• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ጥርስ ውስጥ ገብቷል

October 29, 2012 01:35 pm by Editor 1 Comment

የኦሮሚያን ክልል በውክልና የሚያስተዳድረው ኦህዴድ አቶ መለስ ህይወታቸው ካለፈ በኋላ ውስጥ ውስጡን ሲንተከተክ የቆየው የድርጅቱ “የመስመር” ችግር ይፋ መሆኑን ተከትሎ በተፈጠረ ስጋት የኦሮሚያ ልዩ የፖሊስ ተወርዋሪ ሃይል እንደ ቀድሞው እንደማይታመን ተጠቆመ።

ሲቪል ሆነው በብርጋዴር ጀኔራልነት ስውር ማዕረግ የኦሮሚያን ፖሊስ ሲመሩ የነበሩት አቶ ደምመላሽ ገብረሚካኤል የፌዴራል ፖሊስ የማዕከላዊ መረጃና የወንጀል ኢንተለጀንስ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ረዳት ኮሚሽነርነት ቢዛወሩም አሻራቸው ኦሮሚያ ፖሊስ ውስጥ እንዳለ የሚጠቁሙት የጎልጉል ምንጮች፤ ክልሉ በፌዴራል ፖሊስ ደረጃ ያዋቀረው ተወርዋሪ ሃይል እየተደረገበት ያለው ክትትል ጥርጣሬው ከፍተኛ መሆኑን ያሳያል ብለዋል። አቶ ደምመላሽ አሁን በፌዴራል ደረጃ ያላቸው ኃላፊነት ቀድሞ በኦሮሚያ ከነበራቸው ሥልጣን ጋር ተዳምሮ የተወርዋሪው ልዩ ኃይል ጥርስ ውስጥ መግባት ዋና ተጠቃሽ መሆኑ ተገልጾዋል፡፡

የወደፊት እቅዱ ምን እንደሆነ ያላስታወቀው የፖሊስ አመራር በኦሮሚያ ለጎልጉል ዘጋቢ በሰጠው መረጃ “እንጠረጠራለን፣ ነጻነት የለንም፣ ወገናችን ላይ እርምጃ እንድንወስድ እንገደዳለን፣ ችግር ሲከሰት ‘የማያዳግም እርምጃ አልወሰዳችሁም’ በሚል እንገመገማለን” ሲል በአባላቱ መካከል ያለው መሰላቸት መስፋቱን አመልክቷል።

በተለያዩ የክልሉ እስር ቤቶች በርካታ ወገኖቻቸው በስመ ኦነግነትና በሃይማኖት ሰበብ መታሰራቸውን ያመለከተው ይሄው አመራር “ችግሩ እየሰፋ የሄደው ኦህዴድ ውስጥ የነበረው መከፋፈል ይፋ ከወጣ በኋላ ነው” ይላል። በየቀኑ የጸጥታ ሪፖርትና መረጃ ትንተና በሚል ግለሰቦችን መከታተልና ማሳደድ ላይ ያተኮረ ስራ እንደሚሰሩም አስታውቋል።

በብርጋዴር ጀኔራልነት ስውር ማዕረግ የኦሮሚያን ፖሊስ ሲመሩ የነበሩት አቶ ደምመላሽ ገብረሚካኤል አሁን የፌዴራል ፖሊስ የማዕከላዊ መረጃና የወንጀል ኢንተለጀንስ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ረዳት ኮሚሽነር ናቸው

በከፍተኛ ሥልጣን ላይ ያሉት የኦህዴድ አመራሮች ለህወሃት ስጋት እንዳልሆኑ የጠቆመው የኦሮሚያ ፖሊስ ልዩ ሃይል፣ አሁን የተከሰተው ልዩነት ከመካከለኛ ደረጃ አንስቶ እስከ ቀበሌ መዋቅርና በተዋረድ እስከ ዝቅተኛው ካድሬ ድረስ መውረዱ ችግሩን ከቀድሞው በተለየ አክብዶታል ይላል።

“ኦሮሚያን ራሱን ችሎ ለማስተዳደር ኦህዴድ ብቁ ነው” የሚሉት ክፍሎች በከፍተኛ ደረጃ ተቀባይነት ያላቸውና በማክረር ፖለቲካ ህወሃት በተደጋጋሚ እንደሚከሰው ለሌሎች ብሄረሰቦች ስጋት አለመሆናቸውን አባሉ ይናገራሉ። ጉዳዩ ቅስቀሳ እንዳይመስል በሚል ለቀረበለት ጥያቄ ሲመልስ “ከጁነዲን ሳዶ በኋላ በተዋቀረው የአባዱላ ካቢኔ ውስጥ የተካተቱት የበታችና የመካከለኛ ደረጃ አመራሮች ቀደም ሲል በአመለካከት ተፈርጀው የተገፉ ነበሩ። በኋላ ላይ አቋማቸውን በማስተካከልና ጊዜው እስኪደርስ ክልላችንን እያለማን እንቆይ በሚል አስተሳሰብ ኦህዴድን የተቀላቀሉ ናቸው” ሲል አስተያየቱን ያሰፍራል።

በከፍተኛ ደረጃ ያሉት አመራሮች በአብዛኛው በሙስና መጨመላለቃቸው ድርጅቱን ሽባ እንዳደረገው የማይሸሽገው የፖሊስ አመራር “ሁሉም ራሳቸውን ስለሚያውቁ ከዛሬ ነገ በሙስና ወንጀል እንከሰሳለን በሚል ስጋት ውስጥ መውደቃቸው ችግሩን ካላለዘበው በስተቀር ኦህዴድ ውስጥ የተፈጠረው ግለት በቀላሉ የሚቀዘቅዝ አይሆንም” ይላል። በሌላ በኩል ደግሞ ኦሮሚያ ውስጥ ከጥቅም ጋር በተያያዘ አብዛኛው የህወሃት፣ የፌዴራል ፖሊስና የደህንነት ሃይሎች መነካካታቸው ስለሙስና በማንሳት እውነተኛ ግምገማ ከተነሳ መጫረሱ አስቀድሞ ሊከሰት እንደሚችል ያስረዳል። በማያያዝም በተለያዩ መድረኮች እስከ ገጠር ድረስ ከህዝቡ ጋር ሲወያዩ የሚቀርበው አቤቱታ እየከፋ መሄዱን ጠቁሟል።

“ድሮ ‘ደም መጣጭ በሽታ’ ሲባል አርሶ አደሩ ‘ወባ’ ይል ነበር” ይላል የፖሊስ ልዩ ሃይል አመራር። አሁን ግን ይህ ተቀይሯል። “ደም የሚመጥ በሽታ” ተብለው ሲጠየቁ መልሳቸውን የሚጀምሩት ያወጡትን ደረጃ በማስቀደም ነው። “ደም መጣጭ በሽታ አንደኛ ሙስና፣ ሁለተኛ ኤች አይ ቪ – ኤድስ፣ ሶስተኛ የወባ ትንኝ” እንደሆነ ነው። በክልሉ ያለው ሙስና እንዳማረራቸው በየጊዜው እንደሚናገሩና ከመንግሥት ፍትህ እንደሚፈልጉ ሪፖርት ቢያቀርቡም ምንም ምላሽ እንደማይሰጥ አውስቷል።

የኦሮሚያ ፖሊስ ልዩ ሃይል አመራሮችና አባላት ውስጥ ቅሬታ እንዳለ ያልሸሸገው የጎልጉል ቀጥተኛ ምንጭ፤ የህወሃት ሰዎች፣ የፌዴራል ፖሊስ አመራሮች፣ ኦሮምኛ አቀላጥፈው የሚናገሩ የህወሃት ሰዎች በመካከላቸው መኖራቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ ችግሩን እንዳባባሰው አመልክቷል። “ፖሊስ ባለው መረጃ መሰረት ኦህዴድ ስንት ቦታ ተከፍሏል?” በሚል ለተጠየቀው “ይህ የደህንነቱ ስራ ነው። ግን ማንም እንደሚያወቀው የህወሃት አገልጋይ ኦህዴዶች (ህወሃት/ኦህዴዶች)፣ ኦህዴድ ራሱን መቻል አለበት የሚሉ ኦህዴዶችና ሚዛን አይተው ለመወሰን የተቀመጡ አሉ” ሲል መልስ ሰንዝሯል። የመጀመሪያው ሃሳብ አራማጆች እስከታችኛው የቀበሌ መዋቅር ድረስ ተቀባይነት አላቸው። ግን ውስጥ ውስጡን በጓደኛሞች መካከል የሚወራ እንጂ ይፋ የወጣ ነገር አይደለም።

በድብቅ የብርጋዴር ጀኔራል ሹመት በመያዝ የክልሉን ፖሊስ ከጀርባ ሆነው ሲመሩ የነበሩት አቶ ደምመላሽና የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር አቶ ወርቅነህ ገበየሁ ሁለቱም ሻሸመኔ አንድ መደብ ላይ የተገኙ ሲሆን አሁን አብረው በአንድ ተቋም የሚያገለግሉ ህወሃት/ኦህዴዶች መሆናቸው ይታወቃል።

ስማቸውን ሳይጠቅስ ድምጻቸው ለጥንቃቄ እንዲጎተት ተደርጎ በአሜሪካ ሬድዮ ኦሮሚኛ ክፍለ ጊዜ የቀረቡት የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ኦህዴድ ለሁለት መከፈሉን፣ እነሱም በህወሃት የሚመሩና ድርጅቱ ራሱን ችሎ መሄድ አለበት በሚሉ መካከል እንደሆነና ልዩነቱም ሰፊ መሆኑን ተናግረዋል።

“ከፍተኛ መባላት ተፈጥሯል” ሲሉ የተፈጠረውን አለመግባባት ስም ያወጡለት የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ጁነዲን ሳዶ ከባለቤታቸው ጋር በተያያዘ ብቻ ከፓርቲው አመራርነታቸው መወገዳቸውን ያስረዱት የኦህዴድ ሰው “የኢህዴግን ማዕከላዊ ኮሚቴ ውሳኔ በማክበር የአቶ ሃይለማርያምን ሹመት መቀበል ይገባናል” በሚሉትና “የምርጫው አካሄድና ጥቆማ ትክክል አይደለም” በሚሉት መካከል የተፈጠረው ልዩነት አልተፈታም ይላሉ።

አቶ አለማየሁ አቶምሳ

አቶ በረከትና አቶ ሃይለማርያም የመለስ የቅርብ ሰዎች እንደነበሩ የተናገሩት እኚሁ የኦህዴድ ሰው፤ አቶ መለስ ወደ ውጪ ሲወጡ ቁልፍ የሚሰጡት ለአቶ በረከት እንደሆነና የአቶ ሃይለማርያም ሹመት መነሻውም ቀደም ሲል በተፈጠረ “የቤተሰብ መሰል” ግንኙነት እንደሆነ ይፋ አድርገዋል። አቶ መለስ በሞቱ ማግስት ከኢህአዴግ ምክርቤት እና ከፓርላማው ውሳኔ በፊት አቶ ሃይለማርያም ጠ/ሚ/ር ሆነው እንደሚቀጥሉ በመናገር በወቅቱ የተጠባባቂ ጠ/ሚ/ርነት ሥልጣን ይዘው እንደሚሠሩ አቶ በረከት በወቅቱ በሰጡት ቃለምልልስ መናገራቸው የሚታወስ ነው፡፡ አቶ ሃይለማርያም ለፎርማሊቲ በፓርላማ ፊት ቀርበው ምህላ እንደሚፈጽሙ አቶ በረከት በግላቸው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ መናገራቸው ይህንኑ ቤተሰባዊ ግንኙነት የሚያጠናክር መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ የኦህዴድ ሊቀመንበር አቶ አለማየሁ አቶምሳ ስብሰባ ካልሆነ በስተቀር በሌሎች ስራ እንደማይሳተፉና ክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሳይሰይም የተቀመጠው በህወሃት ጫና የተነሳ መሆኑንን የማዕከላዊ ኮሚቴ አባሉ ለቪኦኤ ከተናገሩት ለመረዳት ተችሏል። ጋዜጠኛ ነሞ ዳንዲ ያናገራቸው ሰው በትክክል የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል መሆናቸውን መረጋገጡና ለጥንቃቄ ሲባል ድምጻቸው እንዲሻክርና እንዲጎተት መደረጉን አስታውቋል።

ኦክቶበር 18/2012 የኦሮሚያ ክልል የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አብርሃም ንጉሴ ወልደሐና በሰጡት ምላሽ በድርጅቱ ውስጥ ምንም ዓይነት ችግር እንደሌለ ተናግረዋል። የጎልጉል ድረገጽ ጋዜጣ አስቀድሞ የዘገበውንና የሰንደቅ ጋዜጣ ለንባብ ያበቃውን የኦህዴድ የመከፋፈል በሽታ አስመልክቶ ሸምጥጠው ክደዋል።

አቶ አብርሃም ንጉሴ ወልደሐና

አቶ አብርሃም ስማቸውን ሳይገልጹ የተናገሩትን አባል አስመልክቶ በግልጽ መናገር እንደሚችሉና፣ በድርጅቱ ውስጥ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ የቆየ ባህል አንዳለ ተናግረዋል። በድርጅት ውስጥ መነጋገር፣ መከራከርና በሃሳብ ያለመግባባት እንደሚኖር ያወሱት አቶ አብርሃም በቀጥታ ከመመለስ ይልቅ የድርጅታቸውንና የክልላቸውን እቅድ በማብራራት የተሰጣቸውን ጊዜ ወስደውታል።

ጎልጉል የኦህዴድን የመስመር መሳት ግምገማና “ይቅርታ የሌለው የመደብ ትግል ግምገማ” አስመልክቶ ሰፊ ዘገባ አስነብቦ ነበር። በወቅቱ የመደብ ትግል በአንድ ድርጅት ውስጥ ከተጀመረ መጫረስ ተጀመረ ማለት እንደሆነ መዘገባችንም አይዘነጋም።

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: abraham negussie, alemayehu atomssa, bereket, demelash gebremichael, Full Width Top, hailemariam, meles, Middle Column, oromiyaa, police

Reader Interactions

Comments

  1. Anoolewako says

    October 29, 2012 09:00 pm at 9:00 pm

    Ammas yoom iyyu tanaan bilisummaa!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule