• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እነ ስብሃት ነጋ ጥያቄያቸው ውድቅ ሆነ

March 23, 2021 10:23 pm by Editor 1 Comment

እነ አቶ ስብሃት ነጋ ጉዳያችን በትግራይ ክልል ፍርድ ቤት ይታይልን ሲሉ አቤቱታ አቅርበው ነበር።

ይህን አቤቱታ ያቀረቡት ዛሬ (ማክሰኞ) በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድቤት አራዳ ምድብ ችሎት ነው።

በችሎት የተገኙት የጠቅላይ አቃቤ ህግ ቡድን በበኩሉላቸው የፌዴራል መንግስትን ስልጣን ለመጣል በሚል የሽብር አዋጁን በመተላለፍ በመላው ሀገሪቱ የተፈጸመ ወንጀል መሆኑን በመጥቀስ ተጠርጣሪዎቹ መቀሌ ሆነው በሰጡት ትዕዛዝ ባህርዳር እና ጎንደርን በሮኬት ማስደብደባቸው አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል።

በተጨማሪም ተከሳሾቹ ስልጣን ተከፋፍለው በተለያዩ ቦታዎች የተፈጸመ ወንጀል ነው ያለው አቃቤ ህግ ዶክተር አዲስ አለም ባሌማ የድርጅቱ ስራ አስፈጻሚ ሆነው አዲስ አባባ ቁጭ ብለው ሲፈጽሙ የነበረው ወንጀል አንድ ቦታ አለመሆኑን ማመላከቻ ነው ብሏል በምላሹ።

ይህ የሚያሳየው በሃገሪቱ በተለያዩ ቦታዎች መፈጸማቸውን ስለሆነ በአካባቢ ስልጣን ሳይገደብ ጉዳያቸው መታየት ያለበት በፌዴራል ፍርድ ቤት ነው ሲል በጠበቆቻቸው ያነሱት መከራከሪያ ውድቅ እንዲደረግ ጠይቋል።

የተጠርጣሪ ጠበቆች ቀዳሚ ምርመራ መደረግ የለበትም አቃቤ ህግም ቀዳሚ ምርመራ እንዲደረግ ያዘዘው ትዕዛዝ አግባብነት የለውም የቀዳሚ ምርመራ ህጉ ተሽሯል ብለው ያነሱት መቃወሚያ በተመለከተም፤ አቃቤ ህግ በቂ ምክንያት ካለው በወንጀለኛ መቅጫ ስነ ስርዓት ህግ አንቀጽ 38 ቀዳሚ ምርመራ ማድረግ ይችላል ብሏል።

እንዲሁም በአንቀጽ 80 ንዑስ አንጽ 2 ስር ህጉን ተከትሎ የቀዳሚ ምርመራ የመወሰን ስልጣን እንዳለው ያስቀምጣል ሲል አብራርቷል።

የቀዳሚ ምርመራ ህግ ሙሉ ለሙሉ አልተሻረም በስራ ላይ ይገኛል ሲል ምላሽ የሰጠው አቃቤ ህግ፤ የውንብድና ወንጀል እና የግፍ ግድያ የተፈጸመ ከሆነ ቀዳሚ ምርመራ ሊደረግ እንደሚችል በህጉ ያስቀምጣል ሲል የአቃቤ ህግ ቡድን ምላሽ ሰጥቷል።

በተጨማሪም የቀዳሚ ምርመራ ምስክሮች ስምና ዝርዝሩ አልተገለጸም እዚህ ላይ ትዕዛዝ ይሰጥልን ሲሉም ላቀረቡት አቤቱታ አቃቤ ህግ የምስክር ጥበቃ አዋጅን ተከትሎ ለምስክሮች ደህንነት ሲባል የስም ዝርዝራቸው እንደማይሰጥ አብራርቷል።

ከዚሀም ባለፈ የተጠርጣሪ ጠበቆች ዳኛው ከዚህ በፊት በነበረ የጊዜ ቀጠሮ ጉዳይን ሲመለከቱ መዝገባችን ተለይቶ ይቅረብ ብለን የጠየቅነው ጥያቄ ሳይታይ አልፏል የሚል ምክንያት በማንሳት ዳኛው ከዚህ ከቀዳሚ ምርመራ መዝገብ ይነሱልን ሲሉም አመልክተዋል።

እንዳጠቃላይ በተነሱ መከራከሪያ ነጥቦች ላይ ፍርድቤቱ ምርምሮ ትዕዛዝ ለመስጠት ለመጋቢት 17 ቀን 2013 ዓ/ም ተለዋጭ ቀጠሮ የሰጠ ሲሆን፤ በትናንትናው እለት ችሎት ከደንበኞቻቸን ጋር ባልተመካከርንበት ሁኔታ ምስክር መሰማቱ ተገቢ አይደለም ተለዋጭ ቀጠሮ ይሰጠን ብለው ያቀረቡት አቤቱታን መርምሮ ችሎቱ የመመካከሪያ በቂ የ7 ቀን ጊዜ ሰጥቻለሁ ሲል ጥያቄያቸውን ውድቅ አድርጓል።

ችሎቱ ስብሃት ነጋ በግል ሃኪም እንዲታከሙ የታዘዘው ትዕዛዝ ተፈጻሚ እንዲሆን አዟል።

አባይ ወልዱ ለዐይናቸው ህመም በግል እንዲታከሙ ያቀረቡት አቤቱታን ተቀብሎ ትዕዛዝ ሰጥቷል። (ፋና)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, Left Column Tagged With: operation dismantle tplf, sibhat, tplf, ችሎት

Reader Interactions

Comments

  1. gihaile says

    April 3, 2021 12:09 am at 12:09 am

    እነዚህ ወንጀለኞች መታየትና መመርመር የነበረባቸው በወታደራዊ የጦር ፍርድ ቤት እንጂ በሲቪል ፍርድ ቤት ኣልነበረም። እነዚህ ግለሰቦች የጦር ወንጀለኞችና የሰብዓዊ መብት ጥሰትና የአገር ሐብትን የመዝረፍ ሕገወጥ ተግባር ጋር የተገናኘ ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule