ባሳለፍናቸው ሳምንታት እሁድ ዕለት አንበሳው የብሔራዊ ቡድናችን ያደረገው ለአፍሪካ ዋንጫ የማለፍ ትንቅንቅ በጣም አጓጊና አስደሳች እንደነበር አይተነዋል። ጀግናው ብሔራዊ ቡድናችን የሱዳን አቻውን ሁለት- ለዐልቦ በሆነ ውጤት በዝረራ አሸንፎ እነሆ ከሰላሳ አንድ አመታት በኋላ ለአፍሪካ ዋንጫ እንድናልፍና ልክ አረንጓዴ ጎርፍ ተብለው የሚጠሩት አትሌቶቻችን ሰንደቅ ዓላማችንን ከፍ አድርገን እንድናውለበልብ እንዳደረጉን ሁሉ ዛሬም ብሔራዊ ቡድናችን አፍሪካ ላይ ለጊዜውም ቢሆን መሀሉ ላይ የሰይጣን አምልኮት ምልክት ያለበትን ባለኮከቡን አረንጓዴ ፥ ቢጫና ፥ ቀዩን ሠንደቅ ዓላማችንን እንድናውለበልብ አድርገውልናል፡፡ ምስጋና ይግባቸው ለዋልያዎቹ። ይህን ድል አቶ መለስ በህይወት ኖረው ቢያዩት ደስ ይለኝ ነበር። የሚሉትን ለመስማት፡፡ ግን አፈር ይክበዳቸውና የሉም። ሀገራችን ኢትዮጵያን … [Read more...] about አስደሳቹ የብሔራዊ ቡድን ውጤትና ቅሌት
Archives for October 2012
ዳያስፖራና “Halloween”
አገራችንን ለቅቀን ከወጣንበት ጊዜ ጀምሮ በባዕድ አገር በርካታ የምንማራቸው፤ የምንለምዳቸው ባህሎች አሉ፡፡ የዚያኑ ያህል መማር የሌለብን ወይም እንዳልተማርን መሆን ያለብንም አሉ፡፡ በተለይ በአሜሪካ ከበርካታዎቹ ሸግዬ ባህሎች መካከል የምስጋና ቀን “Thanksgiving Day” የሚጠቀስ ነው - ወደ ታሪኩና ዝርዝሩ ሳልገባ እንደው በደፈናው ማመስገን መልካም ነው፤ ለዚያም ቢያንስ በዓመት አንዴ ቀን መመደብ ተገቢ ነው በሚለው እሳቤ ብቻ፡፡ ከማማረርና ማጉረምረም አንዳንዴም ባርኮትን ቆጥሮ (ጥቂትም ቢሆን) ማመስገን ሸጋ ነው - ምስጋናው ደግሞ ለፈጣሪ ብቻ ሳይሆን፤ ለወላጅ፣ ለቤተሰብ፣ ለፍቅረኛ፣ ለትዳር ጓደኛ፣ ለልጆች፣ ለወገን፣ ላገር ልጅ፣ … ማብቂያ የለውም፡፡ ታዲያ “ሃሎዊንስ”? የመሰልጠናችን፣ የፈረንጁን ባሕል የመልመዳችን፣ ከኋላ ቀርነት የመላቀቃችን፣ … ምልክት ስለሆነ ይሆን … [Read more...] about ዳያስፖራና “Halloween”
“በፖለቲካ ቂም” የተመሰረተ ክስ ውድቅ ሆነ
በጋምቤላ ሁለት የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞችና ሁለት ጠበቆች “በፖለቲካ ቂም ውሳኔያችንን አናዛባም” በማለታቸው ከስራና ከሃላፊነታቸው መሰናበታቸው ታወቀ። ሁለት የክልሉ የስነ ምግባርና የጸረ ሙስና ኮሚሽን ዓቃብያነ ህግም በተመሳሳይ ውሳኔ ከሃላፊነታቸው መባረራቸው የተጠቆመ ሲሆን ውሳኔው የክልሉ ፕሬዚዳንት ወንድም የሆኑትን ዓቃቤ ህግ አላካተተም። በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ክስ የተመሰረተባቸውን ሶስት የጋምቤላ ክልል ባለሥልጣናት የፍርድ ሂደት ያስቻለው የጠቅላይ ፍርድ ቤት ተከሳሾቹን በነጻ የለቀቀው ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ ነው። አስራ አንድ አባላት ያሉት የክልሉ አስተዳደር ስድስት ለአምስት በሆነ ውሳኔ የንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ሃላፊ በነበሩት አቶ ጀምስ ዴንግ፣ ምክትላቸው ኮንግ ጋልዎክና የክልሉ የፖሊስ ኮሚሽነር በነበሩት ኦቲየንግ ኦቻን በሙስና እንዲወነጀሉ ውሳኔ አስተላልፎ … [Read more...] about “በፖለቲካ ቂም” የተመሰረተ ክስ ውድቅ ሆነ
የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ጥርስ ውስጥ ገብቷል
የኦሮሚያን ክልል በውክልና የሚያስተዳድረው ኦህዴድ አቶ መለስ ህይወታቸው ካለፈ በኋላ ውስጥ ውስጡን ሲንተከተክ የቆየው የድርጅቱ “የመስመር” ችግር ይፋ መሆኑን ተከትሎ በተፈጠረ ስጋት የኦሮሚያ ልዩ የፖሊስ ተወርዋሪ ሃይል እንደ ቀድሞው እንደማይታመን ተጠቆመ። ሲቪል ሆነው በብርጋዴር ጀኔራልነት ስውር ማዕረግ የኦሮሚያን ፖሊስ ሲመሩ የነበሩት አቶ ደምመላሽ ገብረሚካኤል የፌዴራል ፖሊስ የማዕከላዊ መረጃና የወንጀል ኢንተለጀንስ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ረዳት ኮሚሽነርነት ቢዛወሩም አሻራቸው ኦሮሚያ ፖሊስ ውስጥ እንዳለ የሚጠቁሙት የጎልጉል ምንጮች፤ ክልሉ በፌዴራል ፖሊስ ደረጃ ያዋቀረው ተወርዋሪ ሃይል እየተደረገበት ያለው ክትትል ጥርጣሬው ከፍተኛ መሆኑን ያሳያል ብለዋል። አቶ ደምመላሽ አሁን በፌዴራል ደረጃ ያላቸው ኃላፊነት ቀድሞ በኦሮሚያ ከነበራቸው ሥልጣን ጋር ተዳምሮ የተወርዋሪው ልዩ … [Read more...] about የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ጥርስ ውስጥ ገብቷል
ከሳምንቱ አጫጭር ዜናዎች
አቶ ግርማ ለጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ዘለፋ መልስ ሰጡ በተወካዮች ምክር ቤት ብቸኛው የተቃዋሚ ፓርቲ መድረክ ተወካይ አቶ ግርማ ሰይፉ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ መድረክ የምርጫ ስነምግባር ኮዱን ላለመፈረሙ ያቀረቡትን ምክንያትና ዘለፋ አጣጣሉት። አቶ ግርማ ኦክቶበር 22 ቀን 2005 ዓ ም ከሪፖርተር ከጋዜጠኛ ዮሐንስ አምበርብር ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት “ከአይ ዲ ኤ በቀጥታ ተቀዳ የተባለው የምርጫ ስነ ምግባር ኮድ ሁለት ፓኬጆች የተካተቱበት አይደለም” ብለዋል። “ኢሕአዴግ ግን ነጥሎ ያመጣው አንዱን ነው፤ ቀሪ ሁለት ፓኬጆች አሉ፤ እነሱ ይጨመሩ ነው የምንለው፡፡ ምክንያቱም በጣም ጠቃሚ ስለሆኑ ጉዳዮች ነው የሚያስረዱት፡፡ ስለ ምርጫ አስተዳደር የመሳሰሉ፤ ነገር ግን አይፈልጉም፤ ምክንያቱም ምርጫ ቦርድ ወንድማቸውን ሊነካባቸው ነው፡፡ ምርጫ ቦርድ ጠንካራ አስተዳደር … [Read more...] about ከሳምንቱ አጫጭር ዜናዎች
ለመሆኑ ኢሕአዴግ አለ እንዴ?
ጤና ይስጥልኝ ክቡራትና ክቡራን አንባቢያን፤ በዚያኛው ሰሞን ስለብዙዎቹ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ከእግዚአብሔር መንገድ መራቅና ስለሕዝበ ክርስቲያን የመንፈስና የልብ መሸፈት አንዳንድ ነጥቦችን ተናግሬ ነበር፡፡ አንድ ሦስት ያህል የነጻው ሚዲያ ድረገጾች አስተናግደውታል፡፡ እግዚአብሔር ይባርክልኝ፤ መንግሥተ ሰማይንም ያውርስልኝ፡፡ ሙከራየ ጥቂቶችን ከገቡበት አረንቋ እንዲወጡ - እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ - ለማሳሰብ እንጂ ሃይማኖተኝነትን ለመክሰስ ወይ ለመውቀስ አይደለም፡፡ ሃይማኖት የሌለው ሰው ልጓም እንደሌለው የጋማ ከብት ሊሆን የሚችልበት አጋጣሚ እንደመኖሩ በዚያው መጠን ሃይማኖት አለኝ የሚልም ሰው ከለየለት ሃይማኖት የለሹ ሰው ባላነሰ ምናልባትም በከፋ ደረጃ አጥፊ ሊሆን የሚችልበት አጋጣሚ ይስተዋላልና ያን መረዳትና ሲቻልም ማስቀረት እንዲቻለን በዚህ ረገድ የሚታዩብንን … [Read more...] about ለመሆኑ ኢሕአዴግ አለ እንዴ?
ዛሬ ነገ ሳንል መነሳት የዜግነት ግዴታችን ነው!
ለቀድሞው የወያኔ ጠቅላይ ሚኒስትር ለጊዜው ኳሷ በእሳቸው ቁጥጥር ስር እንደሆነች እና የኢትዮጵያ ህዝብን ፍላጎት ማክበር አለበለዚያም የኢትዮጵያ ህዝብ እና ታሪክ ጠላት ሆነው የመቀጠል ሁለት ምርጫ እንዳላቸው በኢትዮጵያ ምሁራን በየአቅጣጫው ቢነገራቸውም ፤ በማን አለብኝነት ኳሷን ባለማከፋፈል ችግር ፣ እኔ ብቻ በኳሷ እንደፈለኩ ከምፈልገው ወገን ጋር ልጫወትባት ፣ ስለ ኳሷ አትጠይቁኝ ፣ ወደ ኳሷም አትጠጉ በማለት ቀይ መስመር በማስመር እና እኔ ብቻ አውቃለሁ በማለት በ 80 ሚሊዮን ህዝብ ራእይ እና ተስፋ ላይ እንደቀለዱ ... (ሙሉውን ጽሑፍ እዚህ ላይ ይገኛል) … [Read more...] about ዛሬ ነገ ሳንል መነሳት የዜግነት ግዴታችን ነው!
“ላለመማር መማር… ፤ ከ’ራስ ክህደት እስከ ሀገር ማፍረስ…”
በመጀመሪያ ‘ራሳቸውን ከዱ፣ ከዚያም በጥላቻ ታውሩ፣ ከዚያም ኢትዮጵያዊነትን ኢትዮጵያን አምርረው ጠሉ፣ ከዚያም በታሪካዊ ጠላቶቻችን እየተመሩና እየታገዙ፣ የገዛ ወገናቸውን ‘ርስ-በ’ርስ እያበጣበጡና እያለያዩ፣ ኢትዮጵያን እያፈራረሱ፣ ለባዕዳንና ለታሪካዊ ጠላቶቻችን እየቸበቸቡ አሁን ካሉበት ደረጃ ደረሱ። (ሙሉው ጽሑፍ እዚህ ላይ ይገኛል) … [Read more...] about “ላለመማር መማር… ፤ ከ’ራስ ክህደት እስከ ሀገር ማፍረስ…”
“… አንድ ኮማንዶ…”
ጊዜው የጠቅላይ ሚኒስትር መለሰ ዜናዊ ሕመማቸውና ሞታቸው በፈረቃ ተቃዋሚንም ሆነ ደጋፊን ዥዋዥዌ ሲያጫውቱት የነበረ ጊዜ ሲሆን፤ በተቃዋሚ በኩል መለስ ሲሞቱ ቢሯቸው ክፍት ስለሚሆን፤ ስልጣን የሚጠብቃት እረኛ በማጣቷ፤ ከቤተመንግሥስት ወጥታ ስትበር በወጥመድ ለመያዝ ያሰፈሰፈ ይመስል ነበር ቢባል፤ ብዙ የሚያሳማ ግንዛቤ አይመስለኝም። በዚያው ሰሞንም ነበር ጥምረትና ኦነገ (የጄ/ል ከማል ገልቹም) አሊያንስ ፈጠሩ ተብሎ የተወራው፤ ነገር ግን ወሬውን አጣጥመን ሳንጨርስ፤ በነሃሴ 1ቀን 2004 ዓ.ም. የተቋቋመው ስብስብ (ሰንጠረዥ ‹‹ለ››) ውስጥ ሁለቱ የአሊያንስ አባል ድርጅቶች ተነጣጥለው ገብተው እናገኛቸዋለን፤ ከዚያ ወዲህም የአሊያንስ ጉዳይ ኮሽታው ይጠፋል። (ሙሉው ጽሑፍ እዚህ ላይ ይገኛል) … [Read more...] about “… አንድ ኮማንዶ…”
ከሲና የተረፉት የሲኦል ነዋሪዎች ጩኸት!!
“ላለፉት ሶስት ዓመታት ማንም ሳያውቀን ታስረናል። አሁን ጉዳያችን ለዓለም መድረሱን ሰማን።የተፈታን መስሎናል” የሚሉት እስራኤል ራምሌ በሚባ እስርቤት ከሶስት ዓመት በላይ ታስረው ያሉት ወገኖች ናቸው። ይህ የሆነው የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር በርዕስ ለእስራኤል ጠ/ሚኒስትር በግልባጭ ደግሞ ከጉዳዩ ጋር አግባብ ላላቸው ለተለያዩ የአገሪቱ ባለስልጣናት፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣ ሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችና የመገናኛዎች አውታሮች ያሰራጩትን ደብዳቤ ተከትሎ በእስር ላይ ያሉት ኢትዮጵያዊያን ጉዳይ በመንቀሳቀሱ ነው። በእስራኤል የኢትዮጵያን እናድን አንድነት ማኅበር ሊቀመንበር አቶ ሳሙኤል አለባቸው አድማሱ ለጎልጉል እንዳስታወቁት ከእስር ቤት በስልክ ያነጋገሯቸው ወገኖች የደብዳቤውን መልዕክት ሰምተው አስታዋሽ በማግኘታቸው ደስታቸውን ገልጸዋል። አቶ ኦባንግ ሜቶ … [Read more...] about ከሲና የተረፉት የሲኦል ነዋሪዎች ጩኸት!!