• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ቪኦኤ በወለጋ ሆሮ ጉድሩ ለተጨፈጨፉ ኦነግ ሸኔን ከደሙ ንጹህ አደረገ

March 19, 2021 04:32 pm by Editor 1 Comment

ቪኦኤ የአማርኛው ዝግጅት ክፍል ጃል መሮ በሚል ስም የሚታወቀውን ሽፍታ ሽፋን ሲሰጠው ስለምንነቱና በትክክልም እሱ ስለመሆኑ መረጃ ሰጥቶ አያውቅም። በቢቢሲ አማርኛና በቪኦኤ እንዳሻው ጊዜ መርጦ ወንጀሉን የሚያስተባብለው ጃል መሮ፤ ሲያሻው የሰጠውን ቃለ ምልልስ ስልክ ደውሎ እንዳይተላለፍ የሚያዝ ለመሆኑ ናኮር መልካ “ጃል መሮ ቃለ ምልልሱ እንዳይተላለፍ በጠየቁት መሠረት ትቼዋለሁ” ሲል ያረጋገጠው ሃቅ ነው።

ቀደም ሲል በሃጫሉ ግድያ ኦነግ ሸኔ እጁ እንዳለበት በመታወቁ እጅግ የተቆጣውን ህዝብ ለማብረድ በናኮር መልካ አመቻችነት የቪኦኤ ዘጋቢ የሆነችው ጽዮን ግርማ ጃል መሮ በሬዲዮ ጣቢያው ቀርቦ ሳይፈተን እንዲፈነጭና ሃጢያቱን እንዲያራግፍ ፈቅዳለት እንደነበር ይታወሳል። ቢያንስ ማንነቱን መጠየቅ ሲገባ፣ ንጹሃንን በየቦታው እያደፈጠ ለሚጨፈጭፍ ሽፍታ፣ ሚዲያውንም ሌላ ጫካ በማድረግ የጨፍጫፊዎችን መሪ ቀረርቶ ስታሰማ “አይ ቪኦኤ ኤዲተርም፣ አለቃም፣ የሌለው ቤት ሆኗል” በሚል በርካቶች ሐዘናቸውን መግለጻቸው አይዘነጋም።

አሁን ደግሞ ከአርባ በላይ ሰዎች በግፍ የታረዱበትና የተጨፈጨፉበት ማስረጃና እማኞች እያሉ በተመሳሳይ ጽዮን በሪፖርቷ ጃል መሮን እንደተለመደው በናኮር በኩል አስገብታ ማስተባበያ ሰርታለታለች። “አወቅሽ አወቅሽ” እንዲሉ በዜና ማመጣጠን ስም ይህን ዘግናኝና ህዝብን ያስቆጣ ጭፍጨፋ ኦነግ ሸኔ በነፍሰ ገዳይነቱ የታወቀበትን ስሙን ቀይሮ “የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት” በሚል እንዲያስተባብል አድርጋለች።

የሆሮ ጉድሩ ሰለባዎች እና የጭፍጨፋው ምስክር የሆኑት ድንጋጤ ባዛለው ድምጽ፣ ሳግ እየተናነቃቸው “ኦነግ ሸኔ አረደን” እያሉ ነበር ለጽዮን የነገሯት። ሆኖም ጽዮን ግርማ “የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት” ዘርና ሃይማኖት ለይቶ እንደማያጠቃ ጃል መሮ ሲነገራት “ኦነግ ሸኔ” ብሎ ስሙን እንዲያስተካክል አላደረገችም። በቃለ ምልልሱ ወቅት በስህተት ቢዘነጋ እንኳ በጽሁፍ መንደርደሪያ ሲሰራለት አልተስተካከለም። ይህም ከደም ጋር ተያይዞ የቆሸሸውን ወንጀለኛውን ኦነግ ሸኔ ስሙን በመቀየር ቪኦኤ ተባባሪ እንዲሆን ያስቻለ በራሱ ወንጀል የሆነ ተግባር ነው።

በሌላ አነጋገር ዱሮ ሲገድል የነበረው ኦነግ ሸኔ ነው፤ እሱ ያለፈ ታሪክ ነው፤ አሁን ያለው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ነው፤ ይህ ሠራዊት ደግሞ በዘርና በሃይማኖት ለይቶ አያጠቃም እንዲባል ያስደረገ ነው። ስለ ሁለቱም ቡድኖች ተወካይ ሆኖ የሚናገረው ደግሞ ጃል መሮ የተባለው በደም የተነከረ ወንጀለኛ ነው። በኦነግ ሸኔ የተበላሸውን ወንጀለኛ ስሙን አስረስቶ በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ስም ሲያድስ ቪኦኤ ዋነኛ ተባባሪው ሆኗል።

ቅንጣቢ እንዳየ ጩሉሌ የገበያ ወሬ የሚጠባበቁት የዩቲዩብ ነጋዴዎች ምኑንም ሳይመረመሩ እንዲህ ያለውን “ክፉ ዓላማ” ያነገበ ዜና ከአድናቆት ጋር ፎቶ በማከል ያሰራጫሉ፤ ከግፍ ሳንቲም ይለቅማሉ። ጃል መሮ የሚባለው በከፍተኛ ወንጀል የሚፈለግ፣ ኢትዮጵያን ለማፍረስ በኦሮሞ ደም ለትህነግ የሚሰራ ሽፍታ “ግድያውን የፈጸሙት የአማራና የኦሮሞ ልዩ ኃይል ናቸው” ብሎ መርዝ እንዲረጭና ክፋቱን እንዲያራባ መፍቀድ በታሪክ የሚመዘገብ አገር የተፈጸመ ሸፍጥ ከመሆን አያልፍም። መልኩን የቀየረ ክህደትም ሊሆን ይችላል። ቢያንስ የኦሮሞ ልዩ ኃይል ገደለ የሚለውን እንቀበል ቢባል፤ አንድ ደም አፍሳሽ ሽፍታ የአማራ ልዩ ኃይል ወለጋ ገብቶ ገደለ ብሎ ሲናገር እንዴት “ለምንድነው የአማራ ኃይል ይህንን በገዛ ወገኖቹ ላይ የሚያደርገው ተብሎ አይጠየቅም”?

በተደጋጋሚ እንደሚነገረው በአገራችን ቋንቋዎች ለሚተላለፉ የውጭ አገር ሚዲያዎች የሚሠሩ ሪፖርተሮች ከመጣው ጋር ሲከንፉ፣ አገራቸውን ጉዳይ በተመለከተ ተሰፍሮ በሚሰጣቸው ልክ የድርጎ ሠፋሪ ጌቶቻቸውንና ቀጣሪዎቻቸውን አቋም ለማሟላት ከመኖር ውጭ ነጻነትን፣ “እኔ አገሬ ላይ ክህደትና ሤራን አላውጅም” በሚል የኢትዮጵያዊነት ጀዝም (ወኔ) ራሱን ያገለለ አንድም ባለሙያ እንደሌላቸው ሕዝብ ልብ ይበል። በዘመነ ደርግ ለወያኔ ሲሰሩ የነበሩ አሁንም አሉ።

በዘመን ህወሃት/ኢህአዴግ ሕዝብ ሲቀጠቀጥና ሲጨፈጨፍ ለወያኔ ሲዘፍኑ የነበሩ ዘጋቢዎች አሁንም አሉ። እነዚህ በሰብዕና ጥራት፣ በሐቅ፣ በኢትዮጵያዊነት መሥፈርት ቢለኩ ማለፍ የማይችሉ ሰሞኑን በአገራችን ላይ በተቃጣው የሚዲያ ዘመቻ ማንነታቸው ጥርት ብሎ ታይቷል።

የለውጡ ሰሞን ቀላቢዎቻቸው ፊታቸውን በትህነግ ላይ ሲያዞሩ አብረው የዞሩ፣ ዛሬ ደግሞ ትህነግ አፈር ሲገባ አፈሩን ልሶ እንዲነሳ አልቅሰው የሚያለቅሱ፣ መረጃ የሚያጣምሙና ሤራ የሚጎነጉኑ እንደ ጃል መሮ ዓይነት በደም የተጨማለቀ ሽፍታ እንዲታመን አዲስ ስም ሰይመው የሚተጉ እንዳሉ ሕዝብ ልብ ብሎ መከታተል ይገባዋል።

አገራችንን እንደ መዥገር እየመጠመጠ፤ እንደ ነቀርሳ እየገደላት የነበረውን ትህነግ በጦር አውድማ በቀላሉ ማምከን ብንችልም በሚዲያ የተነዛብን ፕሮፓጋንዳ ብዙ ጉዳት አድርሶብናል። ለዚህም ደግሞ በአገራችን ቋንቋ እና በሌሎችም በመረጃ ስም ወዳገራችን መርዛቸውን የሚተፉት የምዕራብ ዜና ወኪሎች በዋንኛነት ተጠያቂዎች ናቸው። እንደ ሕዝብ የምንሰማውንና የምናየውን በጭፍን የምንጋት ሳንሆን ከአገር ኅልውና ጋር በማገናዘብ፤ ግራ ቀኙን በማየት በብልሃትና በጥበብ የምንመላለስ ልንሆን ይገባናል።

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ™” አቋም ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Editorial, Left Column Tagged With: jal mero, olf shanee, olf shine, operation dismantle tplf, tsion girma, voa amharic

Reader Interactions

Comments

  1. Yassin Kedir says

    March 20, 2021 08:59 am at 8:59 am

    ቪእኤ, የጀርመን ድምፅ እና TPLF ለኔ ምንም ልዩነት የላቸውም ፡፡

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአብን “ፀሐይ” ጎንደር ላይ ጠለቀች April 22, 2021 09:48 pm
  • ተፈትነን እንጂ ወድቀን አናውቅም April 22, 2021 10:55 am
  • ፍፁም ብርሃኔና ታምራት የማነ በቁጥጥር ሥር ዋሉ April 16, 2021 10:06 am
  • “ለአንድ ፓርቲ የማደላ ከሆነ ሄጄ እዚያው ፓርቲ እገባለሁ” ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ April 16, 2021 08:45 am
  • “ተዋግተን አይደለም ስንተኛ ብንውል እንኳን መቀሌና አዲስ አበባ አይገቡም” ጄኔራል ባጫ April 14, 2021 09:06 am
  • የስኳር ፋብሪካዎች ተሽጠው ዕዳቸውን እንዲከፍሉ ተወሰነ April 14, 2021 08:53 am
  • “ኤርትራዊ ነን” በማለት የመኖሪያ ፈቃድ ሲቀበሉ የኖሩ የትግራይ ሰዎችን መለየት ተጀመረ April 1, 2021 02:01 am
  • ምርጫ ቦርድ የኦነግን ጥያቄ ውድቅ አደረገ April 1, 2021 01:15 am
  • “እርግጠኛ ሆኜ የምነግራችሁ መንግሥት ኮሮጆ አይሰርቅም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ April 1, 2021 01:09 am
  • መንግሥት ካልደረሰልን አሁንም ግድያ ይኖራል – ነዋሪዎች April 1, 2021 01:04 am
  • በትግራይ ሊዘረፍ የነበረ የእርዳታ እህል ተያዘ April 1, 2021 12:39 am
  • “በኢትዮጵያ ክብርና ጥቅም ከመጣችሁ አንገቴ ይቀላል እንጂ አልደራደርም” March 24, 2021 01:22 am
  • “ከዚህ በኋላ ህወሓት ማለት በነፋስ የተበተነ ዱቄት ነው” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ March 23, 2021 11:28 pm
  • እነ ስብሃት ነጋ ጥያቄያቸው ውድቅ ሆነ March 23, 2021 10:23 pm
  • በርግጥ ኢትዮጵያ ዝናብ አዝንባለች? March 23, 2021 10:15 pm
  • አሜሪካ በሴናተሯ አማካይነት “ለቅሶ” ደረሰች March 21, 2021 08:57 pm
  • ቪኦኤ በወለጋ ሆሮ ጉድሩ ለተጨፈጨፉ ኦነግ ሸኔን ከደሙ ንጹህ አደረገ March 19, 2021 04:32 pm
  • ባልደራስና የአብን የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ March 18, 2021 01:56 pm
  • ኤርሚያስ ለገሰ “የወያኔ የፕሮፖጋንዳ ሰራተኛ እያለ የለመደው የቁጥር ጫወታ አለቀቀውም” March 17, 2021 09:54 pm
  • በትግራይ ሰብዓዊ ድጋፍ በተቀላጠፈ ሁኔታ እየተካሄደ ነው – የተመድ የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት March 17, 2021 04:54 am
  • ምርጫ ቦርድ ከፈቀደለት ኦነግ በምርጫው እንደሚወዳደር አስታወቀ March 17, 2021 04:30 am
  • በዓለምአቀፍ ሚዲያ ዘጋቢዎች ላይ እርምጃ ሊወሰድ ነው March 15, 2021 11:25 am
  • በሲዳማ/ሀዋሳ 128 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጥ፤ 2 መትረየስ ከ8,129 ጥይት ጋር ተያዘ March 15, 2021 10:13 am
  • የአክሱም ጅምላ ጭፍጨፋ ተብሎ የተሰራጨው ፎቶ የሐሰት ሆነ March 15, 2021 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule