• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ቪኦኤ በወለጋ ሆሮ ጉድሩ ለተጨፈጨፉ ኦነግ ሸኔን ከደሙ ንጹህ አደረገ

March 19, 2021 04:32 pm by Editor 1 Comment

ቪኦኤ የአማርኛው ዝግጅት ክፍል ጃል መሮ በሚል ስም የሚታወቀውን ሽፍታ ሽፋን ሲሰጠው ስለምንነቱና በትክክልም እሱ ስለመሆኑ መረጃ ሰጥቶ አያውቅም። በቢቢሲ አማርኛና በቪኦኤ እንዳሻው ጊዜ መርጦ ወንጀሉን የሚያስተባብለው ጃል መሮ፤ ሲያሻው የሰጠውን ቃለ ምልልስ ስልክ ደውሎ እንዳይተላለፍ የሚያዝ ለመሆኑ ናኮር መልካ “ጃል መሮ ቃለ ምልልሱ እንዳይተላለፍ በጠየቁት መሠረት ትቼዋለሁ” ሲል ያረጋገጠው ሃቅ ነው።

ቀደም ሲል በሃጫሉ ግድያ ኦነግ ሸኔ እጁ እንዳለበት በመታወቁ እጅግ የተቆጣውን ህዝብ ለማብረድ በናኮር መልካ አመቻችነት የቪኦኤ ዘጋቢ የሆነችው ጽዮን ግርማ ጃል መሮ በሬዲዮ ጣቢያው ቀርቦ ሳይፈተን እንዲፈነጭና ሃጢያቱን እንዲያራግፍ ፈቅዳለት እንደነበር ይታወሳል። ቢያንስ ማንነቱን መጠየቅ ሲገባ፣ ንጹሃንን በየቦታው እያደፈጠ ለሚጨፈጭፍ ሽፍታ፣ ሚዲያውንም ሌላ ጫካ በማድረግ የጨፍጫፊዎችን መሪ ቀረርቶ ስታሰማ “አይ ቪኦኤ ኤዲተርም፣ አለቃም፣ የሌለው ቤት ሆኗል” በሚል በርካቶች ሐዘናቸውን መግለጻቸው አይዘነጋም።

አሁን ደግሞ ከአርባ በላይ ሰዎች በግፍ የታረዱበትና የተጨፈጨፉበት ማስረጃና እማኞች እያሉ በተመሳሳይ ጽዮን በሪፖርቷ ጃል መሮን እንደተለመደው በናኮር በኩል አስገብታ ማስተባበያ ሰርታለታለች። “አወቅሽ አወቅሽ” እንዲሉ በዜና ማመጣጠን ስም ይህን ዘግናኝና ህዝብን ያስቆጣ ጭፍጨፋ ኦነግ ሸኔ በነፍሰ ገዳይነቱ የታወቀበትን ስሙን ቀይሮ “የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት” በሚል እንዲያስተባብል አድርጋለች።

የሆሮ ጉድሩ ሰለባዎች እና የጭፍጨፋው ምስክር የሆኑት ድንጋጤ ባዛለው ድምጽ፣ ሳግ እየተናነቃቸው “ኦነግ ሸኔ አረደን” እያሉ ነበር ለጽዮን የነገሯት። ሆኖም ጽዮን ግርማ “የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት” ዘርና ሃይማኖት ለይቶ እንደማያጠቃ ጃል መሮ ሲነገራት “ኦነግ ሸኔ” ብሎ ስሙን እንዲያስተካክል አላደረገችም። በቃለ ምልልሱ ወቅት በስህተት ቢዘነጋ እንኳ በጽሁፍ መንደርደሪያ ሲሰራለት አልተስተካከለም። ይህም ከደም ጋር ተያይዞ የቆሸሸውን ወንጀለኛውን ኦነግ ሸኔ ስሙን በመቀየር ቪኦኤ ተባባሪ እንዲሆን ያስቻለ በራሱ ወንጀል የሆነ ተግባር ነው።

በሌላ አነጋገር ዱሮ ሲገድል የነበረው ኦነግ ሸኔ ነው፤ እሱ ያለፈ ታሪክ ነው፤ አሁን ያለው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ነው፤ ይህ ሠራዊት ደግሞ በዘርና በሃይማኖት ለይቶ አያጠቃም እንዲባል ያስደረገ ነው። ስለ ሁለቱም ቡድኖች ተወካይ ሆኖ የሚናገረው ደግሞ ጃል መሮ የተባለው በደም የተነከረ ወንጀለኛ ነው። በኦነግ ሸኔ የተበላሸውን ወንጀለኛ ስሙን አስረስቶ በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ስም ሲያድስ ቪኦኤ ዋነኛ ተባባሪው ሆኗል።

ቅንጣቢ እንዳየ ጩሉሌ የገበያ ወሬ የሚጠባበቁት የዩቲዩብ ነጋዴዎች ምኑንም ሳይመረመሩ እንዲህ ያለውን “ክፉ ዓላማ” ያነገበ ዜና ከአድናቆት ጋር ፎቶ በማከል ያሰራጫሉ፤ ከግፍ ሳንቲም ይለቅማሉ። ጃል መሮ የሚባለው በከፍተኛ ወንጀል የሚፈለግ፣ ኢትዮጵያን ለማፍረስ በኦሮሞ ደም ለትህነግ የሚሰራ ሽፍታ “ግድያውን የፈጸሙት የአማራና የኦሮሞ ልዩ ኃይል ናቸው” ብሎ መርዝ እንዲረጭና ክፋቱን እንዲያራባ መፍቀድ በታሪክ የሚመዘገብ አገር የተፈጸመ ሸፍጥ ከመሆን አያልፍም። መልኩን የቀየረ ክህደትም ሊሆን ይችላል። ቢያንስ የኦሮሞ ልዩ ኃይል ገደለ የሚለውን እንቀበል ቢባል፤ አንድ ደም አፍሳሽ ሽፍታ የአማራ ልዩ ኃይል ወለጋ ገብቶ ገደለ ብሎ ሲናገር እንዴት “ለምንድነው የአማራ ኃይል ይህንን በገዛ ወገኖቹ ላይ የሚያደርገው ተብሎ አይጠየቅም”?

በተደጋጋሚ እንደሚነገረው በአገራችን ቋንቋዎች ለሚተላለፉ የውጭ አገር ሚዲያዎች የሚሠሩ ሪፖርተሮች ከመጣው ጋር ሲከንፉ፣ አገራቸውን ጉዳይ በተመለከተ ተሰፍሮ በሚሰጣቸው ልክ የድርጎ ሠፋሪ ጌቶቻቸውንና ቀጣሪዎቻቸውን አቋም ለማሟላት ከመኖር ውጭ ነጻነትን፣ “እኔ አገሬ ላይ ክህደትና ሤራን አላውጅም” በሚል የኢትዮጵያዊነት ጀዝም (ወኔ) ራሱን ያገለለ አንድም ባለሙያ እንደሌላቸው ሕዝብ ልብ ይበል። በዘመነ ደርግ ለወያኔ ሲሰሩ የነበሩ አሁንም አሉ።

በዘመን ህወሃት/ኢህአዴግ ሕዝብ ሲቀጠቀጥና ሲጨፈጨፍ ለወያኔ ሲዘፍኑ የነበሩ ዘጋቢዎች አሁንም አሉ። እነዚህ በሰብዕና ጥራት፣ በሐቅ፣ በኢትዮጵያዊነት መሥፈርት ቢለኩ ማለፍ የማይችሉ ሰሞኑን በአገራችን ላይ በተቃጣው የሚዲያ ዘመቻ ማንነታቸው ጥርት ብሎ ታይቷል።

የለውጡ ሰሞን ቀላቢዎቻቸው ፊታቸውን በትህነግ ላይ ሲያዞሩ አብረው የዞሩ፣ ዛሬ ደግሞ ትህነግ አፈር ሲገባ አፈሩን ልሶ እንዲነሳ አልቅሰው የሚያለቅሱ፣ መረጃ የሚያጣምሙና ሤራ የሚጎነጉኑ እንደ ጃል መሮ ዓይነት በደም የተጨማለቀ ሽፍታ እንዲታመን አዲስ ስም ሰይመው የሚተጉ እንዳሉ ሕዝብ ልብ ብሎ መከታተል ይገባዋል።

አገራችንን እንደ መዥገር እየመጠመጠ፤ እንደ ነቀርሳ እየገደላት የነበረውን ትህነግ በጦር አውድማ በቀላሉ ማምከን ብንችልም በሚዲያ የተነዛብን ፕሮፓጋንዳ ብዙ ጉዳት አድርሶብናል። ለዚህም ደግሞ በአገራችን ቋንቋ እና በሌሎችም በመረጃ ስም ወዳገራችን መርዛቸውን የሚተፉት የምዕራብ ዜና ወኪሎች በዋንኛነት ተጠያቂዎች ናቸው። እንደ ሕዝብ የምንሰማውንና የምናየውን በጭፍን የምንጋት ሳንሆን ከአገር ኅልውና ጋር በማገናዘብ፤ ግራ ቀኙን በማየት በብልሃትና በጥበብ የምንመላለስ ልንሆን ይገባናል።

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ™” አቋም ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial, Left Column Tagged With: jal mero, olf shanee, olf shine, operation dismantle tplf, tsion girma, voa amharic

Reader Interactions

Comments

  1. Yassin Kedir says

    March 20, 2021 08:59 am at 8:59 am

    ቪእኤ, የጀርመን ድምፅ እና TPLF ለኔ ምንም ልዩነት የላቸውም ፡፡

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule