• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው

January 14, 2021 01:37 pm by Editor 1 Comment

“ስብሃትን “አቦይ” አልላቸውም … እንዲህ ዓይነት አባት አልመኝም” ጄኔራል ባጫ

የጁንታው ፈጣሪና መሪ ስብሃት ነጋ በመከላከያ ሰራዊትና በፌዴራል ፖሊስ በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ በተለቀቀው ተንቀሳቃሽ ምስልና ፎቶ ሲስቁ ታይተዋል። በርካቶችም ስብሃት ምን አሉ በሚል ሲነጋገሩ ነበር።

ሌፍተናንት ጄኔራል ባጫ ደበሌ እንደገለጹት ስብሃት ከተያዙ በኋላ አስተያየት ሰጥተዋል። ስብሃት በተያዙበት ሰዓት ለከፍተኛ የመከላከያ መኮንኖች፣ “እኛ እኮ ከሞትን ቆይተናል“ የሚል አስተያየት እንደሰጡ ሌ/ጄኔራል ባጫ ደበሌ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።

ስብሃት ከመያዛቸው አስቀድሞ “ቢያዙ ምን ይሉ ይሆን“ ብለው ጄነራሎቹ ይወያዩ እንደነበር የገለጹት ሌፍተናንት ጄነራል ባጫ “ግለሰቡ ቢያዙ ሕገ መንግሥቱ ጥሩ ነው ፤ ሕገ መንግሥቱ እንደዚህ ነው… ብለው ነው የሚያወሩት” የሚል ግምት በጄኔራሎቹ ሀሳብ እንደነበር ተናግረዋል።

ስብሃት ከተያዙ በኋላም እንደተገመተው፣ አንደኛው ጄኔራል ሲያናግሯቸው “ሕገ መንግሥቱ ጥሩ ነው፤ ተወያዩበት“ እያሉ ሲያወሩ እንደነበር የምዕራብ ዕዝ አዛዥ እንደገለጹላቸው ሌፍተናንት ጄነራል ባጫ ገልጸዋል።

ሌ/ጄኔራል ባጫ ተጫዋች ያሉት የምዕራብ ዕዝ አዛዥ መሰለ ስብሃትን “ስለ ሕገ መንግሥቱ ተወውና አንተ እስኪ ምን ይሰማሃል “ብሎ እንደጠየቋቸው ተናግረዋል። ስብሃት ሲመልሱ “እኔ የሚሰማኝ እኛ ከሞትን እኮ ቆይተናል” የሚል ነው።

“መቼ ነው የሞታችሁት?” የሚል ጥያቄ እንደተነሳላቸው ያስታወቁት ሌ/ጄነራል ባጫ “እኛ የሞትነውማ ኢህአዴግ የሚባለው የጠፋ ጊዜ ነው፤ አሁን የምታደርጉት ምን እንደሆነ ልንገርህ? አሁን እያደረጋችሁ ያላችሁት የቀብር ሥነ ሥነስርዓታችን እየፈጸማችሁ ነው“ ሲሉ ስብሃት ነጋ መመለሳቸውን አንስተዋል።

የጄኔራል ባጫ ንግግር ከዚህ በታች ይገኛል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: meles zenawi, operation dismantle tplf, sibhat, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    January 15, 2021 03:58 pm at 3:58 pm

    መቸውንም ቢሆን ወያኔ ማለት የተንኮል ማሰሮ ማለት ነው። የሚገርመው ግን የሰሜን እዝ ነው። ተደመሰሱ፤ ተያዙ፤ ሞቱ፤ ገደል ገቡ ይሉናል። እሺ ይሁን ገደል ይግቡ ብለን ስንጠብቅ ለሞት አንድ ቀን የቀረውን የወያኔ ቁንጮና የክፋት ውቅያኖስ ስብሃት ነጋን በቃሬዛ ወደ አዲስ አበባ ማምጣት ምን የሚሉት ነገር ነው? የቀድሞው የትግራይ ክልል ፕሬዚዳንት አያሌ ግፎችን የፈጸመ የወያኔን ትዕዛዝ ፈጻሚ ግፍን በግፍ ላይ የተላበሰ የቁም በድን ነው። አሁን ወያኔ ድል አድርጎ ወታደራዊ መሪዎችን ማርኮና ይዞ ቢሆን ኑሮ በድናቸው በመቀሌ አስፓልት እንደሚጎተት ጭራሽ አያጠራጥርም። ጉድ ያደረጋቸው ከግብጽና ከሱዳን ጋር የገቡት የጦርነት ቀን መማታቱ ነው። ለዛ ነው ሱዳን በመሬት አሳባ ወያኔ የሰሜንን እዝ ባጠቃ በሳምንቱ መሬት ቀምቼ ያዝኩ በማለት የደነፋቸው። በግብጽ፤ በአስመራ፤ በደቡብ ሱዳን የመከረው ጄ/አብዱልፋታህ አልቡርሃን ልቡ የደነደነ፤ እጅ በደም የታጠበ የውጭ ሃሎች መጠቀሚያ ሰው ነው። አሁን ማን ይሙት ሱዳን በጎረቤት ሃገር ላይ ጦርነት የምትከፍትበት ጊዜ ነው? ሱዳን የሚበላ የጠፋበት፤ ኑሮና የዲሞክራሲ ጥማት ያስመረረው ወጣት በሰልፍና በተቃውሞ ምድሪቱን የሚያናውጥበት ያልተረጋጋ መንግስት የቆመላት በግብጽ እንደ ጀልባ የምትገፋ ሃገር ናት። ግን የወያኔም ሆነ የሱዳን ጦርነት መክፈት ለግብጽ የህዳሴ ግድቡን ለማጥቃት እንዲያመቻት የተሰላ ሂሳብ ነው። አቅጣጫ ማስቀየሪያ ስልት። ከዚያ ቀደም ብሎ የተደረገው የጦር ልምምድም ከዚሁ ጋር የተያያዘ ነው። በቤኒሻንጉልና ጉምዝ፤ በመተከልና በወለጋ አማራን ብቻ ለይቶ የማጥቃቱም ብልሃት የተነደፈው ከእነዚህ ሃይሎች ነው።
    አሁን በቅርቡ ከገዳሪፍ የደረሰኝ ጥቆማ እንደሚያስረዳው ከየስፍራው አምልጠው ወደ ሱዳን የገቡት የወያኔ ስመ ጄኔራሎችና ባለሌላ ማእረጎች አብረው ከሱዳን ጦር ጎን እንደተሰለፉ የአይን እማኝ ነግሮኛል። በአማካሪነት ደግሞ የግብጽ ሰዎች በቅርብና በሩቅ እንዳሉበት ተደርሶበታል። በዚህም የተነሳ ለኢትዮጵያ እየሰለላችሁ ነው በማለት ብዙ ሃበሾችን ሰብስበው አስረዋል። በትግራይ ተቆርጦ ቀረ የተባለው ጦር ከየስርቻው እየተጠራራ በመሰባሰብ ውጊያ ከፍቶ ችግር እንደፈጠረ ሰምተናል። ወደ 200 ሺህ ሰራዊት አለን ይሉን የነበሩት የክልሉ መሪ ደብረጽዪንና የክፋቱ ኮሮጆዎች ሁለቱ ጌታቸው ደርሰንባቸዋል፤ ተከበዋል፤ ሽማግሌ ልከናል ወዘተ የሚለው ዋጋ የለሽ ወሬ ያሰለቻል። ባለ በሌለ ሃይል ሳይውል ሳያድር ካልተደመሰሱ በስተቀር በራሱ ጥላ ለሚደነብረው ታፍኖ የኖረ ህዝብ እፎይታ አይሰጥም። ይባል አልነበረ ስብሃት ነጋ አፋፍ ላይ ደርሷል? እሱ እንኳን አፋፍ ሊወጣ ተደግፎም መራመድ እንደተሳነው የታመነው ተይዞ ከታየ በህዋላ ነው።
    የአለም የፓለቲካ ንፋስ ቅጡ ጠፍቶታል። ትላንት አለምን ስለ ዲሞክራሲ እናስተምራለን ይሉን የነበሩት አሜሪካኖች በታሪካቸው ታይቶ በማይታወቅ ሃገር በቀል ሽብር ታምሰዋል፤ ገናም ይታመሳሉ። እብዶች ስልጣን ሲጨብጡ የሚሉን ለሃገር ለወገን ነው ይሉና እርስ በእርስ ያጫርሳሉ። የአሜሪካም እድል ፈንታ ገና አለየለትም። ተምረናል፤ አውቀናል፤ ለሃገራችን ቁመናል የሚሉ የህዝብ ተወካዪች በፓርቲ ከለላ ከውሸት ጋር ሲቆሙ ማየት አሜሪካ ሂትለርን ልትመርጥ የቀራት አንድ እርምጃ ብቻ ነው። ሌላው ሁሉ ተንጋሎ መትፋት ነው። ጉረኛውና በውሸት ብቻ ያለምንም መረጃ አራት አመት ሙሉ አለምንና አሜሪካን እያመሰ ያለው ዶናልድ ትራምፕ በዪክሬን ሰበብ መጀመሪያ ላይ ከስልጣን ወርዶ ቢሆን ኑሮ ዛሬ ይህ ሁሉ ችግር ባልተፈጠረ ነበር። ግን የፓለቲካና የቡድን ጽዋ የጨለጡት እውነትን በውሸት ለውጠው ስለታደጉት ዛሬ ለተፈጠረው የከፋ ችግር መንገድ ጠራጊ ሆኗል። ያለምንም መረጃ ስፓንሽ ሳህራ (ሳህራዊ) ለሞሮኮ፤ በሱዳን፤ በባህረ ሰላጤው ሃገራት ሰላምን አመጣሁ እስራኤልና የአረብ ሃገሮች ሰላም ፈጠሩ የሚባለው ሁሉ ለጊዜ ፍጆታ እንጂ በአንድ ጀምበር የሚፈርስ የእንቧይ ካብ ነው። ለፓለቲካ ፍጆታ የተነፋ ጥሩንባ! ቱርክ ሃይሏን አንሰራርታ ከአውሮፓ እስከ አፍሪቃ እኔን ስሙኝ ስትል፤ ቻይና በኢኮኖሚ ጥቅማ ጥቅም አሳባ አፍሪቃን በእጇ አስገብታለች። ወደ 55 ሃገሮች ያሉበት የአፍሪቃ አህጉር እንደ ቀድሞው አሁንም የቀጥታና የእጅ አዙር ሃይሎች የሚቀራመቱት ምድር ሆኗል።
    አቶ ስብሃት እንዳለው “ከሞትን ቆይተናል” ነውና ዛሬ በሃጉሩ ውስጥ ለመኖር ባለመቻላቸው በየመንገድ፤ በየባህሩ ጉዞ ከሞት ተርፈው፤ በየሰው ቤት በግድና በውድ የባርነት ኑሮ የሚኖሩ እህትና ወንድሞቻችን እልፍ ናቸው። እኛም ለዘመናት ስንጠላለፍ ካለንበር ኑሮ እልፍ ሳንል በየክልላችን ባንዲራ እናውለበልባለን። ሲያሳዝን። ሰው በሰው የጭቃ ቤት ቀንቶ እሳት የሚለኩስበት፤ ከክልሌ ውጣ ብሎ አንገት ከሚቆርጥበት ምድር ላይ ቆመን ሽምግልና፤ ልመና፤ ፍትህ ወዘተ ስንል እገረማለሁ። ባጭሩ ሥራ በልብ ነበር። አሁን ግን ሁሉ ነገር በቴሌቪዝን መስኮት ላይ ሆኖ መለፍለፍ ነው። ምን አለበት ሁሉም ነገር ሲጠናቀቅ ቢወራ? ደግሞስ ተደመሰሱ ስትሉን ከእናንተ ጎን የሞተ የለም ማለት ነውን? የማይታመን ነገር? በጦርነት መካከል ቀዳሚ ሟች እውነት ስለሆነች ሁሉንም ነገር ፈትሾና አመሳክሮ ካልሆነ በስተቀር የተሰማውንና የታየውን ሁሉ ሳያልሙ መሰልቀጥ ማወራረጃ ፍለጋ ይሰዳል። አሁን ስዪም መስፍን ሞቷል ተብሏል፡ ቆሞ ሲሄድ ቢታይ የሚቀጥለውን ወሬ የሚታመን ያደርገዋል። ያው እሱ በህይወት እያለ “ባድመ ለእኛ ተፈረደ” እንዳለው አይነት አማች ዜና። እኔ እማዝነው ለተሰላፊዎች፤ ከበሮ እየመቱ ለሚዘፍኑ፤ ትላንትም ዛሬም በሰው ሞት እልል ለሚሉ። ማብቂያው መቼ ነው? ለምንስ እንገዳደላለን? አሁን እውነት ሱዳን በኢትዮጵያ ላይ ጦርነቱ እንዲቀናት የሚጽፉና የሚናገሩ ሰዎች ጤነኞች ናቸው? ለዛ ነው የጥቁር ህዝብ መከራ ይበልጡ የሚመነጨው ከራሳችን ነው የምለው። አይ ሃገር እንዲህ ነው ሲገሉ፤ ሲገዳደሉ፤ በሰው እንባ ክራር እየመቱ ሲጨፍሩ መኖር። ዘርፎና አዘርፎ መኖር። ያለፈው ክፉ ነው እያሉ የዛሬውን የባሰ ሲኦል ማድረግ። እንዲህ ናት ለውጥ… ድንቄም። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule