበ ገብረመድህን የድምጸ ወያኔ ሃላፊ የነበረ፣

4. ዳንኤል አሰፋ (የጌታቸው አሰፋ ወንድም) የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ሃላፊ የነበረ ከሹፌሮቻቸውና ከጥበቃዎቻቸው ጋር፣

በጀግናው የመከላከያ ሠራዊት፣ በፌዴራል የጸጥታ ተቋማትና በትግራይ ህዝብና በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር በተደረገ የተቀናጀ ዘመቻ መደምሰሳቸውን ብርጋዴል ጀኔራል ተስፋዬ አያሌው ለኢዜአ ተናግረዋል።

ቅዱሳን ነጋ

ከተደመሰሱት ውስጥ ሴኩቱሬ ጌታቸው ከዚህ ቀደም በጁንታው መገናኛ ብዙሃን በኩል ጁንታው የመከላከያ ሰራዊት ሰሜን ዕዝ ላይ መብረቃዊ ጥቃት ፈፅሟል ብሎ ማረጋገጡ ይታወሳል።

ከተደመሰሱት በተጨማሪም 9 የጁንታው ቁልፍ አባላት በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን እነሱም፣

1. ቅዱሳን ነጋ የቀድሞ የክልሉ አፈጉባኤ የነበረች፣ የስብሃት ነጋ እህት፣

2. ሰለሞን ኪዳኔ የቀድሞ የትግራይ ክልል ከተማ ልማት ቢሮ ሃላፊና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ የነበረ፣

3. ተክለወይኒ አሰፋ የማረት ስራ አስፈጻሚ የነበረ፣

ሰለሞን ኪዳኔ

4. ገብረመድህን ተወልደ የክልሉ ንግድ ቢሮ ሃላፊ የነበረ፣

5. ወልደጊዮርጊስ ደስታ የክልሉ መንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ የነበረ፣

6. አባዲ ዘሙ በሱዳን የኢትዮጵያ የቀድሞ አምባሳደር የነበረና የጁንታውን ፖለቲካ ክንፍ የተቀላቀለ፣

7. ቴዎድሮስ ሃጎስ የመለስ አመራር አካዳሚ ፕሬዚዳንትና የኢፈርት ቦርድ ሃላፊ የነበረ፣

8. ምህረት ተክላይ የክልሉ ምክር ቤት ህግ አማካሪ የነበረች እንዲሁም

እጅ አልባው አባዲ ዘሙ

9. ብርሃነ አደም መሃመድ የክልሉ የንብረትና ግዢ ስራ ሂደት ሃላፊ የነበረ ሁሉም በቁጥጥር ሥር ውለዋል።

የህወሃት ጁንታ ባለስልጣናት በቁጥጥር ስር የዋሉት በጫካና ዋሻ ለዋሻ ሲንቀሳቀሱ በተደረገ ጠንካራ አሰሳ መሆኑንም ብርጋዴል ጀኔራሉ ገልጸዋል።

የአገር መከላከያ ሰራዊት እነዚህ የጁንታው ቁልፍ የጥፋት ቡድን አባላት እንዲደመሰሱና በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ ያላሰለሰ ድጋፍ ላደረገው መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ምስጋናውን አቅርቧል።

ሠራዊቱ ወንጀለኞቹን አድኖ ለመያዝ ቃል በገባው መሰረት ግዳጁን እየተወጣ መሆኑን ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ የሆነው ጀግናው የመከላከያ ሰራዊት የጀመረውን ቀሪ የጁንታውን ርዝራዦችን አድኖ ለመያዝና በህግ ተጠያቂ ለማድረግ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ብርጋዴል ጀነራል ተስፋዬ አረጋግጠዋል።

ሕዝቡ እያደረገ ያለውን ድጋፍና ተሳትፎ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪ አስተላልፈዋል ሲል ፋና ዘግቧል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: getachew assefa, meles zenawi, operation dismantle tplf, sebhat nega, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    January 9, 2021 09:11 am at 9:11 am

    ጊዜ ከሰው ጋራ እየገፈተረ ባፍጢሙ ለደፋው ለዛሬ ለሌለ
    በትዕቢት ተይዞ ፈርኦን ለሆነ፤ ሲመከር ሲለመን አሻፈረኝ ላለ
    በእነዚህ ግፈኞች የሃገር እሾኾች የተንኮል ኮረጆ
    እንባቸው፤ ደማቸው ዶፍ ሆኖ ያለፈ
    የስንቱ ቤት ፈረሶ ስንቶችስ ሞተዋል?
    በስቃይ ሰቆቃ ዘመን የቆጠሩ እናቶች አባቶች ዛሬ ላይ የቆሙ
    አይባልም ነበር ሰው ሲሞት እሰየው አሁን ግን ጨፍሩ እንዳሻችሁ ሁኑ
    ወያኔ ሞታለች ብላችሁ አብስሩ።

    በአለም ታሪክ ውስጥ የሾኬ ተጠልፈው ከስልጣን የወረድ፤ በጦር ተሸንፈው ያጎበደድ፤ ለመኖር የገደሉና የዘረፉ ለመኖራቸው ቃልቻ መጠየቅ አይሻም። ነበሩ። አሉ፤ ይኖራሉ። ይሁን እንጂ እንደ ወያኔ ያለ በአንድ ዘር ብቻ የተዋቀረ እብድ ቡድን በሃበሻው መሬትም ሆነ በሌላው አለም ታይቶ አይታወቅም። አሁን ይሙት ይዳን የማይታወቀው የወያኔ አፈቀላጼ አቶ ጌታቸው ረዳ ያኔ ከሶስት ዓመት በፊት እንደፈለጉ ሲፈነጩ እንዲህ ብሎ ነበር። “አማራና ኦሮሞ አንድ ሆኑ ማለት እኛ የቤት ስራችንን አልሰራንም ማለት ነው”። ባጭሩ ሲተረጎም እነርሱ ሲጫረሱ የእኛ መኖር ይረጋገጣል ነው። አይ ወያኔ በሰው ደም ታጣቢ። በትግራይ ህዝብ ነጋጂ። በራሱ የፓለቲካ ሸር የሰከረ ድርጅት። እንዲህ እንደ ሮም መንግስት ሸክላ ይሁን? እሰይ የስለት ጧፌን አስገባለሁ። ጧፉ ሲነድ የእነርሱ መቃጠል ይታየኛልና። ከዋሻ የወጣ ምንጊዜም ቢሆን መደበቂያው ዋሻ ነው። የዋሻ አስተሳሰብ እንደያዙ መሞት ግን የሞትም ሞት ነው። ገደል ስለገባቸው የሟች ጄኔራል ሚስት ሳስብ እብደታቸው ምን ያህል ሰማይ ጠቀስ እንደሆነ ያሳያል። እንዴት ሰው አሜሪካን የመሰለ ነገር አይቶ አይማርም። እንዲህ የውሻ ሞት ያስሞታት የሰው ደም ነው። እኔ የሚገርመኝ የስብሃት ነጋ ጠባቂዎች ተደምስሰው እሱ መያዙ። ሁለት እህታማቾች ይጣሉና ትልቋ አንቺ ዝም በይ እኔ እኮ ያንቺን ዳይፕር እየቀየርኩ ነው ያሳደኩሽ ብትላት ያው ቀብድ እየከፈልሽ ነዋ። እኔም አንቺ ስታረጂ የአንቺን መቀየሬ አይቀርም አለቻት። ሁላችንም ተሳስቀን ነገሩ አለፈ። አሁን ማን ይሙት የትግራይ ወጣት ልጆች ተደምስሰው ይህ ጥርሱ የወላለቀ ዲያብሎስ በነፈሱ ይያዛል። የወያኔ ጠባቂዎች ምን ቢጋቱ ነው ቀኑ እንደመሸ አለማወቃቸው? አሁን ድምጽ የጠፋው የጋዜጠኛው እና የስደተኛው ማስታወሻ ደራሲና የሻቢያ ሰላይ አቶ ተስፋዬ ገ/አብ የጋዜጠኛው ማስታወሻ በሚለው ላይ እንዲህ ብሎን ነበር። ” ሰዎች ተሰብስበው በአንድ ክበብ ውስጥ ይጫወታሉ። ብዙዎቹ የወያኔ ባለስልጣኖችና ወታደራዊ መኮንኖች ናቸው። የካራምቦላ ጫዋታ ላይ አንድ ጄኔራል ከስብሃት ነጋ ጋር ሳይግባባ ቀርቶ ስብሃት ስለተቆጣ ይገድልሃል ዝም በል ተብሎ ቁጭ ብሎ እንደ ሴት ልጅ ሲያለቅስ ትዝ ይለኛል ይለናል። በሌላው ትዝታው ደግሞ ወያኔዎች ተሰብስበው ዛሬ ማንን እንግደል በማለት አምቦ የሚገኘውን ባለሃብት የአበበች ደራራን አባት አስገድለው ገዳዪን ወታደር እንደገደሉት ይናገራል። ከዚህ የጨለማ ሃይል ጋር ነው ኦነጎች ህብረት የጀመሩት፡፡ የሙት ትውልድ ሙታንን ይከተላል፡፡ ሰፊና አለም አቀፋዊ እይታ ያለው ደግሞ ለሰው ልጆች መብት ዘርና ቋንቋን ተገን ሳያደርግ ይፋለማል፡፡ በተለይም በአለም ዙሪያ በቆዳቸው ቀለም ብቻ መከራና ሃበሳ ለሚቆጥሩ የጥቁሮች መብት ይቆማል።
    በቅርቡ አንድ ሰው አስቆመኝና ከየት ሃገር ነህ? ኢትዮጵያዊ ትመስላለህ ሲለኝ አዎን ከዛው ነኝ ስለው እኔ ከአልባኒያ ነኝ አለኝ። እሺ አልኩ። ታሪክን ምን ያህል ታውቃለህ ሲለኝ የታሪክ ተማሪ አይደለሁም አላውቅም አልኩት። የእኔና የአንተ ሃገር በፋሺሽቱ ጣሊያ ሞሶሎኒ ሁለት ጊዜ ተወረናል ሲለኝ ድንግጥ አልኩ። የማውቀው የእኛውን ብቻ ነው። እናንተም ሁለት ጊዜ ተወራችሁሃል በጣሊያን አልኩት አዎን። በነጮች የቀን መለኪያ 1918-1920 ከዚያም 1939-1943 በማለት ተጫውተን ተለያየን። ለካ ወረራው ለአውሮፓም ደርሷል ብዬ በሆዴ ቤቴ ገብቼ ታሪኩ እውነት መሆኑ አረጋገጥኩ። የምንሸልለው ወንድምና እህታችንን ገድለን፤ ደሳሳ ጎጆአችን በራፍ ላይ ቆመን ወያኔ ባሰመረው የአፓርታይድ የክልል ስሪት ላይ እስከሆነ ድረስ ብዝሃነት አይኖረንም። አንድ የአንድን ቋንቋና ባህል ካለደነቀ ብቻህን ከመሰሎችህ ጋር ብትዘፍን አበው እንደሚሉት ” በሰው ሃገር የከበረና ጫካ ገብቶ የዘፈነ አንድ ናቸው” አይነት ነው። ህብረ ብሄራዊነት ያለ ክልል፤ ሰው በፈለገው እንደ ፈለገው ተንቀሳቅሶ የመኖር፤ የመስራት፤ የመማር መብት በምድሪቱ ላይ እስካልሰፈነ ድረስ የወያኔ ግባአተ መሬት ብቻውን ለምድሪቱ ሰላም አያመጣም። ሞታቸው አስተሳሰባቸውን፤ የቀበሩትን የክፋት ፈንጂ ሁሉ አፈነዳድቶና በእነርሱ የተበከሉ የዘርና የቋንቋ ሰልፈኞችን እስካላስወገደ ድረስ ችግሩ ራሱን ይደግማል። ግን የወያኔ ሞትና የመቃብር ስፍራ ለሌሎችም ስፍራ አዘጋጅ በመሆኑ የተገኘው ድል ከሁሉ በላይ ለትግራይ ህዝብ ጠቃሚ ነው። ደህና ሁን አንድ ላምስት፡ ደህና ሁን ወያኔ ሁሌ የውሸት ቋት። እፎይ እስቲ ምድሪቱ ከግርግር ትረፍ። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule