የመከላከያ ጥምር ሀይልና ህዝቡ አሸባሪው ቡድን ሰርጎ በገባባቸው አካባቢዎች እንደ እግር እሳት እየፈጀው እንደሚገኝ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ። የፌዴራል መንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ የሽብር ቡድኑ ለከፈተው አገርን የማፍረስ ጦርነት ለመመከት ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በርካታ ቁጥር ያለው ህዝብ በከፍተኛ ቁጭትና ወኔ ወደ ግምባር እየዘመቱ ይገኛሉ ብለዋል። የመከላከያ ጥምር ሀይልና ህዝቡ አሸባሪው ቡድን ሰርጎ በገባባቸው አካባቢዎች እንደ እግር እሳት እየፈጀው እንደሚገኝም ገልጸዋል። አሸባሪው ቡድን ሰርጎ ቢገባም አይወጣም ያሉ የደሴ ወጣቶች "እንደገና" ብለው በመደራጀት አሸባሪውን እየቀጡትና አካባቢያቸውንም በንቃት እየጠበቁ መሆናቸውን አስታውቀዋል። (ኢፕድ) ከዚሁ ጋር … [Read more...] about “የመከላከያ ጥምር ኃይልና ህዝቡ አሸባሪውን ቡድን እንደ እግር እሳት እየፈጁት ነው”
ethiopian terrorists
በቤኒሻንጉል ከትህነግና ሸኔ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት የነበራቸው 98 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከአሸባሪዎቹ ህወሓት እና ሸኔ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት የነበራቸው 98 ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ፖሊስ አስታወቀ፡፡ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽነር አብዱልአዚም መሐመድ ዛሬ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከመውጣቱ አስቀድሞ የክልሉ ፖሊስ የተጠናከር የክትትል ስራ ሲያካሂድ ቆይቷል፡፡ ኮሚሽነሩ እንዳሉት በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጥቅምት 23 ቀን 2014 ዓ.ም ወጥቶ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ የጸደቀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የክልሉን ሠላም ለማስጠበቅ ለፀጥታ አስከባሪ ኃይሉ ተጨማሪ አቅም ሆኖታል። ግለሰቦቹ በሕግ ቁጥጥር ስር የዋሉት ከአሸባሪዎቹ ህወሓት እና ሸኔ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት እንደነበራቸው ፖሊስ በደረሰው መረጃ መሰረት ከጥቅምት 21 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ባደረገው ኦፕሬሽን ነው ብለዋል፡፡ አሸባሪው … [Read more...] about በቤኒሻንጉል ከትህነግና ሸኔ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት የነበራቸው 98 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ
“የዛሬዋ ኢትዮጵያ አይደለም የትላንትናውን ትህነግ የዘመነውን ትህነግ ለመቀበል አትችልም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ
* "በወሎ ግንባር በነበረው ውጊያ ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ ኃይሎች ተሳትፈዋል" * የ፷፪ ዓመት ሽማግሌ ከትግራይ ለትህነግ ዘምቷል በወሎ ግንባር በነበረው ውጊያ ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ ኃይሎች ከአሸባሪው ቡድን ጋር መሳተፋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታወቁ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በጦርነቱ ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ እና የኢትዮጵያውያ ዝርያ የሌላቸው ነጮች እና ጥቁሮች ከአሸባሪው ቡድን ጋር ተሳትፈው መስዋትነት መክፈላቸውን ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያረጋገጡት። “በወሎ ግምባር በነበረው ውጊያ ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ ኃይሎች ተሳትፈውበታል። የኢትዮጵያ ዝርያ የሌላቸው ሰዎች ተሳትፈው መስዋዕትነት ከፍለዋል። ኢትዮጵያዊ ያልሆነ ሰው ኢትዮጵያ መጥቶ በደሴ … [Read more...] about “የዛሬዋ ኢትዮጵያ አይደለም የትላንትናውን ትህነግ የዘመነውን ትህነግ ለመቀበል አትችልም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ
ደሴ በወገን እጅ – መከላከያ እየገፋ ነው!
ደሴን ለመውረር አሰፍስፎ የነበረ አሸባሪው የህወሃት ወራሪ ኃይል አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቷልበወሎ ዩኒቨርሲቲ ፎቶ ለመነሳት ገብቶ የነበረ የጥፋት ቡድኑ ፎቶ ናፋቂም ባለበት አፋጣኝ እርምጃ በመውሰድ እስከወዲያኛው ተሸኝቷልየደሴ ከተማና አካባቢዋን ተቆጣጥረናል በማለት ጮኸው የሚያስጮሁ የወራሪው ወሬ አራጋቢዎችም በስፍራው እየተፋለሙ የሚገኙትን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ወኔና ጀግንነት አልተረዱም ልዩ መረጃ፤ ከጥቂት ደቂዎች በፊት ጎልጉል እንዳረጋገጠው ደሴን ያረጋጋው መከላከያ ሠራዊት፣ ልዩ ኃይል፣ ሕዝባዊ ሚሊሻና ፋኖ በርካታ አካባቢዎችን እየተቆጣጠረና በወገን እጅ ሥር እያደረጋቸው ይገኛል። በዚህም ጠላት በከፍተኛ ሁኔታ እየተደመሰሰና እየሸሸ እንደሆነ ለማረጋገጥ ችለናል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ መንግሥት የትግራይ ሕዝብ ላለቁት ልጆቹ ትህነግን ለመጠየቅ እንዲዘጋጅ … [Read more...] about ደሴ በወገን እጅ – መከላከያ እየገፋ ነው!
ስድስተኛው የአየር ጥቃት ተደርጓል፤ አየር ኃይሉ ብቃቱን አስመስክሯል
ዛሬ መቀሌ ኵሃ አካባቢ የሚገኘው የልዩ ኃይል ፖሊስ ማሠልጠኛ ተቋም በአየር ኃይል ተመቷል። ይህ ተቋም በአሁኑ ወቅት በርካታ የሽብር ቡድኑ ታጣቂዎች እየሰለጠኑበት ያለ ተቋም መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታውቋል። በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ የተጠኑና ወራሪው ሽብርተኛው ህወሓት ወያኔ መሳሪያ በማከማቸት የጦር ስልጠና የሚሰጥበት ቦታ ላይ የኢትዮጵያ አየር ሀይል ለ6 ተኛ ዙር ዛሬ የአየር ጥቃት አድርሷል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ባደረጋቸው የአየር ጥቃቶች ኢላማውን አግኝቶ መምታቱና የጠላትን ወታደራዊ ይዞታዎችን ለይቶ ከጥቅም ውጪ ማድረጉ ስኬታማነቱንና በቂ ሥልጠና እንዳለው እንደሚያሳይ የቀድሞ ሠራዊት አባል ብርጋዴር ጀነራል መስፍን ኃይሌ ገለጹ። ብርጋዴር ጀነራል መስፍን በተለይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ አየር … [Read more...] about ስድስተኛው የአየር ጥቃት ተደርጓል፤ አየር ኃይሉ ብቃቱን አስመስክሯል
ለሸኔ የጦር መሣሪያዎችን በድብቅ ለማስተላለፍ የሞከሩ ተያዙ
የሽብር ተግባር ለመፈጸምና የተለያዩ የጦር መሣሪያዎችን በድብቅ ለማስተላለፍ የሞከሩ የሸኔ ቡድን አባላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ለኢቢሲ በላከው መግለጫ እንዳመለከተው፣ ሽብርተኛው ሸኔ በንፁሃን ዜጎች እና በፀጥታ አካላት ላይ ግድያ እንዲፈፅሙ መልምሎ እና ስልጠና ሰጥቶ ለጥፋት ተልዕኮ ካሰማራቸው ግለሰቦች መካከል በስሩ 5 የገዳይ ቡድን አባላትን በማደራጀት በህቡዕ ሲንቀሳቀሰ የነበረው ጃፋር መሐመድ ሳኒ የተባለው ተጠርጣሪ በተደረገበት ጥብቅ ክትትል በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡ ይህ የሸኔ ታጣቂ በቁጥጥር ስር የዋለው በስሩ ካደራጃቸው 5 ግብረ አበሮቹ ጋር በምዕራብ ሐረርጌ ዞን ኦዳ ቡልቱም ወረዳ ሚደግዱ ቀበሌ እና ቦረማ ጫካ እንዲሁም ዳሮ ለቡ ወረዳ ሚጨታ እና በዴሳ ከተማ ውስጥ በንፁሃን ዜጎች እና በመንግሥት ፀጥታ … [Read more...] about ለሸኔ የጦር መሣሪያዎችን በድብቅ ለማስተላለፍ የሞከሩ ተያዙ
የመቀሌ አየር ድብደባዎች ዒላማቸውን የመቱ ናቸው
የመከላከያ ሠራዊት ያካሄዳቸው የአየር ድብደባዎች ዒላማ ያደረጉት የህወሓት የጦር መሣሪያ ማምረቻ እና የጦር ትጥቅ ጥገና ጣቢያዎች ላይ ብቻ እንደሆነና ኢላማቸውን የመቱ መሆናቸው ተገለጸ፡፡ የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ መረጃ ማጣሪያ ገጽ ባወጣው መግለጫ፤ የመከላከያ ሠራዊት ያካሄዳቸውን የአየር ድብደባዎች በተመለከተ የተዛባ ግንዛቤ ቢኖርም፣ በተቃራኒው ጥቃቶቹ ዒላማ ያደረጉት የህወሓት የጦር መሣሪያ ማምረቻ እና የጦር ትጥቅ ጥገና ጣቢያዎችን ብቻ ነው ብሏል። የመከላከያ ሠራዊት የሚያከውናቸው እነዚህ ሥራዎች የሽብር ድርጅቱ ከባድ የጦር መሣሪያዎችን እና ሌሎች ሕገወጥ የጦር መሣሪያዎችን ለመሸሸግ የሚጠቀምባቸውን እና ወደ ወታደራዊ መገልገያነት የቀየራቸውን የተወሰኑ ቦታዎች ከጥቅም ውጭ ለማድረግ ያለመ ነው ሲልም አስታውቋል። ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about የመቀሌ አየር ድብደባዎች ዒላማቸውን የመቱ ናቸው
ትህነግ የዛሪማን መስጊድ አወደመ
አሸባሪው ህወሓት በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን የዛሪማ መስጊድን በከባድ መሳሪያ ደብድቦ ማውደሙን የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት አረጋ ገጠ። አሸባሪ ቡድኑ የፈጸመው ድርጊትም የሰዎችን እምነት የሚጋፋ መሆኑን ምክር ቤቱ ገልጿል። የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ዋና ፀሐፊ ሀጂ ሙሀመድ ሀሰን፣ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለፁት፣ በሰሜን ጎንደር ውስጥ በሚገኘውና በቅርብ በተገነባው የዛሪማ መስጊድ ላይ በከባድ መሳሪያ ተኩሶ መስጊዱን በከፊል አውድሟል። በአካባቢው አሸባሪው ቡድን ሸሽቶ ጫካ በመግባቱና ደብቆ ባከማቸው የከባድ መሳሪያ ከርቀት በማስወንጨፍ በዛሪማ መስጊድና በአካባቢው በሚገኙ ቤተ-እምነቶችና ንፁሀን ላይ ጉዳት እያደረሰ እንዳለ ገልጸዋል። አሸባሪ ቡድኑ የፈጸመው ተግባርም ለእምነት ክብር እንደማይሰጥ አንዱ ማሳያ መሆኑንም … [Read more...] about ትህነግ የዛሪማን መስጊድ አወደመ
በወለጋ የሰፈሩ ኦሮሚኛ ተናጋሪ ትህነጎችና የሸኔ ግፍ
በምስራቅ ወለጋ ዞን ኪረሙ ወረዳ ሀሮ ከተማ ፅንፈኛው የአሸባሪ ቡድን ሸኔ ጥቅምት 1 እና 2 በንፁሃን ላይ በከፈተው ጥቃት በሰው ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን የኦሮሚያ ክልል የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል። ቡድኑ ከህውሃት የሽብረ ቡድን ጋር ህብረቱን ካረጋገጠ በኋላ በብሄር ብሄረሰቦች ላይ ትንኮሳ በማድረግ ግጭቶችም የብሄር መልክ እንዲይዙ እየሰራ ይገኛል ብለዋል የቢሮው ኃላፊ አቶ ሀይሉ አዱኛ። ኃላፊው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለፁት ሸኔ በአካባቢው ከሚንቀሳቀስ ሌላ የሽፍታ ቡድን ጋር በመተባበር በሀሮ ከተማ በከፈተው ጥቃት የ15 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ የንብረት ውድመት እንዳደረሰ እንዲሁም 967 አባወራዎች ከቤት ንብረታቸው እንደተፈናቀሉ ተናግረዋል። የክልሉ መንግስት ተጨማሪ የፀጥታ ሀይል ወደ ስፍራው በማሰማራት ወረዳውን እና ከተማውን … [Read more...] about በወለጋ የሰፈሩ ኦሮሚኛ ተናጋሪ ትህነጎችና የሸኔ ግፍ
እያፈገፈገ ያለውን ሽፍታ የሚመራው ፃድቃን ጦርነቱ “በቀናት፣ ግፋ ቢል በሳምንታት ይጠናቀቃል” አለ
የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር / ትህነግ አማጺ ሃይል መሪ የሆነው ጻድቃን ገብረትንሳይ ጦርነቱ እንደማይራዘም አመለከተ። አዲስ ተጀመረ የተባለውን ጦርነት “የቀናት ጉዳይ ነው፣ ግፋ ቢል በሳምንታት ውስጥ ይጠናቀቃል” ሲል የተናገረው ለኒውዮርክ ታይምስ ነው። የትግራይ ሕዝብ የዕድሜ ልክ ጠላት ሲሉ የጠራቸው ኢሳያስ መወገድ እንዳለባቸው ለዓለም ማህበረሰብ አስታውቋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት እስካሁን ማጥቃት አለመጀመሩን፣ ነገር ግን ዝግጅቱን አጠናቆ መመሪያ እየጠበቀ መሆኑንና ማጥቃት ከጀመረ “ድረሱልኝ” የሚል ጊዜ የሚሰጥ እንዳልሆነ ከዚህ በፊት ሲነገር ነበር። ትህነግ ያወጣውን የድረሱልኝ ጥሪ ተከትሎ መከላከያ ይህንን ቢልም የተለያዩ ሃላፊዎችና ዓለም ዓቀፍ ሚዲያዎች ደጋግመው ጥቃት መጀመሩን እያስታወቁ ነው። የአየር ሃይል አዛዥም በባንዲራ ቀን አየር ኃይል “ጠላትን … [Read more...] about እያፈገፈገ ያለውን ሽፍታ የሚመራው ፃድቃን ጦርነቱ “በቀናት፣ ግፋ ቢል በሳምንታት ይጠናቀቃል” አለ