• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሸኔ የሚባል የፖለቲካ ፓርቲ የለም፣ ህወሃትና ሸኔ አሸባሪ መባላቸው ለውጥ አያመጣም፤ መረራ ጉዲና

May 6, 2021 09:14 am by Editor Leave a Comment

ውሳኔ ከመዘግየቱ በስተቀር ተገቢ ነው፤ የህግ ባለሙያዎች

የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ ተቀዳሚ ሊቀመንበር የሆኑት ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና፣ መንግስት “ሸኔ” እና “ህወሓት” ቡድንን በሽብርተኝነት እንዲፈረጁ ለማድረግ መዘጋጀቱ መሰረታዊ ለውጥ አያመጣም ብለዋል፡፡

እንዲህ አይነት ፍረጃ የቀድሞ መንግስትም ሲያደርገው የነበረ ነዉ የሚሉት ፕሮፌሰሩ፣ ይህ ዓይነቱ ፍረጃ መሰረታዊ ለውጥ የሚያመጣ ቢሆን እዚህ ደረጃ ላይ አንደርስም ነበር፤ ይህም ተግባር ቀድሞ ከነበረው መንግስት የተለየ ነው ብዬ አላስብም ብለዋል ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና፡፡

“ሸኔ የሚባል የፖለቲካ ፓርቲ የለም፣ በኦሮሞ ስም የሚንቀሳቀሱ ሀይሎችን በተዘዋዋሪ መጥራት ይመስለኛል የሚሉት ፕሮፌሰር መረራ በዚህ ስም ራሱን የሚጠራ ድርጅት በሌለበት፣ መንግስት ግን በኦሮሚያ አካባቢ በኦሮሞ ስም የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶችን ኢላማ ያደረገ ስያሜ ይመስለኛል” ብለዋል፡፡

ቀድሞ የተለያዩ የመንግስት ባለስልጣናት ኦነግ ሸኔ ብለው የሚጠሩትን ሸኔ ብቻ ማለቱ ለውጥ አይኖረውም ወይ በሚል ለቀረበላቸዉ ጥያቄ፣ ፕሮፌሰር መረራ ብዙም ለውጥ እንደማይኖረው ጠቅሰው “ድሮም ቢሆን ኦነግ ሸኔ ሲባል በዛ ስም የእኛንም ሆነ የኦነግን አባላት ጨምሮ የኦሮሞ አክቲቪስቶች ይታሰሩ ነበር፤ አሁንም ቢሆን ያ ነው እየቀጠለ ያለዉ ብለዋል፡፡

ከዚህ ቀደም በአቶ ዳውድ ኢብሳ በሚመራው ኦነግ ቃልአቀባይ የሆኑት አቶ በቴ ኦርጌሳ እኛን ከሸኔ ጋር የሚያገናኘን ነገር የለም ማለታቸዉ ይታወሳል፡፡

ሌላኛው በአቶ አራርሳ ቢቂላ የሚመራውን ኦነግ ቃል አቀባይ የሆኑት አቶ ቀጀላ መርዳሳ በበኩላቸው ሸኔ በመንግሥት ሰዎች ፕሮፓጋንዳ የተፈጠረ ነው” ካሉ በኋላ ኦነግ የሚለው ስም ከዚህ ተቀጥሎ እንዳይጠራ እየተነጋገርን ነው፤ ምክንያቱም እኛ ከሸኔ ጋር ግንኙነት የለንም፤ የታጠቀ ሰራዊትም የለንም ብለዋል፡፡

አቶ ቀጀላ እንዳሉት ቀደም ሲል ሸኔ ማለት የስራ አስፈጻሚ አባላት የሚጠሩበት እንደነበር አስታውሰው አሁን ላይ ግን የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በሚል እየተጠራ መሆኑን ነግረዉናል፡፡

በጂጅጋ ዮኒቨርስቲ የህግ አማካሪ የሆኑት አቶ ሰለሞን ጓዴ ለጣቢያችን እንዳሉት ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) እና ቀድሞ ኦነግ ‘ሸኔ’ በመባል የሚጠሩት ቡድኖች ህዝባዊ መሰረት ያላቸው እና ብሔር ተኩር ፖለቲካ ስርአትን የሚከተሉ በመሆናቸው ነገሩን ከባድ አድርገውታል ብለዋል፡፡

በዚህ የተነሳም ሀገር ታምሳለች፤ ንጹሀን ዜጎች ህይታቸው አልፏል ንብረት ውድሟል፤አሁን ላይ ግን እንዲህ መቀጠል አይቻልም ነዉ ያሉት፡፡

የሀገር በር ከፍተን መከላከያን መተን ለውጭ ሀይል ሰጥተናል፤ ስለዚህ እነዚህን ሀይሎች ከዚህ በኋላ መፈረጁ የሚጠቅመው እነኚህን ሀይሎች ለመታገል፤ ለመዋጋት እጅ እንዲሰጡ ለማድረግ ምክንያት ይሰጣል ብለዋል አቶ ሰለሞን፡፡

ከዚህ ባሻገርም ከእነዚህ ሀይሎች ጋር በገንዘብም ሆነ በኢንፎርሚሽን አሊያም በቁሳቁስ፤ በአመለካከት ቢሆን ግንኙነት ያላቸውን ሰዎች ለማራቅ ጥሩ አጋጣሚን ይፈጥራል ሲሉ አክለዋል፡፡

ከእነዚህ ሀይሎች በላይ አሸባሪ የለም የሚሉት የህግ አማካሪው አቶ ሰለሞን፣ ወለጋ እና አጣዬ ላይ ምን እየተፈጠረ እንዳለ ይታወቃል፤አሁንም ቢሆን ከእነዚህ ሀይሎች በላይ የገዛ ሀገሩን እያሸበረ ያለ አካል የለም ነዉ ያሉት፡፡

ወሳኔው ከመዘግየቱ ውጪ ተገቢነት ያለው ነው ብለዋል፡፡

ይህ ዘርፈ ብዙ ጥቅም እንዳለው የሚናገሩት የህግ ባለሙያው አቶ ሰለሞን ጥፋተኛውን ከህዝብ እየለዩ ለመቅጣት ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረዉ ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም በአገር ውስጥ ያሉትን ብቻ ሳይሆን ማንኛውም የውጪ አካል ለማስታረቅ ወይም ለመደራደር የሚያደርገውን ጥረት ወንጀል እንደሚያደርገውም ያስረዳሉ።

በተለይም አሜሪካን ጨምሮ የተለያዩ የውጪ መንግሥታት በትግራይ ክልል ያለው ግጭት በስምምነት እንዲቋጭ ሲያቀርቡ የነበሩ ጥያቄዎችን ለመዝጋት የታሰበ ይመስላልም ሲሉም አስረድተዋል። (በያይኔአበባ ሻምበል -Ethio FM 107.8)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, Left Column, News, Politics Tagged With: merera gudina, olf, olf shanee, olf shine, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule