• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ቪኦኤ በወለጋ ሆሮ ጉድሩ ለተጨፈጨፉ ኦነግ ሸኔን ከደሙ ንጹህ አደረገ

March 19, 2021 04:32 pm by Editor 1 Comment

ቪኦኤ የአማርኛው ዝግጅት ክፍል ጃል መሮ በሚል ስም የሚታወቀውን ሽፍታ ሽፋን ሲሰጠው ስለምንነቱና በትክክልም እሱ ስለመሆኑ መረጃ ሰጥቶ አያውቅም። በቢቢሲ አማርኛና በቪኦኤ እንዳሻው ጊዜ መርጦ ወንጀሉን የሚያስተባብለው ጃል መሮ፤ ሲያሻው የሰጠውን ቃለ ምልልስ ስልክ ደውሎ እንዳይተላለፍ የሚያዝ ለመሆኑ ናኮር መልካ “ጃል መሮ ቃለ ምልልሱ እንዳይተላለፍ በጠየቁት መሠረት ትቼዋለሁ” ሲል ያረጋገጠው ሃቅ ነው።

ቀደም ሲል በሃጫሉ ግድያ ኦነግ ሸኔ እጁ እንዳለበት በመታወቁ እጅግ የተቆጣውን ህዝብ ለማብረድ በናኮር መልካ አመቻችነት የቪኦኤ ዘጋቢ የሆነችው ጽዮን ግርማ ጃል መሮ በሬዲዮ ጣቢያው ቀርቦ ሳይፈተን እንዲፈነጭና ሃጢያቱን እንዲያራግፍ ፈቅዳለት እንደነበር ይታወሳል። ቢያንስ ማንነቱን መጠየቅ ሲገባ፣ ንጹሃንን በየቦታው እያደፈጠ ለሚጨፈጭፍ ሽፍታ፣ ሚዲያውንም ሌላ ጫካ በማድረግ የጨፍጫፊዎችን መሪ ቀረርቶ ስታሰማ “አይ ቪኦኤ ኤዲተርም፣ አለቃም፣ የሌለው ቤት ሆኗል” በሚል በርካቶች ሐዘናቸውን መግለጻቸው አይዘነጋም።

አሁን ደግሞ ከአርባ በላይ ሰዎች በግፍ የታረዱበትና የተጨፈጨፉበት ማስረጃና እማኞች እያሉ በተመሳሳይ ጽዮን በሪፖርቷ ጃል መሮን እንደተለመደው በናኮር በኩል አስገብታ ማስተባበያ ሰርታለታለች። “አወቅሽ አወቅሽ” እንዲሉ በዜና ማመጣጠን ስም ይህን ዘግናኝና ህዝብን ያስቆጣ ጭፍጨፋ ኦነግ ሸኔ በነፍሰ ገዳይነቱ የታወቀበትን ስሙን ቀይሮ “የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት” በሚል እንዲያስተባብል አድርጋለች።

የሆሮ ጉድሩ ሰለባዎች እና የጭፍጨፋው ምስክር የሆኑት ድንጋጤ ባዛለው ድምጽ፣ ሳግ እየተናነቃቸው “ኦነግ ሸኔ አረደን” እያሉ ነበር ለጽዮን የነገሯት። ሆኖም ጽዮን ግርማ “የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት” ዘርና ሃይማኖት ለይቶ እንደማያጠቃ ጃል መሮ ሲነገራት “ኦነግ ሸኔ” ብሎ ስሙን እንዲያስተካክል አላደረገችም። በቃለ ምልልሱ ወቅት በስህተት ቢዘነጋ እንኳ በጽሁፍ መንደርደሪያ ሲሰራለት አልተስተካከለም። ይህም ከደም ጋር ተያይዞ የቆሸሸውን ወንጀለኛውን ኦነግ ሸኔ ስሙን በመቀየር ቪኦኤ ተባባሪ እንዲሆን ያስቻለ በራሱ ወንጀል የሆነ ተግባር ነው።

በሌላ አነጋገር ዱሮ ሲገድል የነበረው ኦነግ ሸኔ ነው፤ እሱ ያለፈ ታሪክ ነው፤ አሁን ያለው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ነው፤ ይህ ሠራዊት ደግሞ በዘርና በሃይማኖት ለይቶ አያጠቃም እንዲባል ያስደረገ ነው። ስለ ሁለቱም ቡድኖች ተወካይ ሆኖ የሚናገረው ደግሞ ጃል መሮ የተባለው በደም የተነከረ ወንጀለኛ ነው። በኦነግ ሸኔ የተበላሸውን ወንጀለኛ ስሙን አስረስቶ በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ስም ሲያድስ ቪኦኤ ዋነኛ ተባባሪው ሆኗል።

ቅንጣቢ እንዳየ ጩሉሌ የገበያ ወሬ የሚጠባበቁት የዩቲዩብ ነጋዴዎች ምኑንም ሳይመረመሩ እንዲህ ያለውን “ክፉ ዓላማ” ያነገበ ዜና ከአድናቆት ጋር ፎቶ በማከል ያሰራጫሉ፤ ከግፍ ሳንቲም ይለቅማሉ። ጃል መሮ የሚባለው በከፍተኛ ወንጀል የሚፈለግ፣ ኢትዮጵያን ለማፍረስ በኦሮሞ ደም ለትህነግ የሚሰራ ሽፍታ “ግድያውን የፈጸሙት የአማራና የኦሮሞ ልዩ ኃይል ናቸው” ብሎ መርዝ እንዲረጭና ክፋቱን እንዲያራባ መፍቀድ በታሪክ የሚመዘገብ አገር የተፈጸመ ሸፍጥ ከመሆን አያልፍም። መልኩን የቀየረ ክህደትም ሊሆን ይችላል። ቢያንስ የኦሮሞ ልዩ ኃይል ገደለ የሚለውን እንቀበል ቢባል፤ አንድ ደም አፍሳሽ ሽፍታ የአማራ ልዩ ኃይል ወለጋ ገብቶ ገደለ ብሎ ሲናገር እንዴት “ለምንድነው የአማራ ኃይል ይህንን በገዛ ወገኖቹ ላይ የሚያደርገው ተብሎ አይጠየቅም”?

በተደጋጋሚ እንደሚነገረው በአገራችን ቋንቋዎች ለሚተላለፉ የውጭ አገር ሚዲያዎች የሚሠሩ ሪፖርተሮች ከመጣው ጋር ሲከንፉ፣ አገራቸውን ጉዳይ በተመለከተ ተሰፍሮ በሚሰጣቸው ልክ የድርጎ ሠፋሪ ጌቶቻቸውንና ቀጣሪዎቻቸውን አቋም ለማሟላት ከመኖር ውጭ ነጻነትን፣ “እኔ አገሬ ላይ ክህደትና ሤራን አላውጅም” በሚል የኢትዮጵያዊነት ጀዝም (ወኔ) ራሱን ያገለለ አንድም ባለሙያ እንደሌላቸው ሕዝብ ልብ ይበል። በዘመነ ደርግ ለወያኔ ሲሰሩ የነበሩ አሁንም አሉ።

በዘመን ህወሃት/ኢህአዴግ ሕዝብ ሲቀጠቀጥና ሲጨፈጨፍ ለወያኔ ሲዘፍኑ የነበሩ ዘጋቢዎች አሁንም አሉ። እነዚህ በሰብዕና ጥራት፣ በሐቅ፣ በኢትዮጵያዊነት መሥፈርት ቢለኩ ማለፍ የማይችሉ ሰሞኑን በአገራችን ላይ በተቃጣው የሚዲያ ዘመቻ ማንነታቸው ጥርት ብሎ ታይቷል።

የለውጡ ሰሞን ቀላቢዎቻቸው ፊታቸውን በትህነግ ላይ ሲያዞሩ አብረው የዞሩ፣ ዛሬ ደግሞ ትህነግ አፈር ሲገባ አፈሩን ልሶ እንዲነሳ አልቅሰው የሚያለቅሱ፣ መረጃ የሚያጣምሙና ሤራ የሚጎነጉኑ እንደ ጃል መሮ ዓይነት በደም የተጨማለቀ ሽፍታ እንዲታመን አዲስ ስም ሰይመው የሚተጉ እንዳሉ ሕዝብ ልብ ብሎ መከታተል ይገባዋል።

አገራችንን እንደ መዥገር እየመጠመጠ፤ እንደ ነቀርሳ እየገደላት የነበረውን ትህነግ በጦር አውድማ በቀላሉ ማምከን ብንችልም በሚዲያ የተነዛብን ፕሮፓጋንዳ ብዙ ጉዳት አድርሶብናል። ለዚህም ደግሞ በአገራችን ቋንቋ እና በሌሎችም በመረጃ ስም ወዳገራችን መርዛቸውን የሚተፉት የምዕራብ ዜና ወኪሎች በዋንኛነት ተጠያቂዎች ናቸው። እንደ ሕዝብ የምንሰማውንና የምናየውን በጭፍን የምንጋት ሳንሆን ከአገር ኅልውና ጋር በማገናዘብ፤ ግራ ቀኙን በማየት በብልሃትና በጥበብ የምንመላለስ ልንሆን ይገባናል።

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ™” አቋም ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial, Left Column Tagged With: jal mero, olf shanee, olf shine, operation dismantle tplf, tsion girma, voa amharic

Reader Interactions

Comments

  1. Yassin Kedir says

    March 20, 2021 08:59 am at 8:59 am

    ቪእኤ, የጀርመን ድምፅ እና TPLF ለኔ ምንም ልዩነት የላቸውም ፡፡

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule