የሱዳን ወታደሮች በሱዳን ግዛት ውስጥ ሲንቀሳቀስ የነበረ ኢትዮጵያዊ የሚሊሻ መሪ በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን አስታወቁ። የሚሊሻ መሪ ነው የተባለው ግለሰብ በሱዳን ክልል ውስጥ ከህወሓት ወገን ሆኖ ሲዋጋ የነበረ መሆኑንም ሱዳን ትሪቢዩን ታማኝ ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል። ማንነቱ ያልተጠቀሰው ግለሰብ ከቤተሰቦቹ እና በርካታ ቁጥር ካላቸው ወታደሮችና አጃቢዎች ጋር በገዳሪፍ ግዛት አልፋሻቃ ውስጥ በቁጥጥር ስር መዋሉም ነው የተገለጸው። በወቅቱም አምስት ቢሊየን ፓውንድ (የሱዳን ይሁን የእንግሊዝ ያልተጠቀሰ)፣ መጠኑ ያልተገለጸ ወርቅ፣ የእንጨት ስራ ውጤቶች እና ሁለት ዘመናዊ ተሽከርካሪዎች ጋር መያዙም ተገልጿል። ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about አምስት ቢሊየን (የሱዳን) ፓውንድ በሱዳን ይዞ ሲንቀሳቀስ የነበረ የወንበዴው አባል ተያዘ
operation dismantle tplf
ምሽግ ሠባሪው የራያው ግምባር ልዩ ኮማንዶ ኃይል
በራያ ግንባር ተሰልፎ ያለው የኮማንዶ ኃይል ኮንክሪት ምሽጎች እና አስቸጋሪ ተራራማ ቦታዎችን በመስበር ከፍተኛ ስራ እንደሠራ በልዩ ዘመቻዎች ሃይል የኮማንዶ አዛዥ የሆኑት ኮ/ል ከማል በሪሱ ገልጸዋል። ባልተጠበቁ ቦታዎች ላይ በፍጥነት ቆርጦ በመግባት፤ የታፈነ ወገንን በማስለቀቅ እና በቀጥታ ውጊያዎች ከሌሎች የሰራዊቱ ክፍሎች ጋር በመቀናጀት የኮማንዶ አባላት የላቀ ጀግንነት መፈፀማቸውንና እየፈፀሙም እንደሚገኙ ኮ/ል ከማል ገልፀዋል። ቀደም ሲልም በሁመራ ግንባር ቅርቅር በተባለው ቦታ የተያዘውን ስትራቴጂክ ቦታ በማስለቀቅና የህውሓት ቡድን ከወታደራዊ ጠቀሜታ አንፃር ምቹ የሆኑትን የመሬት ግፆችን እንዳይጠቀባቸው በማድረግ አንጻር ትልቅ ስራ መሰራቱን ኮሎኔል ከማል ተናግረዋል። (መረጃውን ለቲክቫህ የላከው በራያ ግንባር የሚገኘው ሃምሳ አለቃ አበበ ሰማኝ ነው) ጎልጉል … [Read more...] about ምሽግ ሠባሪው የራያው ግምባር ልዩ ኮማንዶ ኃይል
በማይካድራ 18 ሰው በጉድጓድ ተጥሎ፤ 57 ደግሞ በጎርፍ ማፋሰሻ ቦይ ተገድለው ተገኙ
ጥቅምት 30/2013 ዓ.ም በንጹኃን የአማራ ብሔር ተወላጆች ላይ ዘርን መሠረት ያደረገ ጥቃት በማይካድራ ከተማ መፈፀሙ ይታወቃል። ይህን አስነዋሪ ተግባር የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በቦታው በመገኘት ባደረገው ጥናት እና ይፋ ባደረገው መረጃ የሟቾች ቁጥር በትንሹ 600 እንደሆነ ገልጾ ነበር። ግድያውም ዘርን መሠረት ያደረገና በተለይም የአማራ ተወላጆች ላይ ያነጣጠረ ጅምላ ጭፍጨፋ መሆኑን ገልጿል። ይሁን እንጂ የሟቾች ቁጥር በትንሹ 600 ነው ተብሎ የተገለጸው በማይካድራ ከተማ በየቤቱ ህይወታቸው አልፎ የተገኙ እና በቤተክርስቲያን ውስጥ የተቀበሩትን ብቻ መሠረት ያደረገ ነው። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ጥናት አድርጎ ከተመለሠ በኃላ ከማይካድራ ከተማ ወጣ ባሉ የገጠር አካባቢዎች በርካታ የጅምላ መቃብሮች መገኘታቸውን የአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት ጋዜጠኞች በቦታው … [Read more...] about በማይካድራ 18 ሰው በጉድጓድ ተጥሎ፤ 57 ደግሞ በጎርፍ ማፋሰሻ ቦይ ተገድለው ተገኙ
በጎንደር ከተማ የሽብር ተግባር ለመፈፀም በዝግጅት ላይ የነበረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ
በጎንደር ከተማ የሽብር ተግባር ለመፈፀም በዝግጅት ላይ የነበረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉን የጎንደር ከተማ ፖሊስ መምሪያ ገለፀ። የከተማው ፖሊስ መምሪያ ሀላፊ ኮማንደር አየልኝ ታክሎ፤ የከተማው ፖሊስ ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት ጋር ባደረጉት ክትትል ተጠርጣሪው ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉን ገልጸዋል። ግለሰቡ ለሽብር ተግባር ለመጠቀም ካዘጋጃቸው 35 ተቀጣጣይ ቁሳቁስ፣ 216 ማሰልጠኛ ማንዋል፣ ሶስት የተለያዩ ባንኮች ደብተር፣ 20 ገንዘብ ገቢና ወጪ ደረሰኝ እና ከአንድ ላፕቶፕ ጋር በቁጥጥር ስር መዋሉንም ተናግረዋል። በግለሰቡና በግብረ አበሮቹ ላይ የሚደረገው ምርመራ እንደቀጠለ መሆኑን የገለፁት ኮማንደር አየልኝ ስለጉዳዩ ዝርዝር መረጃ እንደሚሰጥም ጠቅሰዋል። ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about በጎንደር ከተማ የሽብር ተግባር ለመፈፀም በዝግጅት ላይ የነበረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ
ባለፉት 2ተኩል ዓመታት ትህነግ ስፖንሰር ያደረጋቸው ግጭቶች
ሰኞ ዕለት በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ትንታኔ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ “መንግሥት ሥራ እንዳይሠራ በተቀናጀ መልኩ በየቦታው ሽብር ይፈጠርለት ነበር” በማለት ትህነግ/ህወሓት ስፖንሰር ያደረጋቸው 113 ግጭቶች እንደነበሩ ገልጸዋል - ዝርዝራቸውን በዚህ መልኩ ነበር ያቀረቡት በኦሮሚያ ውስጥ ብቻ 37 ግጭቶች ነበሩ፤በአማራ ክልል 23 ግጭቶች ነበሩ፤በቤባሻንጉል ጉሙዝ 15 ግጭቶች ነበሩ፤በአዲስ አባበ 14 ግጭቶች ነበሩ፤በደቡብ፣ በጋምቤላና በተቀሩት የአገሪቷ ክልሎች ግጭቶች ነበሩ፤በሁሉም ክልሎች ችግሮች አሉ፤ ትግራይ ብቻ ነው ሰላም የነበረው፤እነሱም አያፍሩም እኛ ብቻ ነን ሰላም ይሉ ነበር፤ ዋናው የችግሩ ባለቤቶች እነሱም ነበሩ፤አሠራራቸው ተራ አልነበረም፤ ገንዘብ፣ ስልጠና ስምሪት ሚዲያም ነበራቸው፤ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about ባለፉት 2ተኩል ዓመታት ትህነግ ስፖንሰር ያደረጋቸው ግጭቶች
ሁለት ሻንጣ ሙሉ ብር ተያዘ
ሁለት ሻንጣ ሙሉ ብር ይዘው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ግለሰቦች በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ዋሉ። ዋና ሳጅን ታከለ እሸቴ ይባላል የምዕራብ ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ ባልደረባ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ደግሞ በሁመራ ከተማ ሰላም እያስከበረ ይገኛል። በቀን 19/03/2013 ዓ.ም ሰላም እያስከበረ በሚገኝበት ሁመራ ከተማ ላይ በአንድ በባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪ (ባጃጅ) ላይ ሁለት ግለሰቦች ሁለት ሻንጣ ይዘው በመጓዝ ላይ ሳሉ ካለው ወቅታዊ ሁኔታ አኳያ ፍተሻ በሚያደርግበት ጊዜ ሁለቱም ሻንጣ ሙሉ ብር ሆኖ ተገኝቷል። በወቅቱ ግለሰቦች አንዱን ሻንጣ ሙሉ ብር እንስጥህና ልቀቀን ቢሉትም ቃል የገባለትን ህዝብ እና ሙያውን በማስበለጥ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አውሏቸዋል። በአሁኑ ሰዓት በሁለቱም ተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራ እየተጣራባቸው ይገኛል። (ምንጭ፤ አማራ ፖሊስ) ጎልጉል የድገጽ … [Read more...] about ሁለት ሻንጣ ሙሉ ብር ተያዘ
የራያ ህዝብ ወደ ወሎ እንዲጠቃለል ሃሳብ ቀረበ
የትግራይ ህዝብ ነጻነት ግንባር (ትህነግ) ቡድን ድል በተደረገበት ማግስት የራያ ህዝብ እጣ ፋንታ ምን መሆን አለበት በሚል ሃሳብ የአካባቢው ተወላጆች እና ሙህራን እሁድሕዳር 20 ቀን 2013 ዓ.ም በአዲስ አበባ መክረዋል። በዚህ ውይይት ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ እና የአገልግሎት ዘርፎች ክላስተር አስተባባሪ አቶ ጃንጥራር አባይ የራያ ህዝብ ውብ ባህሉ እና ማንነቱ ተከብሮ ወደ ሚፈልገው እና ወደ ሚመስለው የወሎ ህዝብ እንዲጠቃለል የምሁራን ውይይት አስፈላጊ ነው ብለዋል። ጊዜው ችግሮችን በውይይት የምንፈታበት እንደመሆኑ ህዝቡ ምን ይላል የሚለውን አዳምጦ በትህነግ ጭቆና ውስጥ የነበረውን ማህበረሰብ የነጻነት አየር የሚተነፍስበት ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚገባ አሳስበዋል። በመድረኩ የመወያያ ሃሳብ ያቀረቡት ምህራን ትህነግ የአማርኛ ስም መጠሪያ … [Read more...] about የራያ ህዝብ ወደ ወሎ እንዲጠቃለል ሃሳብ ቀረበ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ፓርላማ ፊት ቀርበው ከተናገሩት
በለውጡ ዋዜማ የገጠመን መፈናቀል በሚሊዮን የሚቆጠር እንደነበርና በአንድ ጉድጓድ በርካቶችን የመቅበር ሂደት ይታይ ነበር፤ከለውጡ በፊት የአገርን ደህንነት ለማስጠበቅ የተቋቋመ ተቋም የኦነግን ባንዲራ በገፍ በማሳተምና እሱን የያዙ ሰዎችን ኢሬቻ በዓል የሚከበርበት ቦታ ውስጥ በማስገባት ሰዎችን ለማፈን ይጠቀምበት ነበር፤ ሎጎ የሌላው ባንዲራም በተመለከተ ተመሳሳይ ነው፤ይህም በስልጣን ላይ የነበረው ቡድን ዜጎችን ለማሳዘንና የተፈራው ለውጥ እንዳይመጣ ለማድረግ ነው፤ከለውጡ ጋር በተያያዘ ለውጡን በቅርበት በሚመሩት አካላት ላይ የደህንነት አስጨናቂ ክትትልና ዛቻ እንዲሁም የእስር ማዘዣ እስከማውጣት ተደርሶ ነበር - በጁንታው ስብስብ፤ከኢህአዴግ ሊቀመንበር ምርጫ ጋር በተያያዘ የፈለጉት ሰው ለማስመረጥ የጁንታው አባላት ያልፈነቀሉት ድንጋይ አልነበረም - ግን አልተሳካላቸውም፤ፍላጎቱ እኛን … [Read more...] about ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ፓርላማ ፊት ቀርበው ከተናገሩት
መለዮ ለባሾቹ የቁርጥ ቀን ልጆች
ከዚህ በፊት ባልተለመደ መልኩ የጦር ኃይሎች ዋና አዛዡ ዐቢይ አህመድ ጄኔራሎቻቸውን በቅጽል ስም በመጥራት ለኢትዮጵያ የሰሩትን ውለታ በዚህ መልኩ አወድሰዋል፤ 1. ድል ቁርሱ ጀነራል ብርሃኑ ጁላ 2. ትንታጉ ሌ/ጀነራል አበባዉ ታደሰ 3. ነበልባሉ ሌ/ጀነራል ባጫ ደበሌ 4. ሀገር ወዳዱ ሌ/ጀነራል ዮሃንስ ገብረመስቀል 5. የወገን አቅም ገንቢዉ ሌ/ጀነራል ሀሰን ኢብራሂም 6. ግስላዉ ሌ/ጀነራል ጌታቸዉ ጉዲና 7. አነፍናፊዉ ሌ/ጀነራል አስራት ዲናሮ 8. የጦርነት ሊቁ ሜ/ጀነራል አለምሸት ደግፌ 9. ሰዉ ሀይል አመጋጋቢ ሜ/ጀነራል ሀጫሉ ሸለማ 10. አይበገሬዉ ሜ/ጀነራል ዘዉዱ በላይ 11. ሳተናዉ ሜ/ጀነራል በላይ ሥዩም 12. ልበ ቆራጡ ሜ/ጀነራል መሰለ መሰረት 13. ሎጂስቲክስ አሳላጩ ሜጀር ጀኔራል አብዱራህማን … [Read more...] about መለዮ ለባሾቹ የቁርጥ ቀን ልጆች
ህወሓት በማይካድራ በፈፀመው ወንጀል በሽብርተኝነት እንዲፈረጅ ተጠየቀ
የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ሕወሓት ዘርን መሠረት አድርጎ በማይካድራ በፈፀመው የንጹሐን ዜጎች የግድያ ወንጀል መንስዔ በሽብርተኝነት እንዲፈረጅ ጠየቁ። አባላቱ ይህንን እና ሌሎች መሰል ወቅታዊ ጥያቄዎችን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አቅርበዋል። የተደረገው ፍጹም ጭካኔያዊ እና አረመኔያዊ ድርጊት እጅግ እንዳሳዘናቸውም አያይዘው ገልጸዋል። ተግባሩም የጦር ወንጀለኝነት መሆኑንም አበክረው ተናግረዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት አክለውም፤ የሀገርን እና የህዝብን አደራ ተቀብለው ግዳጃቸውን እየተወጡ በነበሩት የሰሜን ዕዝ የሠራዊት አባላት ላይ የሕወሓት ጽንፈኛ ቡድን የወሰደው ኢ-ሰብዓዊ ድርጊትም እጅግ እንዳሳዘናቸው ገልጸዋል። በየትኛውም የህግ መመዘኛ ተቀባይነት እንደሌለውም አስረድተዋል። የፓርላማ አባላቱ በተጨማሪም፤ የኢፌዴሪ የሀገር … [Read more...] about ህወሓት በማይካድራ በፈፀመው ወንጀል በሽብርተኝነት እንዲፈረጅ ተጠየቀ