• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሸኔ የሚባል የፖለቲካ ፓርቲ የለም፣ ህወሃትና ሸኔ አሸባሪ መባላቸው ለውጥ አያመጣም፤ መረራ ጉዲና

May 6, 2021 09:14 am by Editor Leave a Comment

ውሳኔ ከመዘግየቱ በስተቀር ተገቢ ነው፤ የህግ ባለሙያዎች

የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ ተቀዳሚ ሊቀመንበር የሆኑት ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና፣ መንግስት “ሸኔ” እና “ህወሓት” ቡድንን በሽብርተኝነት እንዲፈረጁ ለማድረግ መዘጋጀቱ መሰረታዊ ለውጥ አያመጣም ብለዋል፡፡

እንዲህ አይነት ፍረጃ የቀድሞ መንግስትም ሲያደርገው የነበረ ነዉ የሚሉት ፕሮፌሰሩ፣ ይህ ዓይነቱ ፍረጃ መሰረታዊ ለውጥ የሚያመጣ ቢሆን እዚህ ደረጃ ላይ አንደርስም ነበር፤ ይህም ተግባር ቀድሞ ከነበረው መንግስት የተለየ ነው ብዬ አላስብም ብለዋል ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና፡፡

“ሸኔ የሚባል የፖለቲካ ፓርቲ የለም፣ በኦሮሞ ስም የሚንቀሳቀሱ ሀይሎችን በተዘዋዋሪ መጥራት ይመስለኛል የሚሉት ፕሮፌሰር መረራ በዚህ ስም ራሱን የሚጠራ ድርጅት በሌለበት፣ መንግስት ግን በኦሮሚያ አካባቢ በኦሮሞ ስም የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶችን ኢላማ ያደረገ ስያሜ ይመስለኛል” ብለዋል፡፡

ቀድሞ የተለያዩ የመንግስት ባለስልጣናት ኦነግ ሸኔ ብለው የሚጠሩትን ሸኔ ብቻ ማለቱ ለውጥ አይኖረውም ወይ በሚል ለቀረበላቸዉ ጥያቄ፣ ፕሮፌሰር መረራ ብዙም ለውጥ እንደማይኖረው ጠቅሰው “ድሮም ቢሆን ኦነግ ሸኔ ሲባል በዛ ስም የእኛንም ሆነ የኦነግን አባላት ጨምሮ የኦሮሞ አክቲቪስቶች ይታሰሩ ነበር፤ አሁንም ቢሆን ያ ነው እየቀጠለ ያለዉ ብለዋል፡፡

ከዚህ ቀደም በአቶ ዳውድ ኢብሳ በሚመራው ኦነግ ቃልአቀባይ የሆኑት አቶ በቴ ኦርጌሳ እኛን ከሸኔ ጋር የሚያገናኘን ነገር የለም ማለታቸዉ ይታወሳል፡፡

ሌላኛው በአቶ አራርሳ ቢቂላ የሚመራውን ኦነግ ቃል አቀባይ የሆኑት አቶ ቀጀላ መርዳሳ በበኩላቸው ሸኔ በመንግሥት ሰዎች ፕሮፓጋንዳ የተፈጠረ ነው” ካሉ በኋላ ኦነግ የሚለው ስም ከዚህ ተቀጥሎ እንዳይጠራ እየተነጋገርን ነው፤ ምክንያቱም እኛ ከሸኔ ጋር ግንኙነት የለንም፤ የታጠቀ ሰራዊትም የለንም ብለዋል፡፡

አቶ ቀጀላ እንዳሉት ቀደም ሲል ሸኔ ማለት የስራ አስፈጻሚ አባላት የሚጠሩበት እንደነበር አስታውሰው አሁን ላይ ግን የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በሚል እየተጠራ መሆኑን ነግረዉናል፡፡

በጂጅጋ ዮኒቨርስቲ የህግ አማካሪ የሆኑት አቶ ሰለሞን ጓዴ ለጣቢያችን እንዳሉት ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) እና ቀድሞ ኦነግ ‘ሸኔ’ በመባል የሚጠሩት ቡድኖች ህዝባዊ መሰረት ያላቸው እና ብሔር ተኩር ፖለቲካ ስርአትን የሚከተሉ በመሆናቸው ነገሩን ከባድ አድርገውታል ብለዋል፡፡

በዚህ የተነሳም ሀገር ታምሳለች፤ ንጹሀን ዜጎች ህይታቸው አልፏል ንብረት ውድሟል፤አሁን ላይ ግን እንዲህ መቀጠል አይቻልም ነዉ ያሉት፡፡

የሀገር በር ከፍተን መከላከያን መተን ለውጭ ሀይል ሰጥተናል፤ ስለዚህ እነዚህን ሀይሎች ከዚህ በኋላ መፈረጁ የሚጠቅመው እነኚህን ሀይሎች ለመታገል፤ ለመዋጋት እጅ እንዲሰጡ ለማድረግ ምክንያት ይሰጣል ብለዋል አቶ ሰለሞን፡፡

ከዚህ ባሻገርም ከእነዚህ ሀይሎች ጋር በገንዘብም ሆነ በኢንፎርሚሽን አሊያም በቁሳቁስ፤ በአመለካከት ቢሆን ግንኙነት ያላቸውን ሰዎች ለማራቅ ጥሩ አጋጣሚን ይፈጥራል ሲሉ አክለዋል፡፡

ከእነዚህ ሀይሎች በላይ አሸባሪ የለም የሚሉት የህግ አማካሪው አቶ ሰለሞን፣ ወለጋ እና አጣዬ ላይ ምን እየተፈጠረ እንዳለ ይታወቃል፤አሁንም ቢሆን ከእነዚህ ሀይሎች በላይ የገዛ ሀገሩን እያሸበረ ያለ አካል የለም ነዉ ያሉት፡፡

ወሳኔው ከመዘግየቱ ውጪ ተገቢነት ያለው ነው ብለዋል፡፡

ይህ ዘርፈ ብዙ ጥቅም እንዳለው የሚናገሩት የህግ ባለሙያው አቶ ሰለሞን ጥፋተኛውን ከህዝብ እየለዩ ለመቅጣት ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረዉ ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም በአገር ውስጥ ያሉትን ብቻ ሳይሆን ማንኛውም የውጪ አካል ለማስታረቅ ወይም ለመደራደር የሚያደርገውን ጥረት ወንጀል እንደሚያደርገውም ያስረዳሉ።

በተለይም አሜሪካን ጨምሮ የተለያዩ የውጪ መንግሥታት በትግራይ ክልል ያለው ግጭት በስምምነት እንዲቋጭ ሲያቀርቡ የነበሩ ጥያቄዎችን ለመዝጋት የታሰበ ይመስላልም ሲሉም አስረድተዋል። (በያይኔአበባ ሻምበል -Ethio FM 107.8)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Law, Left Column, News, Politics Tagged With: merera gudina, olf, olf shanee, olf shine, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule