ወ/ሮ ውዴ በለጠ ይባላሉ። ነዋሪነታቸው ጎንደር ከተማ ቀበሌ 17 ነው። ሀገሬ በችግር ውስጥ ሆና እኔ በድሎት አልኖርም በማለት ልጆቻቸው ለቀለብ ብለው ከሚሰጧቸው ጥቂት ገንዘብ እየቆጠቡ ለሰራዊት አባላት በግላቸው ስንቅ አዘጋጅተው አቅርበዋል። ወ/ሮ ውዴ የልጆቻቸውን እጅ ጠብቀው የሚኖሩ እናት ቢሆኑም ለህልውና ዘመቻ የሀገርን ክብርና የወገንን ህልውና ለማስጠበቅ ግንባር ለተሰለፉ የመከላከያ ሰራዊት አባላት፣ የአማራ ልዩ ሀይል፣ ሚሊሻና ፋኖ ይሁንልኝ ሲሉ 3 ኩንታል በሶ አዘጋጅተው ድጋፍ አበርክተዋል። ግለሰቧ “ከዚህ በፊትም ልጆቼ በቻሉት አቅም ግንባር ለዘመቱ ወገኖቻቸው ድጋፍ አድርገዋል” ይላሉ። “አሁን ደግሞ የኔ ተራ ነው፤ ከወር ቀለቤ እየቀነስኩ በሰበሰብኳትና ልጆቼ በሰጡኝ ጥቂት ገንዘብ ይህንን አድርጌያለሁ” አሉ። እኔ በሰላም ወጥቼ እንዲገባ እነሱ ህይወታቸውን … [Read more...] about ከልጅ እጅ ጠብቀው፥ ከሚያገኙት ቀንሰው ለወገን ጦር ድጋፍ የቸሩ እናት
ethiopian terrorists
ከ20 ቤተሰብ የመጡ 40 ወንድማማቾችና እህትማማቾች በአንድ ላይ ዘመቱ
አሸባሪውን ህወሓት የፈጸመውን ወረራ በመቀልበስ ኢትዮጵያን ለማዳን ከ20 የተለያዩ ቤተሰቦች 40 ወንድማማቾችና እህትማማቾች በአንድ ላይ ዘምተዋል። እነዚህ የኢትዮጵያ ዘማቾች ያለፈው ረቡዕ መስከረም 12፤2014ዓም ከደሴ ከተማ ወደ ስልጠና ማዕከል ሽኝት ተደርጎላቸዋል። (ኢፕድ) ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about ከ20 ቤተሰብ የመጡ 40 ወንድማማቾችና እህትማማቾች በአንድ ላይ ዘመቱ
በስልኩ ብቻ 15 የጁንታ ታጣቂዎችን ማርኮ፤ 40ዎቹን እንዲደመሰሱ ያደረገው ጀግና
ሰፊው በቀለ ናደው ይባላል። በደቡብ ጎንደር ዞን ላይ ጋይንት ወረዳ ቀበሌ 03 ነዋሪ ሲሆን፤ ውልደትና እድገቱ ምንጭ ውሃ በሚባል አካባቢ ነው። ጁንታው ከነ ጀሌዎቹ ወደ ሥፍራው በመጣ ጊዜ ለኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትና ለአማራ ልዩ ኃይሉ ስንቅና ትጥቅ በማቀበል ጉልህ አስተዋጽኦ አበርክቷል። ብዙ ተጋድሎም ፈጽሟል። አባቱ ሻምበል በቀለ ናደው የቀድሞ ሰራዊት አባል ሲሆኑ፣ አያቱም ታሪክ እንዳላቸውና የእነርሱን ታሪክ ለመድገም ቆርጦ መነሳቱን ያስታውሳል። በዚህም ያለ ጥይትና ያለ ክላሽ በያዛት ስልክ ብቻ ጠላቱን እንደተዋጋ ይናገራል። ኦፕሬሽኑን ለሚመሩት አካላት ጠላትን እየተከታተለ መረጃ በመስጠት ትልቅ ጀብዱ ፈጽሟል። ሰፊው የሹፍርና ሙያ ያለው ሲሆን፣ ጁንታዎች በመንገድ ቢያገኙት መታወቂያውን አይተው መኪና ሊያስነዱት እንደሚችሉ በማመኑ በመታወቂያው ላይ “ሹፌር” የሚለውን … [Read more...] about በስልኩ ብቻ 15 የጁንታ ታጣቂዎችን ማርኮ፤ 40ዎቹን እንዲደመሰሱ ያደረገው ጀግና
“የአማራ ክልል ልዩ ኃይል ሲተኩስ ከአንገት በላይ መምታት እንዳለበት አምኖ ነው”
በጋሸና ግንባር የሚገኙ የአማራ ክልል ልዩ ኃይል አባላት በጠላት ላይ የላቀ የበላይነት እያገኙ እንደሆነ አባላቱና መሪዎቹ ተናግረዋል። ሳጅን ካሳዬ ወርቁ በጋይንት ግንባር ያለው የአማራ ልዩ ኃይል ተጋድሎ አኩሪ እንደነበረ ተናግሯል። ልዩ ኃይሉ ከጋሳይ ጀምሮ እስከ ደብረ ዘቢጥ ጀብድ ፈጽሟል ብሏል። የሀገር መከላከያ ሠራዊትና ልዩ ኃይሉ አሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድንን በተቀናጀ መልኩ እንደደመሰሱት ገልጿል። ጠላት ከፍተኛ ሰብዓዊ ጉዳት የደረሰበት ሲሆን በርካታ የጦር መሳሪያዎችን ለማስረከብ እንደተገደደም አስረድቷል። ኮንስታብል አሳልፍ ተመሰለው ልዩ ኃይሉ ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ጋር በመቀናጀት የአሸባሪው ትህነግ ወራሪ ቡድንን እንደደመሰሱት ተናግሯል። የአማራ ብሎም የኢትዮጵያ ሕዝቦች ከአሸባሪው ትህነግ ወራሪ ቡድን ነፃ እስኪሆኑ ድረስ ተጋድሏቸውን እንደሚቀጥሉ ነው … [Read more...] about “የአማራ ክልል ልዩ ኃይል ሲተኩስ ከአንገት በላይ መምታት እንዳለበት አምኖ ነው”
5 ሚሊዮን “የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት” ዘመቻ ተጀመረ
ኢትዮጵያ የያዘችውን እውነታ ለዓለም የማስረዳትና የአሸባሪውን ህወሃት የጥፋት ድርጊት ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ማሳየትን አላማ ያደረገው "የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት" ዘመቻ በይፋ ተጀምሯል። ዘመቻው ይፋ ሲደረግ ሚኒስትሮች፣ የተለያዩ ታዋቂ ግለሰቦችና በርካታ ወጣቶች መገኘታቸውን ኢዜአ ዘግቧል። "የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት" ዘመቻ ከዛሬ ጀምሮ አስከ መስከረም 15 ቀን 2014 ዓ.ም የሚካሄድ መሆኑ ታውቋል። “በኢትዮጵያ ላይ በተሳሳተ መልኩ የሚነዛው አሉባልታ ከእውነት የራቀ መሆኑን ለዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ ለማሳየት በዘመቻው ይሰራል” ተብሏል። በዚሁ ንቅናቄ ኢትዮጵያ የያዘችውን እውነታ ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እንዲደርስ ይሰራል ተብሏል። በዚህ ዘመቻ ከ5 ሚሊዮን በላይ ወጣቶች እንደሚሳተፉ ይጠበቃል። በሌላ በኩል … [Read more...] about 5 ሚሊዮን “የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት” ዘመቻ ተጀመረ
ሃብትና ቀለባቸው በትህነግ ወራሪ ተዘርፎ የዕለት ጉርስ አልባ የሆኑት እማሆይ ሲሳይ ዋጋው
እማሆይ ሲሳይ ዋጋው የደብረ ዘቢጥ ከተማ ነዋሪ ናቸው። የዛሬን አያድረገውና በየዓመቱ የዘመን መለወጫ በዓል ሲመጣ ቤት ያፈራውን በማዘጋጀት በዓሉን በደስታ ያከብሩ ነበር። “የዘመን መለወጫ ለእኔ ልዩ በዓል ነበር” ያሉት እማሆይ ሲሳይ አሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድን ከተማቸውን በወረረበት ወቅት ሀብትና ቀለባቸው በመዝረፉ በዓልን አስፈላጊውን ነገር አዘጋጅቶ በደስታ ማሳለፍ ቀርቶ የዕለት ጉርስ ማጣታቸውን ተናግረዋል። እማሆይ ሲሳይ እንዳሉት የእሳቸው ንብረት ብቻ ሳይሆን የቀበሌው ነዋሪዎች ሁሉ በሽብር ቡድኑ በመዘረፉ ችግሩን የበለጠ የከፋ ያደርገዋል። “ይህ ክፉ ጊዜ ይለፍ እንጅ በዓል ሁሌም ይደረሳል። ብቻ ሀገራችንን ሰላም ያድርጋት” ነው ያሉት። አሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድን ከተማቸውን በወረረበት ወቅት አቅም በሌለው ጉልበታቸው ወደ ጫካ ገብተው … [Read more...] about ሃብትና ቀለባቸው በትህነግ ወራሪ ተዘርፎ የዕለት ጉርስ አልባ የሆኑት እማሆይ ሲሳይ ዋጋው
የሽብርተኛው ትህነግ ግፍና በደል በዛሪማ
አሸባሪው የህወሓት ቡድን በዛሪማና አካባቢው ሰርገው በገቡባቸው ቀናት የተለያዩ ግፍና በደሎች መፈፀማቸውን ተጎጂ የከተማዋ ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ በዛሪማ ከተማ የሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ የተከራየውን ንብረትነቱ የኪዳነምህረት ገዳም የሆነ ህንፃ የሚቆጣጠሩት አባ ገብረማርያም ሳሙኤል እንደተናገሩት፣ አሸባሪ ቡድኑ እኔን እንኳ በአባትነት ሳያከብሩኝ ገፍትረው ጥለው የባንኩን ኤቲኤም ማሽን ሰብረው መዝረፋቸውንና ወደውስጥ በመግባትም የፈለጉትን አድርገው መውጣታቸውን ተናግረዋል፡፡ በዛሪማ ከተማ ተወልደው ያደጉት አቶ ባዬ አትክልት እና አቶ ዳግማዊ ገነነውም የሽብር ቡድኑ ዘራፊዎች የሞቀ ቤታቸውን በማዘጋት ሱቃቸውንና የቤት ውስጥ መገልገያ ቁሳቁሳቸውን እንደዘረፏቸው ገልጸዋል፡፡ ቋንቋና ዘርን እየለዩ አሰቃይተውናል ያሉት አቶ ባዬ እና አቶ ዳግማዊ መሳሪያ … [Read more...] about የሽብርተኛው ትህነግ ግፍና በደል በዛሪማ
የዛሪማን ድልድይ በውስጥ በኩል ቦርቡሮ ፈንጅ ለመደበቅ ያሤረው ጠላት ተደምስሷል
በማይጠብሪ ግንባር የሚገኘው የወገን ጦር ጠላትን እየደመሰሰ ወደ ፊት እየገሰገሰ ነው። በጭና ቆርጦ ደባርቅና ዳባትን ሊይዝ የነበረው የትግራይ ወራሪ ቡድን በጭና እና በተለያዩ አካባቢዎች ድባቅ ተመትቶ አብዛኛው ተደምስሷል። የቀረው ወደ ኋላ በመመለስ ወደ መጣበት እየፈረጠጠ ነው። በግንባሩ የተሰማራው የወገን ጦርም እየተከታተለ እየደመሰሰው ነው። በግንባሩ የክፍለ ጦር አዛዥ እንደነገሩን ሠራዊቱ በቦዛ፣ በጭና፣ በብና እና በተለያዩ አካባቢዎች ከባድ ጦርነት ማድረጉን ነው የተናገሩት። በተደረገው ጦርነትም የጠላት ቡድን ተደምስሷል። በዛሪማና በድብ ባሕር አድርጎ ወደ ሊማሊሞ ሊወጣ የነበረው አሸባሪ ቡድንም በወገን ጦር ተመትቷል ነው ያሉት። ከድብ ባሕር እስከ ዛሪማ እየተቀጠቀጠ አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቶ መመለሱን ነው የተናገሩት። ጠላት መልሶ እንዳይቋቋም ካደረጉት ምቶች መካከል … [Read more...] about የዛሪማን ድልድይ በውስጥ በኩል ቦርቡሮ ፈንጅ ለመደበቅ ያሤረው ጠላት ተደምስሷል
CNN ትህነግን እንደ ማስረጃ ጠቅሶ የሠራው ዘገባና ያፈተለከው ቅሌት
ሲኤንኤን (CNN) “አሰቃቂው ዕይታ” የሚል ርዕስ የሰጠውን እና በሁመራ ተፈፅሟል ያለውን ግርፋት፣ ጅምላ እስር እና ግድያን በተመለከተ የምርመራ ዘገባ አቅርቧል። እነዚህ ግርፋት፣ ጅምላ እስር እና ግድያ የተፈፀሙት “በኢትዮጵያ ሠራዊት እና አጋሮቹ” ሲል በገለጻቸው ኃይሎች መሆኑንም ምስክሮቹን ጠቅሶ ደምድሟል። የዚህ የምርመራ ዘገባ መነሻ የሆነው በሱዳን ድንበር አካባቢ በሚገኝ ወንዝ ላይ የሚንሳፈፉ አስከሬኖች ዳግም መገኘታቸው እንደሆነ ሚዲያው ጠቅሷል። ኒማ ኤልባጊር ይሁን እንጂ የዘገባው አዘጋጅ የሆነችው ሱዳናዊቷ ጋዜጠኛ ኒማ ኤልባጊር ለምስክርነት የመረጠቻቸው ሰዎች ገለልተኛ አለመሆን እና የአሸባሪው ህወሓት ቡድን ደጋፊዎች መሆናቸው የዘገባውን ተዓማኒነት አጠያያቂ አድርጎታል። በተለይ ተፈፅመዋል የተባሉትን ግድያዎች በዝርዝር የሚናገረው እና የሞቱ ሰዎች … [Read more...] about CNN ትህነግን እንደ ማስረጃ ጠቅሶ የሠራው ዘገባና ያፈተለከው ቅሌት
ሲራጅ ዲቢል አሊ 5 ገድለው 6 ክላሽ የማረኩ የድሬ ሮቃው ጀግና
ስማቸው ሲራጅ ዲቢል አሊ ይባላሉ። በሀብሩ ወረዳ 024 ድሬ ሮቃ ቀበሌ ነዋሪ ናቸው። ከሰሞኑ አሸባሪው የትህነግ ወራሪ ቡድን ወደ ቀበሌያቸው ለመግባት ሲሞክር ቀበሌያቸውን ባለማስደፈር ታላቅ ጀብዱ ሰርተዋል። በሚኖሩበት ድሬ ሮቃ ቀበሌ ግንባር ላይ በመሰለፍ አንድ የአሸባሪው ቡድን አባል በወገን ጦር ላይ ጥቃት ለመፈፀም ሲሞክር በድንጋይ አንገቱን ብለው የያዘውን ክላሽ ማርከውታል። ከዚያም ሌሎች አምስት የአሸባሪው ቡድን አባላት ጓደኛቸውን ለማንሳት ሲመጡ አምስቱንም በመግደል የያዙትን አምስት ክላሽ በመማረክ በአጠቃላይ 6 ክላሽ ከአሸባሪው ትህነግ ወራሪ ቡድን መማረክ ችለዋል። በሃይማኖቴ እና በኢትዮጵያዊነቴ አልደራደርም የሚሉት አቶ ሲራጅ ወጣቱ የሀገሩን ሰላም እንዲጠብቅ ጥሪ … [Read more...] about ሲራጅ ዲቢል አሊ 5 ገድለው 6 ክላሽ የማረኩ የድሬ ሮቃው ጀግና