• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለትምህርት እንዲሆነን

January 11, 2021 01:20 pm by Editor Leave a Comment

ታላቁ መጽሐፍ የተጻፈበትን ምክንያት ሐዋርያው ጳውሎስ ሲናገር “የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር” ተጻፈ ይላል።

በአገራችን የፖለቲካ ታሪክ እጅግ ዘግናኝ ጊዜያት አሳልፈናል። በሥልጣን የተቀመጠ የሚወርድ እስከማይመስለውና ሰብዓዊነቱን እስኪዘነጋ ድረስ ሕዝብን ሲበድል ይኖራል። የሕይወቱ መጽሐፍ ሲጠናቀቅ ይሰናበታል። ስንብቱ ግን በአሰቃቂና አሳፋሪ ሁኔታ ሲሆን መመልከቱ በየዘመናቱ የመሰከርነው ሐቅ ነው።

ንጉሡ በደርግ ሲተኩ፤ ደርግ “ለለውጥ ባጎፈረው” ህወሓት ሲተካ፤ አሁን ደግሞ አይደረስብንም፣ አንበገርም፣ እንደ ደርግ አንሆንም፣ ዓቅምም፣ ገንዘብም፣ ሁሉም ነገር አለን ሲል የነበረው በረኸኛው የወንበዴ ጥርቅም ከየጉድጓዱና ሰርጡ እንደ አውሬ እየተፈለገ ሲወጣ አየን። መቼ ነው የምንማረው?

የሥልጣኑን ጫፍ የተቆናጠጡት ዘመነኞች ከዚህ ትምህርት ቢወስዱ መልካም ነው። ሰብዓዊነት ዘላለማዊነት አይሆንም፤ ሆኖ አያውቅም፤ ለመሆንም አይችልም። ሥልጣን በየትኛውም የሤራ ጥበብ ቢታቀድ፣ የትኛውንም ዓይነት የገንዘብና የጦር መሣሪያ ብቃት ላይ ቢደረስ ማብቂያው ይመጣል። ጉዳዩ እንዴት ያልቃል የሚለው ላይ ነው።

ትምህርት መውሰዱ የሚጠቅመው ለዚህ ነው። ቀድመው ያልዘሩት ለከርሞ አይበቅልም። አስቀድሞ ያልተሰራ በጎነት ከጃርት ጉድጓድ ሲገኙና ከገደል ሥር ተጎትተው ሲወጡ በድንገት ሐዘኔታን አይፈጥርም። ዕድሜና ጉስቁልና ፍትሕንም እንዲያሳንስ ወይም እንዲያዛባ ሊፈቀድለትም አይገባም። ስለዚህ ከታች ከቀበሌ ካለው ሥልጣን እስከ ማማው ድረስ አሁን ያሉት ሊገነዘቡ የሚገባው ሁሉም ወደ ማብቂያው ይመጣል። አስተላለቁ እንዴት ይሆናል የሚለው ነው።

ጧሪ አንድ ልጃቸውን ብቻ ሳይሆን በርካታ ልጆች ካንድ ቤት ያጡ ወላጆች፤ በየሜዳው ተጥለው ጠያቂ የሌላቸው የግፍ ሰለባዎች፤ ደማቸው በየጉድጓዱ ተደፍቶ የቀረው፤ ተገቢው ቀብር ያልተደረገላቸው ሥፍር ቁጥር የሌላቸው፤ የታረዱ፣ ከሞታቸው አልፎ ክብራቸውን የተነፈጉ፤ ስብዕናቸው የተዋረደው፤ ወጥቶ የመግባት መሠረታዊ መብት ተነፍገው እንደወጡ የቀሩ፤ ወዘተ ለእነዚህ ፍትሕ ሳይመጣ በወንጀል የጠገቡ የዕድሜና ጉስቁልናቸው ታይቶ ምህረት ይደረግላቸው የሚባል አስተሳሰብ፤ አሁን ያላችሁትም ከዚህ ምንም ትምህርት አትውሰዱ፤ አሁን የፈለጋችሁትን አድርጉና ስትያዙ እንዲሁ ይቅርታ ይጠየቅላችኋል በማለት ግፍንና ወንጀልን ማደፋፈር ነው። ትምህርት የሚገኘው ካለፈው፣ አሁን ካለውና ከፍትህ ነው። ይህ በሙላት ተከሽኖ ለትውልድ ሲቀመጥ ትምህርቱ ምሉዕ ይሆናል። ስለዚህ ለበጎ ሥራ በመዘጋጀት ቅን ልብ ኖሮን ለራሳችንም ለወገንም ጥቅም መስጠት እንድንችል ከዚህ እጅግ አስከፊ ውድቀት ትምህርት እንውሰድ። ሰሚ ጆሮ ያለው የዘመኑ ሹመኛ ይስማ!

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ™” አቋም ነው።

Filed Under: Editorial, Middle Column Tagged With: derg, getachew assefa, hailesillasie, meles zenawi, operation dismantle tplf, sebhat nega, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule