• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በርካታ ቁጥር ያለው የህወሓት የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ሥር ዋለ

November 17, 2020 02:00 am by Editor Leave a Comment

ታጣቂው ህወሓት ልዩ ኃይል በሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ በአማራ ልዩ ኃይልና በሚሊሻ አባላት እየተደመሰሰ ይገኛል።

በዚህ ታላቅ ጀብድ ሰራዊቱ የህወሓት ስግብግብ ኃይል ለጦርነት እየተጠቀመባቸው የነበሩ ከ230 በላይ ክላሽንኮቭ፣ ከ1 ሺህ በላይ የእጅ ቦምብና ሌሎች ተተኳሽ መሳሪያዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የደቡብ ዕዝ የሰው ሐብት ልማትና የሚዲያ አስተባባሪ ኮሎኔል ደጀኔ ጸጋዬ ተናግረዋል።

እየተካሄደ ባለው ህግ የማስከበር ለህልውና ዘመቻ የአማራ ልዩ ኃይልና የሚሊሻ አባላት በተሰጣቸው ቀጣና በጠላት ላይ ከባድ ወታደራዊ ጥቃት በመፈጸምና በመደምስስ ግዳጃቸውን በብቃት እየፈጸሙ መሆኑንም ማመላከታቸውን ፋና ዘግቧል።

በሌላ በኩል በጋምቤላ ከልል ዲማ ወረዳ በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 5 ክላሽንኮቭ የጦር መሳሪያና አንድ F1 የእጅ ቦንብ ከስድስት ተጠርጣሪ ጋር መያዙን ፖሊስ አስታወቀ።

የጦር መሳሪያው ሰሞኑን ከደቡብ ሱዳን ድንበር ወደ ዲማ ወረዳ በማስገባት ሊሸጥ ሲል ነው በቁጥጥር ስር የዋለው።

ከጋምቤላ ፕሬስ ሴክሬታሪያት ጽህፈት ቤት (ህዳር 7/2013 ዓ.ም) የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ፈጥኖ ዋና ሳጂን ጋዲሳ ቶሎሳ እንዳሉት በወረዳው በተለያዩ ጊዜያት ህገወጥ የጦር መሳሪያ እንደሚያዝ አስታውሰው በዚህ ድርጊት የሚሳተፉ አካላት ላይ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ገልፀዋል።

ሰሞኑን በቁጥጥር ስር የዋለው የጦር መሳሪያ ከደቡብ ሱዳን ድንበር አካባቢ ወደ ዲማ ሊገባ ሲል በህብረተሰብ ጥቆማ መያዙን አስታውቀዋል።

የክልሉንና የሃገሪቱን ሰላም የማይፈልጉ አካላት አላማቸውን ለማሳካት የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን ሊያካሂዱ ስለሚችሉ ሁሉም አካባቢውን ነቅቶ መጠበቅ እንደሚኖርበት ማመልታቸውን የፕሬስ ሴክሬታሪያት ጽ/ቤቱ አስታውቋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule