• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በ96 የህወሃት ወንበዴዎች ላይ የፍርድ ቤት ማዘዣ ወጣባቸው

November 12, 2020 01:50 pm by Editor 1 Comment

የአገር ክህደት ወንጀል በፈፀሙ የጁንታው ሕወሓት ቡድን ላይ የፍርድ ቤት የመያዣ ትዕዛዝ እንደወጣባቸው የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።

የጥፋት ቡድኑ አባላት ከኦነግ ሸኔ እና ከሌሎች ፀረ-ሰላም ሃይሎች ጋር በመቀናጀትም ከተለያዩ ክልሎች አገርን የማፍረስ ተልዕኮ ያላቸውን ኃይሎች በመመልመል ትግራይ ክልል ድረስ በመውሰድ ለእኩይ ተልዕኮቸው ስኬት የተለያዩ ስልጠናዎችን በመስጠት እንዲሁም የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፎችን በማድረግ በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች ብሄርን ከብሄር በማጋጨት እና በሃይማኖት ሽፋን ሁከትና ብጥብጥ እንዲፈጠር በማድረግ በርካታ ንፅሁን ዜጎች እንዲገደሉ፣ በአካልና በንብረት ላይም ከባድ ጉዳት እንዲደርስ ማድረጋቸውን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በላከው መግለጫ አመልክቷል፡፡

እነዚህ የሀገር ህልውናን አደጋ ላይ በመጣል እንዲሁም ህገ-መንግስቱንና ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱን በሀይል በመናድ ወንጀል የሚፈለጉትና የፍርድ ቤት የመያዣ ትዕዛዝ የወጣባቸው፡-

  1. ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል
  2. ጌታቸው ረዳ
  3. ፈትለወርቅ ገ/እግዝያብሄር
  4. አስመላሽ ወ/ስላሴ
  5. ዶ/ር አብርሃም ተከስተ
  6. ኪሪያ ኢብራሂም
  7. ረዳይ አለፎም
  8. አማኑኤል አሰፋ
  9. ዶ/ር አትንኩት መዝገቡ
  10. ኪሮስ ሀጎስ
  11. ያለም ፀጋ
  12. ሰብለ ካህሳያ
  13. ጌታቸው አሰፋ
  14. ዳንኤል አሰፋ
  15. ኢሳያስ ታደሰ
  16. ዶ/ር አክሊሉ ሀ/ሚካኤል
  17. አለም ገ/ዋህድ
  18. ተክላይ ገ/መድህን
  19. ዶ/ር እያሱ በርሄ
  20. ዶ/ር ረዳይ በርሄ
  21. ዶ/ር ኪዳን ማርያም በርሄ
  22. ነጋ አሰፋ
  23. ሺሻይ መረሳ
  24. ዶ/ር ገ/ህይወት ገ/እግዝያብሄር
  25. አፅብሃ አረጋዊ
  26. ዶ/ር ኢ/ር ሰለሞን ኪዳኔ
  27. ሀዱሽ ዘነበ
  28. በርሄ ገ/እየሱስ
  29. ይትባረክ አምሃ
  30. ዶ/ር ገ/መስቀል ካህሳይ
  31. ዶ/ር ፍስሃ ሀ/ፂዮን
  32. ርስቀ አለማየው
  33. ዶ/ር አዲስ አለም ቤሌማ
  34. ዘነበች ፍስሃ
  35. ፍሬወይኒ ገ/እግዝያብሄር
  36. ስዩም መስፍን
  37. አባይ ፀሐዬ
  38. እያሱ ተስፋይ
  39. ለምለም ሀድጎ
  40. ፕሮፌሰር ክንድያ ገ/ህይወት
  41. ሀብቱ ኪሮስ
  42. በየነ ምክሩ
  43. ካሳዬ ገ/ህይወት
  44. ሩፈኤል ሽፈራ
  45. ሊያ ካሳ
  46. ተወለደ ገ/ፃዲቅ
  47. ሙሉ ገ/እግዝያብሄር
  48. ኪሮስ ጉዑሽ
  49. ዶ/ር አማኑኤል ሀይሌ
  50. ደሳለኝ ተፈራ
  51. ኢንጅነር አርአያ ብርሀኔ
  52. አልማዝ ገ/ፃድቅ
  53. ሰለሞን መአሾ
  54. ተኪኡ ማዕሾ
  55. ገነት አረፈ
  56. ብርክቲ ገ/መድህን
  57. ዶ/ር ሀጎስ ገዳፋይ
  58. ዘራይ አስጎዶም
  59. አሰፋ በላይ
  60. ሸዋንግዘው ገዛኸኝ
  61. አፅብሃ ግደይ
  62. ስብሀት ነጋ
  63. ሴኮትሬ ጌታቸው
  64. በሪሁን ተ/ብርሃን የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ዳኛ የነበረ ናቸው፡፡

ከላይ ስማቸው የተዘረዘረው የወንበዴው የጁንታው ሕወሓት የጥፋት ቡድን አባላት የአገር ክህደት ወንጀል ከመፈጸማቸውም በተጨማሪ በከፍተኛ የአገር ሃብት ምዝበራና ዘረፋ እንዲሁም በሰብዓዊ መብት ጥሰት ወንጀልም ጭምር የሚፈለጉ መሆናቸውን ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በመግለጫው አሳውቋል፡፡

በተመሳሳይም ከጁንታው ሕወሓት ቡድን አባላት ጋር እየተገናኙ የሀገር ክህደት ወንጀል በፈፀሙና አገር በማፍረስ ሴራ በተሳተፉ የሀገር መከላከያ ሰራዊት እና የፖሊስ አመራሮች ላይም የፍርድ ቤት የመያዣ ትዕዛዝ እንደወጣባቸው የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በመግለጫው አስታውቋል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ መንግስት እና ሕዝብ የጣለባቸውን አገራዊ ኃላፊነትና ህገመንግስታዊ ግዴት ወደጎን በመተው መቀመጫዉን ትግራይ ክልል ካደረገዉ ከወንበዴው የህወሃት የጁንታው ቡድን አባላት ተልዕኮ በመቀበል በሰሜን ዕዝ ሰራዊት አባላት ውስጥ ሴሎችን በማደራጀት ከማዕከል የነበረው ግንኙነት እንዲቋረጥና ጥቅምት24 ቀን 2013 ዓ/ም ጥቃት እንዲፈጸም በማድረግ የሞት፣ የአካል ጉዳት እና የጦር መሳሪያ ዝርፊያ እንዲፈፀም ማድረጋቸውን የኮሚሽኑ መግለጫ ያመለክታል፡፡

ባለፉት 21 አመታት በምሽግ አብረው ሲኖሩ የነበሩ ጓዶቻቸውን የጁንታው ቡድን እኩይ አላማ ማስፈጸሚያ በማድረግ አገር በማፍረስ ተልዕኮው በመምራትና በመሳተፍ የሚፈለጉት ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖችና የፖሊስ አባላት፡-

1. ሌ/ጀኔራል ታደሰ ወረደ ተስፋዬ (ወዲወረደ)
2. ሜ/ጄኔራል ዮሐንስ ወ/ጎርጊስ ተስፋይ (መዲድ)፣
3. ሜ/ጄኔራል ብርሃነ ነጋሽ በየነ (ወዲመድህን)፣
4. ብ/ጄኔራል ሀ/ስላሴ ግርማይ ገ/ሚካኤል
5.ብ/ጄኔራል ምግበ ሃይለ ወ/አረጋይ (አባበርሃ፣)
6. ሜ/ጄኔራል ኢብራሂም አብዱልጀሊል መሀመድዙን
7. ብ/ጄኔራል ገ/ኪዳን ገ/ማርያም የእብዮ
8. ሜ/ጄኔራል ገብረ ገ/አድሃና ወ/ዘጉ (ገብረዲላ)
9. ሜ/ጄኔራል ገ/መስቀል ገ/ዮሀንስ /አስቴር/
10. ብ/ጄኔራል አብርሃ ተስፋይ በርሄ /ድንኩል/
11. ብ/ጄኔራል ፍስሃ በየነ (ወርቅአይኑ)
12. ሜ/ጄኔራል ህንፃ ወ/ጎርጊስ ዮሐንስ
13. ብ/ጄኔራል አለፎም አለሙ ወ/ማርያም /ቸንቶ/
14. ብ/ጄኔራል ገ/መስቀል ገ/እግዝያብሄር (ጠቀም)
15. ብ/ጄኔራል ተ/ብርሃን ወ/አረጋዊ
16. ሜ/ጄኔራል አታክልቲ በርሄ ገ/ማርያም
17. ኮሚሽነር መኮንን ካህሳይ ገ/መስቀል (ፅንቡላ) የትግራይ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር
18. ም/ኮሚሽነር መንግስቴ አረጋዊ የትግራይ ክልል ፖሊስ ም/ኮሚሽነር
19. ኮ/ር ጌታቸው ኪሮስ የትግራይ ፖሊስ አመራር የነበረ
20. ም/ኮሚሽነር ግርማይ ከበደ (ማንጁስ/ የፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ዘርፍ ሃላፊ የነበረ
21. ም/ኮሚሽነር ተክላይ ፀሃዬ የፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ዘርፍ ም/ሃላፊ የነበረ
22. ኮ/ር ንጉስ ወ/ገብርኤል የትግራይ ልዩ ሃይል ፖሊስ ሃላፊ፣
23. ኮ/ር ገ/ስላሴ ታፈረ የፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል አመራር የነበረ
24. ኮ/ር ፍስሃ ተ/ማርያም (ወዲአርባ) የፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል አመራር የነበረ
25. ኮ/ር ተስፋዬ ገ/ኪዳን (ተስፋዬ ባንዳ) የፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል አመራር የነበረ
26. ሜ/ጀነራል ገ/መድህን ፍቃዱ ሃይሉ (ወዲ ነጮ) በቁጥጥር ስር የዋሉ
27. ሜ/ጀነራል ይርዳው ገ/መድህን ገ/ፃድቅ(አስቴር)በቁጥጥር ስር የዋሉ
28. ብ/ጀነራል ገ/ህይወት ሲስኖስ ገብሩ በቁጥጥር ስር የዋሉ
29. ብ/ጀነራል ኢንሶ እጃጆ እራሾ በቁጥጥር ስር የዋሉ
30. ብ/ጀነራል ፍስሃ ገ/ስላሴ እንሁን በቁጥጥር ስር የዋሉ
31. ኮ/ል ደሳለኝ አበበ ተስፋዬ በቁጥጥር ስር የዋሉ
32. ኮ/ል እያሱ ነጋሽ ተሰማ በቁጥጥር ስር የዋሉ

በመጨረሻም የጁንታው ሕወሓት ወንበዴ ቡድን ተፈላጊዎችን በዝርዝር እየገለፅን የምንሄድ መሆኑን በዚህ አጋጣሚ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን እናሳውቃለን፡፡

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Left Column, News, Politics Tagged With: operation dismantle tplf

Reader Interactions

Comments

  1. GI haile says

    November 12, 2020 05:04 pm at 5:04 pm

    የሕወኣትና የጌታቸው አሰፋ የ27 ኣመት የአፈና፣የግዲያና የዘረፋ ተቋም በመጨረሻ የእስርና ክስ መመስረቱ እጅግ ትልቅ እርምጃ ነው። Finally Justice will be served. TPLPTerrorist and their diabolical act the violations of human rights and treason. Thanks to The federal Armed forces and Federal Governments decisions to bring terrorists to Justice.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule