• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለትምህርት እንዲሆነን

January 11, 2021 01:20 pm by Editor Leave a Comment

ታላቁ መጽሐፍ የተጻፈበትን ምክንያት ሐዋርያው ጳውሎስ ሲናገር “የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር” ተጻፈ ይላል።

በአገራችን የፖለቲካ ታሪክ እጅግ ዘግናኝ ጊዜያት አሳልፈናል። በሥልጣን የተቀመጠ የሚወርድ እስከማይመስለውና ሰብዓዊነቱን እስኪዘነጋ ድረስ ሕዝብን ሲበድል ይኖራል። የሕይወቱ መጽሐፍ ሲጠናቀቅ ይሰናበታል። ስንብቱ ግን በአሰቃቂና አሳፋሪ ሁኔታ ሲሆን መመልከቱ በየዘመናቱ የመሰከርነው ሐቅ ነው።

ንጉሡ በደርግ ሲተኩ፤ ደርግ “ለለውጥ ባጎፈረው” ህወሓት ሲተካ፤ አሁን ደግሞ አይደረስብንም፣ አንበገርም፣ እንደ ደርግ አንሆንም፣ ዓቅምም፣ ገንዘብም፣ ሁሉም ነገር አለን ሲል የነበረው በረኸኛው የወንበዴ ጥርቅም ከየጉድጓዱና ሰርጡ እንደ አውሬ እየተፈለገ ሲወጣ አየን። መቼ ነው የምንማረው?

የሥልጣኑን ጫፍ የተቆናጠጡት ዘመነኞች ከዚህ ትምህርት ቢወስዱ መልካም ነው። ሰብዓዊነት ዘላለማዊነት አይሆንም፤ ሆኖ አያውቅም፤ ለመሆንም አይችልም። ሥልጣን በየትኛውም የሤራ ጥበብ ቢታቀድ፣ የትኛውንም ዓይነት የገንዘብና የጦር መሣሪያ ብቃት ላይ ቢደረስ ማብቂያው ይመጣል። ጉዳዩ እንዴት ያልቃል የሚለው ላይ ነው።

ትምህርት መውሰዱ የሚጠቅመው ለዚህ ነው። ቀድመው ያልዘሩት ለከርሞ አይበቅልም። አስቀድሞ ያልተሰራ በጎነት ከጃርት ጉድጓድ ሲገኙና ከገደል ሥር ተጎትተው ሲወጡ በድንገት ሐዘኔታን አይፈጥርም። ዕድሜና ጉስቁልና ፍትሕንም እንዲያሳንስ ወይም እንዲያዛባ ሊፈቀድለትም አይገባም። ስለዚህ ከታች ከቀበሌ ካለው ሥልጣን እስከ ማማው ድረስ አሁን ያሉት ሊገነዘቡ የሚገባው ሁሉም ወደ ማብቂያው ይመጣል። አስተላለቁ እንዴት ይሆናል የሚለው ነው።

ጧሪ አንድ ልጃቸውን ብቻ ሳይሆን በርካታ ልጆች ካንድ ቤት ያጡ ወላጆች፤ በየሜዳው ተጥለው ጠያቂ የሌላቸው የግፍ ሰለባዎች፤ ደማቸው በየጉድጓዱ ተደፍቶ የቀረው፤ ተገቢው ቀብር ያልተደረገላቸው ሥፍር ቁጥር የሌላቸው፤ የታረዱ፣ ከሞታቸው አልፎ ክብራቸውን የተነፈጉ፤ ስብዕናቸው የተዋረደው፤ ወጥቶ የመግባት መሠረታዊ መብት ተነፍገው እንደወጡ የቀሩ፤ ወዘተ ለእነዚህ ፍትሕ ሳይመጣ በወንጀል የጠገቡ የዕድሜና ጉስቁልናቸው ታይቶ ምህረት ይደረግላቸው የሚባል አስተሳሰብ፤ አሁን ያላችሁትም ከዚህ ምንም ትምህርት አትውሰዱ፤ አሁን የፈለጋችሁትን አድርጉና ስትያዙ እንዲሁ ይቅርታ ይጠየቅላችኋል በማለት ግፍንና ወንጀልን ማደፋፈር ነው። ትምህርት የሚገኘው ካለፈው፣ አሁን ካለውና ከፍትህ ነው። ይህ በሙላት ተከሽኖ ለትውልድ ሲቀመጥ ትምህርቱ ምሉዕ ይሆናል። ስለዚህ ለበጎ ሥራ በመዘጋጀት ቅን ልብ ኖሮን ለራሳችንም ለወገንም ጥቅም መስጠት እንድንችል ከዚህ እጅግ አስከፊ ውድቀት ትምህርት እንውሰድ። ሰሚ ጆሮ ያለው የዘመኑ ሹመኛ ይስማ!

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ™” አቋም ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Editorial, Middle Column Tagged With: derg, getachew assefa, hailesillasie, meles zenawi, operation dismantle tplf, sebhat nega, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule