• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለትምህርት እንዲሆነን

January 11, 2021 01:20 pm by Editor Leave a Comment

ታላቁ መጽሐፍ የተጻፈበትን ምክንያት ሐዋርያው ጳውሎስ ሲናገር “የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር” ተጻፈ ይላል።

በአገራችን የፖለቲካ ታሪክ እጅግ ዘግናኝ ጊዜያት አሳልፈናል። በሥልጣን የተቀመጠ የሚወርድ እስከማይመስለውና ሰብዓዊነቱን እስኪዘነጋ ድረስ ሕዝብን ሲበድል ይኖራል። የሕይወቱ መጽሐፍ ሲጠናቀቅ ይሰናበታል። ስንብቱ ግን በአሰቃቂና አሳፋሪ ሁኔታ ሲሆን መመልከቱ በየዘመናቱ የመሰከርነው ሐቅ ነው።

ንጉሡ በደርግ ሲተኩ፤ ደርግ “ለለውጥ ባጎፈረው” ህወሓት ሲተካ፤ አሁን ደግሞ አይደረስብንም፣ አንበገርም፣ እንደ ደርግ አንሆንም፣ ዓቅምም፣ ገንዘብም፣ ሁሉም ነገር አለን ሲል የነበረው በረኸኛው የወንበዴ ጥርቅም ከየጉድጓዱና ሰርጡ እንደ አውሬ እየተፈለገ ሲወጣ አየን። መቼ ነው የምንማረው?

የሥልጣኑን ጫፍ የተቆናጠጡት ዘመነኞች ከዚህ ትምህርት ቢወስዱ መልካም ነው። ሰብዓዊነት ዘላለማዊነት አይሆንም፤ ሆኖ አያውቅም፤ ለመሆንም አይችልም። ሥልጣን በየትኛውም የሤራ ጥበብ ቢታቀድ፣ የትኛውንም ዓይነት የገንዘብና የጦር መሣሪያ ብቃት ላይ ቢደረስ ማብቂያው ይመጣል። ጉዳዩ እንዴት ያልቃል የሚለው ላይ ነው።

ትምህርት መውሰዱ የሚጠቅመው ለዚህ ነው። ቀድመው ያልዘሩት ለከርሞ አይበቅልም። አስቀድሞ ያልተሰራ በጎነት ከጃርት ጉድጓድ ሲገኙና ከገደል ሥር ተጎትተው ሲወጡ በድንገት ሐዘኔታን አይፈጥርም። ዕድሜና ጉስቁልና ፍትሕንም እንዲያሳንስ ወይም እንዲያዛባ ሊፈቀድለትም አይገባም። ስለዚህ ከታች ከቀበሌ ካለው ሥልጣን እስከ ማማው ድረስ አሁን ያሉት ሊገነዘቡ የሚገባው ሁሉም ወደ ማብቂያው ይመጣል። አስተላለቁ እንዴት ይሆናል የሚለው ነው።

ጧሪ አንድ ልጃቸውን ብቻ ሳይሆን በርካታ ልጆች ካንድ ቤት ያጡ ወላጆች፤ በየሜዳው ተጥለው ጠያቂ የሌላቸው የግፍ ሰለባዎች፤ ደማቸው በየጉድጓዱ ተደፍቶ የቀረው፤ ተገቢው ቀብር ያልተደረገላቸው ሥፍር ቁጥር የሌላቸው፤ የታረዱ፣ ከሞታቸው አልፎ ክብራቸውን የተነፈጉ፤ ስብዕናቸው የተዋረደው፤ ወጥቶ የመግባት መሠረታዊ መብት ተነፍገው እንደወጡ የቀሩ፤ ወዘተ ለእነዚህ ፍትሕ ሳይመጣ በወንጀል የጠገቡ የዕድሜና ጉስቁልናቸው ታይቶ ምህረት ይደረግላቸው የሚባል አስተሳሰብ፤ አሁን ያላችሁትም ከዚህ ምንም ትምህርት አትውሰዱ፤ አሁን የፈለጋችሁትን አድርጉና ስትያዙ እንዲሁ ይቅርታ ይጠየቅላችኋል በማለት ግፍንና ወንጀልን ማደፋፈር ነው። ትምህርት የሚገኘው ካለፈው፣ አሁን ካለውና ከፍትህ ነው። ይህ በሙላት ተከሽኖ ለትውልድ ሲቀመጥ ትምህርቱ ምሉዕ ይሆናል። ስለዚህ ለበጎ ሥራ በመዘጋጀት ቅን ልብ ኖሮን ለራሳችንም ለወገንም ጥቅም መስጠት እንድንችል ከዚህ እጅግ አስከፊ ውድቀት ትምህርት እንውሰድ። ሰሚ ጆሮ ያለው የዘመኑ ሹመኛ ይስማ!

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ™” አቋም ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial, Middle Column Tagged With: derg, getachew assefa, hailesillasie, meles zenawi, operation dismantle tplf, sebhat nega, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule