• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሓት ተሠረዘ!!!

January 18, 2021 01:32 pm by Editor 1 Comment

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በህግ ከተቋቋመባቸው ዋና ዋና ተግባራት አንዱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ድጋፍ፥ ቁጥጥር እና ክትትል ነው። በመሆኑም በምርጫ እና የፖለቲካ ፓርቲዎች አዋጅ ቁጥር 1162/2011 መሰረት ፓርቲዎች የተለያዩ መስፈርቶችን ማሟላታቸውን ክትትል ሲያደርግ ቆይቷል።

በዚህም መሰረት ቀደም ብሎ መስፈርት አሟልተው ምዝገባቸው የተጠናቀቀ እና በሂደት ላይ ያሉ ፓርቲዎች ዝርዝርን ማሳወቁ ይታወሳል። ቦርዱ ከዚህ ቀደም ውሳኔ ያልሰጠባቸው እንዲሁም የተጠየቁትን ማብራሪያዎች ያቀረቡ ፓርቲዎችን አስመልክቶ የሚከተሉትን ውሳኔዎች አስተላልፏል።

1. ቦርዱ ህዝባዊ ወያነ ሐርነት ትግራይ (ሕወሃት) የአመጻ ተግባር ላይ ተሰማርቷል ወይ የሚለውን ሁኔታ ለማጣራት በፓርቲው የተሰጡ መግለጫዎችን እና በይፋ የሚታወቁ ጥሬ ሃቆችን በማቅረብ ፓርቲው ኃይልን መሠረት ያደረገ የአመጻ ተግባር ላይ መሣተፉን አረጋግጧል። በተጨማሪም ፓርቲው መልስ የመስጠት እድል እንዲኖረው በማሰብ በፓርቲው እና በቦርዱ መካከል አገናኝ በመሆን ይሰሩ የነበሩትን የፓርቲውን የአዲስ አበባ ቢሮ የቀድሞ ተወካይ ለማነጋገር ጥረት ያደረገ ሲሆን ተወካዮም ፓርቲውን መወከል እንደማይችሉ ገልጸዋል። በመሆኑም፦

ሀ. በአዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 98/1//4/ መሠረት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፓርቲውን ህጋዊ ሰውነት ሰርዞታል። በዚሁ አዋጅ አንቀጽ 99 መሠረት የፓርቲው ኃላፊዎች በፓርቲው ስም መንቀሳቀስ እንደማይችሉም ውሳኔ አስተላልፏል።

ለ. የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ አቃቤ ህግ በፓርቲው እና በፓርቲው አመራሮች ላይ በሚያደርገው ምርመራ የሚገኙ በህወሐት ሥም የተመዘገቡ ተንቀሳቃሽና የማይንቀሳቀስ ንብረቶችን በተመለከተ ያገኘውን ዝርዝር መረጃ እንዲልክ ቦርዱ ጥያቄ አቅርቧል።

ሐ. የፓርቲው ንብረት በአዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 99/2/ መሠረት ንብረቱ ተጣርቶ ዕዳ ካለበት ለዕዳው መሸፈኛ እንዲውል፤ ይሁንና እዳውን ሸፍኖ የሚተርፍ ንብረት ከተገኘ ቀሪው ገንዘብና ንብረት በዚሁ አዋጅ አንቀጽ 99/3/ መሠረት ለሥነ ዜጋና መራጮች ትምህርት እንዲውል ቦርዱ ወስኗል። (ምንጭ የምርጫ ቦርድ ፌስቡክ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: meles zenawi, operation dismantle tplf, sibhat, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    January 20, 2021 09:16 am at 9:16 am

    በቅርቡ ከአንድ የትግራይ ተወላጅ ጓደኛዬ ጋር (አባቱን ወያኔ የገደለበት) ሰፋ ያለ ጫወታ ስንጫወት የትግራይ ህዝብና ወያኔ አንድ አይደሉም አለኝ። አይ ናቸው አልኩት። በጋለ የሃሳብ ንትርክ መካከል እንዲህ ብየ ጠየኩት። 45 ዓመት ሲቀልድበት የኖረን አንድ ድርጅት ያልተቃወመ ህዝብ እንዴት ነው ወያኔ አፍቃሪ አይደለም የምትለው ስለው። ኦ አሁን ራሴን አሳመምከኝ። ሰሞኑን ሃገር ቤት ደውዬ ነበርና ስንጫወት አንድ ወያኔ ይሻለናል አሁን ከሚደረገው ነገር ቢለኝ እንዴ እንዴት እንዲህ ትላለህ ስለው “ያው የዘረፉትን ዘርፈው የቀረውን በልተን እንድናደር ይበቃ ነበር አሁን ጭራዙን ጾም አዳሪዎች ሆንን” በማለት መለሰልኝና የለሆሳስ ወሬውን ጉልበቱ እንደራደው ሰው ጨርሶ አወራኝና አትሰማኝም ጮክ ብለህ ተናገር እያልኩ በዚያው ተቋረጠ። ሌላ ጥሪ መቶበት ይሆናል። አይ ጊዜ! ጊዜ ወልጋዳ ነው። እስቲ የሰሜኑን ጦር ወያኔ በሸር ከውስጥና ከውጭ ካጠቃው በህዋላ ያለውን ጉዳይ ከዓይን እማኞች እኔ ራሴ ያሰባሰብኩትን ላጫውታችሁ እና መንግስትን ወረፍ አርጌ ሃሳቤን አጠቃልላለሁ።
    የአይን ምስክር – በብዙ መቶ የምንቆጠር የበታችንና የበላይ መኮንኖች በእግር ጉዞ እንደ ቀንድ ከብት እየተገፋን እንጓዛለን። በዚህ መካከል ተቀመጡ ተባለና በረድፍ በረድፍ ሆነን ተቀመጥን። ድንገት ሳናስበው አንድ የወያኔ ታጣቂ ከተቀመጥነው መካከል አንተ ውጣ። አንቺ ውጪ እያለ እያስወጣ ከተቀመጥነው ፊት ለፊት አስቆማቸው። እነዚህ አማራ ይመስላሉ በማለት በሩምታ ተኩስ ሁሉንም ገደሏቸው። ይህን ያጫወተኝ አንድ ሻለቃ ነው፡፤ አሁን ስራው ላይ ተመልሶአል። ከዚያ እኛም ይህ አይቀርልንም በማለት 15 የምንሆን አመለጥን ይላል ሻለቃው። ገበሬዎች አይተውን ኑረው ሄደው ይናገሩ እና በዚህም በዚያም ከበው ተከፋፍለን ስንሄድ ስለነበር ከፊታችን የቀደሙትን በመያዝ 7 ቱን ረሸኗቸው፡ ገበሬው የእኛን ቡድን ስላላዪ ያመላከቷቸው እነርሱን ብቻ በመሆኑ እኛ ተፍጨርጭረን ለመትረፍ በቃን በማለት በሲቃ አጫውቶኛል። በእኔ እምነት የትግራይ ህዝብና ወያኔ አንድ ናቸው። ዝም ብሎ ለፓለቲካ ፍጆታ አይደሉም የሚባለው። ይህ አባባል በተግባር ያልተመሰከረ የቀበሌ ጡርንባ ነው። ይህ ሲባል ቅን አስተዋይ፤ ሃገራቸውን የሚወድ፤ ለእምነታቸው የሚያድሩ፤ የትግራይ ተወላጆች የሉም ማለት አይደለም። በ 45 ዓመቱ የገደልና የከተማ ትግል ውስጥ ከሞት የተረፉትንና ከወያኔ ቁራሽ ተካፍይ የሆኑትን ጨምሮ ይህ ድርጅት ከተፈጠረ በህዋላ የተወለድት ሁሉ ጭራሽ ብሄራዊ ወይም አለም አቀፋዊ እይታ የላቸውም። ለዚህ ነው ዛሬ በትግራይ በሴራ የተደበደበውን ጦር እንደ ጠላት የሚቆጥሩት። ወያኔ ያጠፋውና የሚያበላሸው ሁሉ ለአፍቃሪ ወያኔዎችና ስለ ትግራይ ብቻ ለሚያስቡ ጠባቦች ጥፋት አይደለም። አጭዶ፤ ት/ቤት ሰርቶ/አንበጣ አባሮ፤ ተጋብቶና ተዛምዶ ለዘመናት የኖረውን የሰሜን ጦር ከውስጥና ከውጭ ወያኔ ሲያጠቃው፤ ሰዎች በዘራቸው እየተለዪ ሲረሸኑ ለምን ብሎ የጠየቀ የለም። ባጭሩ ምድሪቱ በወያኔ የክፋት ፓለቲካ የተበከለች ናት። 45 ዓመት ስለ ትግራይና ለትግራይ እያለ ከበሮ ይዞ ይዘል የነበረ ድርጅት ከሥሩ ሲመነገል እንዴት ነው የትግራይ ህዝብ በወር ብቻ ረሃብተኛ የሚሆነው? የታለ የምግብ ዋስትናው እቅድና ፕላን? አሁን በመቀሌና በዙሪያዋ የወታደሩን እንቅስቃሴ ለወያኔ ትራፊ ታጣቂዎች እየጠቆሙ የሚያስገድሏቸው እነማን ናቸው? መንግሥትስ እከሌን ከገደል አወጣን እያሉ ወሬ ከመንዛት ሞቱ፤ ተደመሰሱ ያልናቸው ሳናስበው ተኩስ ከፍተው ይህን ያህል ወታደሮች ገደሉብን ለማለት እንዴት ይሳነዋል? የዚህ ሁሉ ሴራና ገመና ዋንኛ ተዋናዪች መሳሪያ አስረክበናል ያሉ፤ የሚሊሻ፤ የፌዴራልና የክልል የጸጥታ ሃይል መለዪ የለበሱ የወያኔ ተባባሪዎች ለመሆናቸው ምስክር አያሻም። በመቀሌ ከተማና በዙሪያዋ በመሳሪያ የታገዘ ግድያ፤ ዝርፊያ፤ ሴት መድፈር፤ ማፈን የሚያካሄድት የወታደር ልብስ ለብሰው ድምጽ በማያሰማ መሳሪያ እየታገዙ ነው። ይህ ደግሞ ለወያኔ ይኸው እኛ ከሌለን ህግና ሰላም ፈረሰ ለማለት አማራውን በሌሎቹ ክልል እንዲጨፈጨፍ በማቀድ ከሚያካሂድት እቅድ ጋር ይያያዛል። በወገኑ ደም የሚነግደው ወያኔ በዶ/ር አብይ መንግስት ሁሌ መቆላመጡ ግራ ያጋባኛል። የገደለ፤ ሃገር ያፈረሰ፤ በዘርና በጎሳ ሃገር ቆራርጦ እኔን ብቻ እዩኝ ያለ ድርጅት መደምሰስ አለበት። እጅ ስጡ፤ በሰላም ኑሩ የሚለው ጥሪ ሁሉ ለወያኔ የፍርሃት ምልክት እንጂ ሌላ መስሎ አይታየውም። በየጊዜው ይህን ገደልን፤ ያን ያዝን እዚህ ጋ ተደመሰሱ የሚባለው ነገር ሁሉ ለይደር ቢቆይ መልካም ነው። የተያዘም፤ የሞተም፤ የፈረጠጠም፤ በውጭ ሃገር ሆነው አይዞህ የሚሉትም፤ ከሱዳን ጎን ተሰልፈው ወረራ የሚያደርጉትን ሁሉ ለይቶ በመያዝና በማወቅ በመረጃ ሁሉንም አፈር ካለበሱ በህዋላ ነው ኦሮማይ ማለት እንጂ እንዲህ የነጠብጣብ ወሬ ማናፈስ ወያኔ የራሱን የስለላ መረብ ለመቀጠል ይረዳዋል እንጂ ግፍ ለደረሰበት የወገን ጦር የሚጠቅም ፋይዳ የለውም። ሙያ በልብ ነው ይሉ የለ አበው።
    በመጨረሻም ምንም ይሁን ምንም አንድ ህዝብ ሰላምን የሚሻው ራሱ ሲሻና ሲፈልግ እንጂ በሌላ ሃይል ተገዶ ወይም ተገፍቶ እንዳልሆነ ታሪክ ያስተምረናል። ጠበንጃ ማንገትን እንደ ቁም ነገር የሚቆጥር ትውልድ፤ ወንድምና እህቱን በዘርና በቋንቋ መዝኖ አንገት የሚቀላ ፍጡር ስለ ሰላም ያስባል ብሎ ማመን ጅልነት ነው። የመጽሃፉ አር ዕስት ተረሳኝ እንጂ አንድ የቀድሞ ሰው የጻፉት ያ መጽሃፍ ስለ ሃበሻው የፓለቲካ ፍትጊያ ይተነትናል። በመዝጊያው እንዲህ የሚለው ቃል ትዝ ይለኛል “ሲገድሉም ሲገዳደሉም ኖሩ” ይላል። ለዛ ነው ውጭ ሃገር ላይ ቁጭ ብለው በስማ በለው ፓለቲካ በዘሩና በቋንቋው ሰክሮ ሰው እንዲጫረስ የውሸት ፕሮፓጋንዳ ሲነዙ የሚውሉት። ያሰለቻል። ሰው እንዴት እድሜ ልኩን ያዘው ጥለፈው ሲል ይኖራል? አባካችሁ እናንተ መንግስት ነን የምትሉ ከማይክሮፎንና ከሚዲያ መስኮቶች ራቁ፤ ሞቱ፤ ተያዙ፤ ተገደሉ፤ ተደመሰሱ አትበሉን። ስራችሁን ስሩና ከእናንተም የሞተውን፤ ወያኔ በዚያች ሰአት ያደረሰውን የንበረት ውድመትና የሰው ህይወት ጥፋት ከተረፉት ሰዎች በመረዳት፤ ሌሎች መረጃዎችንም በማከል በመጽሃፍ መልክ ብታወጡት የተሻለ ይሆናል። ሌላው ሁሉ ነገር በማሰሮ ውስጥ አስገቡትና እዚያው ይብላላ። የፈጠራም ሆነ እውነት ነክ ወሬ ስልችቶናል። የህዝባችንን እንባ አስቁሙ። ያ ነው ጀግንነት። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule