በአዲስ አበባና በአንዳንድ የኦሮሚያ ከተሞች የተቀናጀ የሽብር ጥቃት ለመፈፀም አቅደው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የሽብር ቡድን አባላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የደህንነትና ፀጥታ የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቀ፡፡ የደህንነትና ፀጥታ የጋራ ግብረ ኃይል ለመገናኛ ብዙሃን በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፥ በአዲስ አበባና በአንዳንድ የኦሮሚያ ከተሞች ሁከት፣ ሽብርና ትርምስ በመፍጠር ድብቅ የፖለቲካ አጀንዳቸውን ለማሳካት በሚንቀሳቀሱ የውጭ እና የውስጥ ፀረ-ሰላም ኃይሎች የሚደገፉ የሸብርተኞቹ የህወሓትና የሸኔ ቡድን አባላት በሰው ሕይወትና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ለማድረስ ሴራ ወጥነው ወደ እንቅስቃሴ ለመግባት በዝግጅት ላይ እንዳሉ በጋራ ግብረ ኃይሉ በተደረገባቸው ጥብቅና የተቀናጀ ክትትል በቁጥጥር ስር ውለዋል። ይህን እኩይ የጥፋት ሴራ ለመፈጸም ከውጭ በተለያዩ አካላት በሚደረግላቸው … [Read more...] about የሽብር ጥቃት ለመፈፀም ሲንቀሳቀሱ የነበሩ በቁጥጥር ስር ዋሉ
Archives for May 2021
በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 110 ሺህ ዶላር ከነተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር ዋለ
በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እና በብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በተደረገ ክትትል በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 1 መቶ 10 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ከነተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ በህገ ወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረው ዶላር የተያዘው ሚያዚያ 28 ለ29 አጥቢያ 2013 ዓ/ም በአዲስ አበባ የካ ክፍለ ከተማ ላምበረት መናኸሪያ ግቢ ውስጥ ከለሊቱ 10 ሰዓት ገደማ ነው፡፡ ከአዲስ አበባ ወደ ሃረር ሊጓዙ የተዘጋጁ ሁለት ተጠርጣሪዎች በያዙት ሻንጣ ላይ በተደረገ ፍተሻ በጥቁር ላስቲክ የተጠቀለለ 110 ሺህ የአሜሪካ ዶላር መገኘቱን ፖሊስ ያስታወቀው፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝም የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡ (ኢብኮ) ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 110 ሺህ ዶላር ከነተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር ዋለ
“የአውሮፓ ህብረት የምርጫ ታዛቢዎች ውዝግብን ከመጫር ባሻገር የፈየዱልን አንዳችም ነገር የለም” ፕ/ር በየነ
የአውሮፓ ህብረት የምርጫ ታዛቢዎች መምጣት አለመምጣት በአገራዊው የምርጫ ሂደት ላይ የሚያሳድረው አንዳችም ተጽዕኖ እንደሌለ የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ኢሶዴፓ)ፕሬዚዳንትና የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ አስታወቁ ። ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ በተለይም ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቁት፣ የአውሮፓ ህብረት የምርጫ ታዛቢዎች መምጣት አለመምጣት በአገራዊው የምርጫ ሂደት ላይ የሚያሳድረው አንዳችም ተጽእኖ የለም፤ ምክንያቱም ታዛቢዎች ባሉበት ባለፉት ምርጫዎች ወቅትም ውዝግብን ከመጫር ባሻገር የፈየዱልን አንዳችም ነገር የለም። በተለይም በ1997ቱ ምርጫ ወቅት የአውሮፓ ህብረት ታዘብኩ ብሎ ያወጣው መረጃ እንደ አገር ብዙ ዋጋ የከፈልንበት ብዙ ትርምስ የተፈጠረበት ከመሆኑ አንጻር አሁን ላይ አንመጣም ማለታቸው የሚያጎለው አንዳችም … [Read more...] about “የአውሮፓ ህብረት የምርጫ ታዛቢዎች ውዝግብን ከመጫር ባሻገር የፈየዱልን አንዳችም ነገር የለም” ፕ/ር በየነ
ከ6ሺ ኩንታል በላይ በቆሎ በግለሠብ መጋዘን ውስጥ ተገኘ
በደብረ ማርቆስ ከተማ ከ6ሺ ኩንታል በላይ በቆሎ በአንድ ግለሠብ መጋዘን ውስጥ ተከዝኖ ተገኘ። በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ቀበሌ ዐ5 ልዩ ቦታው ኢንዱስትሪ መንደር ውስጥ በሚገኝ ለሙጫና እጣን ማቀነባበሪያ መጋዘን ውስጥ ከ6ሺ ኩንታል በቆሎ በላይ ተከዝኖ መገኘቱን የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ገልጿል። የተገኘውን እህል በከተማው ለሚገኙ አስራ አራት ሸማች ህብረት ስራ ማህበራት እንደሚከፋፈል እና በዛሬው ዕለት ሁለት ሸማች ማህበራት ከአራት መቶ በላይ ኩንታል መውሰዳቸውን እና ለህብረተሰቡ እንደሚከፋፈል የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ብርሀኑ መኩሪያው ገልጸዋል። የወንጀሉ ጉዳይም ፖሊስ አስፈላጊውን ምርምራ እያጣራ መሆኑን አስረድተዋል። (የደብረ ማርቆስ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት) ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about ከ6ሺ ኩንታል በላይ በቆሎ በግለሠብ መጋዘን ውስጥ ተገኘ
በበጀት ዓመቱ 272 ማንሆል ክዳኖች ተሰርቀዋል – የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን
የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን በበጀት ዓመቱ ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው 272 ማንሆል ክዳን እንደተሰረቀበት አስታውቋል። ባለስልጣኑ በአሁኑ ሰዓት ከ1500 ኪሎ ሜትር በላይ የፍሳሽ መስመሮች በመዲናዋ ተዘርግተዋል ያለ ሲሆን የፍሳሽ መስመሮቹን የፍሰት መቆጣጠሪያነት እና ጽዳት ለመከታተል የሚያስችል ማንሆሎች በመገንባት እንዲከደኑ ቢያደርግም 272 ክዳኖች በህገወጥ ሰዎች ተሰርቀዋል ብሏል። ይህም በፍሳሽ መስመሩ ላይ ባዕድ ነገር እንዲገባ በማድረግ የማጣሪያ ጣቢያዎች ህልውና እየተፈታተነ እንደሚገኝና ከዚህም ባሻገር ህብረተሰቡ ክፍት በሆነ ማንሆል ውስጥ ገብቶ ጉዳት እየደረሰበት እንደሆነ ገልጿል። ድርጊቱ ህገ-ወጥ ድርጊቱ የከተማዋን የዘመናዊ ፍሳሽ አወጋገድ ስርዓት ላይ አደጋ የደቀነ መሆኑን በመረዳት ከምንም በላይ ህብረተሰብ እና የጸጥታ አካላት … [Read more...] about በበጀት ዓመቱ 272 ማንሆል ክዳኖች ተሰርቀዋል – የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን
በአዲስ አበባ በ9 ወራት ከ4 ሚሊዮን ብር በላይ የመንገድ ጉዳት ደርሷል
በመዲናይቱ በ9 ወራት ብቻ ከ4 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የመንገድ ኃብት ላይ ጉዳት ደርሷል። በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ 179 የመንገድ መሰረተ ልማቶች ላይ ጉዳት የደረሰ ሲሆን ይህም በገንዘብ ሲሰላ ከ4 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው ልዩ ልዩ የመንገድ ኃብት ላይ በተሽከርካሪ ግጭት ምክንያት ለጉዳት ተዳርገዋል። ከደረሱት የግጭት አደጋዎች መካከል 45 የሚሆኑት በቀለበት መንገድ ላይ ሲሆን ቀሪዎቹ 134 የሚሆኑት ደግሞ ከቀለበት መንገድ ውጪ የደረሱ አደጋዎች መሆናቸውን የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን አስታውቋል። (tikvahethmagazine) ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about በአዲስ አበባ በ9 ወራት ከ4 ሚሊዮን ብር በላይ የመንገድ ጉዳት ደርሷል
ዓለምአቀፉ አሸባሪ ትክክለኛ ስሙን አገኘ
ድልድይ በማፍረስ፤ መሠረተ ልማቶችን በማውደም ከየቦታው በተለቃቀሙ ወንበዴዎች መሪነት ኢትዮጵያን በነጻ አውጪ ስም በግፍ ሲገዛ የነበረው ህወሃት/ትህነግ ዛሬ ትክክለኛ ስሙን አገኘ። ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት/ትህነግ) በማለት የሚጠራውና በኢትዮጵያ እጅግ አስከፊ የሚባልና ትውልድን ያወደመ ርዕዮት በመከተል አገር ያፈረሰው የወንበዴዎች ጥርቅም፤ እስካሁንም በዓለምአቀፍ የአሸባሪዎች የመረጃ ቋት በአሸባሪነት ተመዝግቦ የሚገኝ ድርጅት መሆኑ ይታወቃል። አባላቱና ደጋፊዎችም በዚሁ ሁኔታ የሚታዩ መሆናቸውን ብዙዎች የሚስማሙበት ነው። ከዚህ በታች የሚገኘው መረጃ በዓለምአቀፉ የአሸባሪዎች ቋት ተመዝግቦ የሚገኝ የህወሃት ወንጀል ዝርዝር ነው። የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ “ህወሓት” እና “ሸኔ” … [Read more...] about ዓለምአቀፉ አሸባሪ ትክክለኛ ስሙን አገኘ
“በተለምዶ ‘ሸኔ’ የሚባለው ራሱን ‘የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት’ ብሎ የሚጠራው ቡድን ነው”
በርካቶች 'ሸኔ' እያለ እራሱን የሚጠራ ድርጅት በሌለበት እንዴት አሸባሪ ተብሎ ይሰየማል ሲሉ ይጠይቃሉ። ይህ ስያሜ አንዳች ነገር ለመሸፈን ተፈልጎ ነው በሚል ጥርጣሬያቸውን የሚገልፁ ምሁራንም አልጠፉም። ለመሆኑ 'ሸኔ' ማነው? በዚህ ጉዳይ ላይ በዛሬው ዕለት የተጠየቁት የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ዶ/ር ጌድዮን ጢሞቲዮስ ተከታዩን ማብራሪያ ሰጥተዋል፦"በተለምዶ 'ሸኔ' የሚባለው እራሱን ደግሞ 'የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት' ብሎ የሚጠራው ቡድን ነው። በምዕራብ ኦሮሚያ፣ በሌሎችም ክልሎች እየተንቀሳቀሰ ጥቃት የሚያደርስ ድርጅት ነው። እራሱ ለእራሱ የሰጠውን ስያሜ ግን እኛ የምናፀድቅበት ምክንያት የለንም፤ ተገቢም አይሆንም ብለን እናምናለን። ይህ ቡድን ከዚህ በፊት እንደ 'ህወሓት' ተመዝግቦ፣ ህጋዊ እውቅና፣ ህጋዊ ሰውነት እና ሰርተፊኬት ኖሮት የሚያውቅ አይደለም፤ … [Read more...] about “በተለምዶ ‘ሸኔ’ የሚባለው ራሱን ‘የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት’ ብሎ የሚጠራው ቡድን ነው”
ሸኔ የሚባል የፖለቲካ ፓርቲ የለም፣ ህወሃትና ሸኔ አሸባሪ መባላቸው ለውጥ አያመጣም፤ መረራ ጉዲና
ውሳኔ ከመዘግየቱ በስተቀር ተገቢ ነው፤ የህግ ባለሙያዎች የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ ተቀዳሚ ሊቀመንበር የሆኑት ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና፣ መንግስት “ሸኔ” እና “ህወሓት” ቡድንን በሽብርተኝነት እንዲፈረጁ ለማድረግ መዘጋጀቱ መሰረታዊ ለውጥ አያመጣም ብለዋል፡፡ እንዲህ አይነት ፍረጃ የቀድሞ መንግስትም ሲያደርገው የነበረ ነዉ የሚሉት ፕሮፌሰሩ፣ ይህ ዓይነቱ ፍረጃ መሰረታዊ ለውጥ የሚያመጣ ቢሆን እዚህ ደረጃ ላይ አንደርስም ነበር፤ ይህም ተግባር ቀድሞ ከነበረው መንግስት የተለየ ነው ብዬ አላስብም ብለዋል ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና፡፡ “ሸኔ የሚባል የፖለቲካ ፓርቲ የለም፣ በኦሮሞ ስም የሚንቀሳቀሱ ሀይሎችን በተዘዋዋሪ መጥራት ይመስለኛል የሚሉት ፕሮፌሰር መረራ በዚህ ስም ራሱን የሚጠራ ድርጅት በሌለበት፣ መንግስት ግን በኦሮሚያ አካባቢ በኦሮሞ ስም የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶችን ኢላማ … [Read more...] about ሸኔ የሚባል የፖለቲካ ፓርቲ የለም፣ ህወሃትና ሸኔ አሸባሪ መባላቸው ለውጥ አያመጣም፤ መረራ ጉዲና