• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሸኔ የሚባል የፖለቲካ ፓርቲ የለም፣ ህወሃትና ሸኔ አሸባሪ መባላቸው ለውጥ አያመጣም፤ መረራ ጉዲና

May 6, 2021 09:14 am by Editor Leave a Comment

ውሳኔ ከመዘግየቱ በስተቀር ተገቢ ነው፤ የህግ ባለሙያዎች

የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ ተቀዳሚ ሊቀመንበር የሆኑት ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና፣ መንግስት “ሸኔ” እና “ህወሓት” ቡድንን በሽብርተኝነት እንዲፈረጁ ለማድረግ መዘጋጀቱ መሰረታዊ ለውጥ አያመጣም ብለዋል፡፡

እንዲህ አይነት ፍረጃ የቀድሞ መንግስትም ሲያደርገው የነበረ ነዉ የሚሉት ፕሮፌሰሩ፣ ይህ ዓይነቱ ፍረጃ መሰረታዊ ለውጥ የሚያመጣ ቢሆን እዚህ ደረጃ ላይ አንደርስም ነበር፤ ይህም ተግባር ቀድሞ ከነበረው መንግስት የተለየ ነው ብዬ አላስብም ብለዋል ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና፡፡

“ሸኔ የሚባል የፖለቲካ ፓርቲ የለም፣ በኦሮሞ ስም የሚንቀሳቀሱ ሀይሎችን በተዘዋዋሪ መጥራት ይመስለኛል የሚሉት ፕሮፌሰር መረራ በዚህ ስም ራሱን የሚጠራ ድርጅት በሌለበት፣ መንግስት ግን በኦሮሚያ አካባቢ በኦሮሞ ስም የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶችን ኢላማ ያደረገ ስያሜ ይመስለኛል” ብለዋል፡፡

ቀድሞ የተለያዩ የመንግስት ባለስልጣናት ኦነግ ሸኔ ብለው የሚጠሩትን ሸኔ ብቻ ማለቱ ለውጥ አይኖረውም ወይ በሚል ለቀረበላቸዉ ጥያቄ፣ ፕሮፌሰር መረራ ብዙም ለውጥ እንደማይኖረው ጠቅሰው “ድሮም ቢሆን ኦነግ ሸኔ ሲባል በዛ ስም የእኛንም ሆነ የኦነግን አባላት ጨምሮ የኦሮሞ አክቲቪስቶች ይታሰሩ ነበር፤ አሁንም ቢሆን ያ ነው እየቀጠለ ያለዉ ብለዋል፡፡

ከዚህ ቀደም በአቶ ዳውድ ኢብሳ በሚመራው ኦነግ ቃልአቀባይ የሆኑት አቶ በቴ ኦርጌሳ እኛን ከሸኔ ጋር የሚያገናኘን ነገር የለም ማለታቸዉ ይታወሳል፡፡

ሌላኛው በአቶ አራርሳ ቢቂላ የሚመራውን ኦነግ ቃል አቀባይ የሆኑት አቶ ቀጀላ መርዳሳ በበኩላቸው ሸኔ በመንግሥት ሰዎች ፕሮፓጋንዳ የተፈጠረ ነው” ካሉ በኋላ ኦነግ የሚለው ስም ከዚህ ተቀጥሎ እንዳይጠራ እየተነጋገርን ነው፤ ምክንያቱም እኛ ከሸኔ ጋር ግንኙነት የለንም፤ የታጠቀ ሰራዊትም የለንም ብለዋል፡፡

አቶ ቀጀላ እንዳሉት ቀደም ሲል ሸኔ ማለት የስራ አስፈጻሚ አባላት የሚጠሩበት እንደነበር አስታውሰው አሁን ላይ ግን የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በሚል እየተጠራ መሆኑን ነግረዉናል፡፡

በጂጅጋ ዮኒቨርስቲ የህግ አማካሪ የሆኑት አቶ ሰለሞን ጓዴ ለጣቢያችን እንዳሉት ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) እና ቀድሞ ኦነግ ‘ሸኔ’ በመባል የሚጠሩት ቡድኖች ህዝባዊ መሰረት ያላቸው እና ብሔር ተኩር ፖለቲካ ስርአትን የሚከተሉ በመሆናቸው ነገሩን ከባድ አድርገውታል ብለዋል፡፡

በዚህ የተነሳም ሀገር ታምሳለች፤ ንጹሀን ዜጎች ህይታቸው አልፏል ንብረት ውድሟል፤አሁን ላይ ግን እንዲህ መቀጠል አይቻልም ነዉ ያሉት፡፡

የሀገር በር ከፍተን መከላከያን መተን ለውጭ ሀይል ሰጥተናል፤ ስለዚህ እነዚህን ሀይሎች ከዚህ በኋላ መፈረጁ የሚጠቅመው እነኚህን ሀይሎች ለመታገል፤ ለመዋጋት እጅ እንዲሰጡ ለማድረግ ምክንያት ይሰጣል ብለዋል አቶ ሰለሞን፡፡

ከዚህ ባሻገርም ከእነዚህ ሀይሎች ጋር በገንዘብም ሆነ በኢንፎርሚሽን አሊያም በቁሳቁስ፤ በአመለካከት ቢሆን ግንኙነት ያላቸውን ሰዎች ለማራቅ ጥሩ አጋጣሚን ይፈጥራል ሲሉ አክለዋል፡፡

ከእነዚህ ሀይሎች በላይ አሸባሪ የለም የሚሉት የህግ አማካሪው አቶ ሰለሞን፣ ወለጋ እና አጣዬ ላይ ምን እየተፈጠረ እንዳለ ይታወቃል፤አሁንም ቢሆን ከእነዚህ ሀይሎች በላይ የገዛ ሀገሩን እያሸበረ ያለ አካል የለም ነዉ ያሉት፡፡

ወሳኔው ከመዘግየቱ ውጪ ተገቢነት ያለው ነው ብለዋል፡፡

ይህ ዘርፈ ብዙ ጥቅም እንዳለው የሚናገሩት የህግ ባለሙያው አቶ ሰለሞን ጥፋተኛውን ከህዝብ እየለዩ ለመቅጣት ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረዉ ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም በአገር ውስጥ ያሉትን ብቻ ሳይሆን ማንኛውም የውጪ አካል ለማስታረቅ ወይም ለመደራደር የሚያደርገውን ጥረት ወንጀል እንደሚያደርገውም ያስረዳሉ።

በተለይም አሜሪካን ጨምሮ የተለያዩ የውጪ መንግሥታት በትግራይ ክልል ያለው ግጭት በስምምነት እንዲቋጭ ሲያቀርቡ የነበሩ ጥያቄዎችን ለመዝጋት የታሰበ ይመስላልም ሲሉም አስረድተዋል። (በያይኔአበባ ሻምበል -Ethio FM 107.8)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Law, Left Column, News, Politics Tagged With: merera gudina, olf, olf shanee, olf shine, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule