• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለትምህርት እንዲሆነን

January 11, 2021 01:20 pm by Editor Leave a Comment

ታላቁ መጽሐፍ የተጻፈበትን ምክንያት ሐዋርያው ጳውሎስ ሲናገር “የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር” ተጻፈ ይላል።

በአገራችን የፖለቲካ ታሪክ እጅግ ዘግናኝ ጊዜያት አሳልፈናል። በሥልጣን የተቀመጠ የሚወርድ እስከማይመስለውና ሰብዓዊነቱን እስኪዘነጋ ድረስ ሕዝብን ሲበድል ይኖራል። የሕይወቱ መጽሐፍ ሲጠናቀቅ ይሰናበታል። ስንብቱ ግን በአሰቃቂና አሳፋሪ ሁኔታ ሲሆን መመልከቱ በየዘመናቱ የመሰከርነው ሐቅ ነው።

ንጉሡ በደርግ ሲተኩ፤ ደርግ “ለለውጥ ባጎፈረው” ህወሓት ሲተካ፤ አሁን ደግሞ አይደረስብንም፣ አንበገርም፣ እንደ ደርግ አንሆንም፣ ዓቅምም፣ ገንዘብም፣ ሁሉም ነገር አለን ሲል የነበረው በረኸኛው የወንበዴ ጥርቅም ከየጉድጓዱና ሰርጡ እንደ አውሬ እየተፈለገ ሲወጣ አየን። መቼ ነው የምንማረው?

የሥልጣኑን ጫፍ የተቆናጠጡት ዘመነኞች ከዚህ ትምህርት ቢወስዱ መልካም ነው። ሰብዓዊነት ዘላለማዊነት አይሆንም፤ ሆኖ አያውቅም፤ ለመሆንም አይችልም። ሥልጣን በየትኛውም የሤራ ጥበብ ቢታቀድ፣ የትኛውንም ዓይነት የገንዘብና የጦር መሣሪያ ብቃት ላይ ቢደረስ ማብቂያው ይመጣል። ጉዳዩ እንዴት ያልቃል የሚለው ላይ ነው።

ትምህርት መውሰዱ የሚጠቅመው ለዚህ ነው። ቀድመው ያልዘሩት ለከርሞ አይበቅልም። አስቀድሞ ያልተሰራ በጎነት ከጃርት ጉድጓድ ሲገኙና ከገደል ሥር ተጎትተው ሲወጡ በድንገት ሐዘኔታን አይፈጥርም። ዕድሜና ጉስቁልና ፍትሕንም እንዲያሳንስ ወይም እንዲያዛባ ሊፈቀድለትም አይገባም። ስለዚህ ከታች ከቀበሌ ካለው ሥልጣን እስከ ማማው ድረስ አሁን ያሉት ሊገነዘቡ የሚገባው ሁሉም ወደ ማብቂያው ይመጣል። አስተላለቁ እንዴት ይሆናል የሚለው ነው።

ጧሪ አንድ ልጃቸውን ብቻ ሳይሆን በርካታ ልጆች ካንድ ቤት ያጡ ወላጆች፤ በየሜዳው ተጥለው ጠያቂ የሌላቸው የግፍ ሰለባዎች፤ ደማቸው በየጉድጓዱ ተደፍቶ የቀረው፤ ተገቢው ቀብር ያልተደረገላቸው ሥፍር ቁጥር የሌላቸው፤ የታረዱ፣ ከሞታቸው አልፎ ክብራቸውን የተነፈጉ፤ ስብዕናቸው የተዋረደው፤ ወጥቶ የመግባት መሠረታዊ መብት ተነፍገው እንደወጡ የቀሩ፤ ወዘተ ለእነዚህ ፍትሕ ሳይመጣ በወንጀል የጠገቡ የዕድሜና ጉስቁልናቸው ታይቶ ምህረት ይደረግላቸው የሚባል አስተሳሰብ፤ አሁን ያላችሁትም ከዚህ ምንም ትምህርት አትውሰዱ፤ አሁን የፈለጋችሁትን አድርጉና ስትያዙ እንዲሁ ይቅርታ ይጠየቅላችኋል በማለት ግፍንና ወንጀልን ማደፋፈር ነው። ትምህርት የሚገኘው ካለፈው፣ አሁን ካለውና ከፍትህ ነው። ይህ በሙላት ተከሽኖ ለትውልድ ሲቀመጥ ትምህርቱ ምሉዕ ይሆናል። ስለዚህ ለበጎ ሥራ በመዘጋጀት ቅን ልብ ኖሮን ለራሳችንም ለወገንም ጥቅም መስጠት እንድንችል ከዚህ እጅግ አስከፊ ውድቀት ትምህርት እንውሰድ። ሰሚ ጆሮ ያለው የዘመኑ ሹመኛ ይስማ!

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ™” አቋም ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial, Middle Column Tagged With: derg, getachew assefa, hailesillasie, meles zenawi, operation dismantle tplf, sebhat nega, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule