• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አስደሳቹ የብሔራዊ ቡድን ውጤትና ቅሌት

October 31, 2012 08:30 am by Editor 2 Comments

ባሳለፍናቸው ሳምንታት  እሁድ ዕለት አንበሳው የብሔራዊ ቡድናችን ያደረገው ለአፍሪካ ዋንጫ የማለፍ ትንቅንቅ በጣም አጓጊና አስደሳች እንደነበር አይተነዋል።  ጀግናው ብሔራዊ ቡድናችን የሱዳን አቻውን  ሁለት- ለዐልቦ  በሆነ ውጤት በዝረራ አሸንፎ እነሆ ከሰላሳ አንድ አመታት በኋላ ለአፍሪካ ዋንጫ እንድናልፍና  ልክ  አረንጓዴ ጎርፍ ተብለው የሚጠሩት አትሌቶቻችን ሰንደቅ ዓላማችንን ከፍ አድርገን እንድናውለበልብ እንዳደረጉን ሁሉ ዛሬም ብሔራዊ ቡድናችን አፍሪካ ላይ ለጊዜውም ቢሆን መሀሉ ላይ የሰይጣን አምልኮት ምልክት ያለበትን ባለኮከቡን አረንጓዴ ፥ ቢጫና ፥ ቀዩን ሠንደቅ ዓላማችንን እንድናውለበልብ አድርገውልናል፡፡ ምስጋና ይግባቸው ለዋልያዎቹ።

ይህን ድል አቶ መለስ በህይወት ኖረው ቢያዩት ደስ ይለኝ ነበር። የሚሉትን ለመስማት፡፡ ግን አፈር ይክበዳቸውና የሉም። ሀገራችን ኢትዮጵያን እግዚአብሔር አምላክ በቸርነቱ እንደሚጠብቃት ብዙ ምልክቶችን አሳይቶናል። ለዚህም ለአብነት ያህል፦ አዲስ አመት መግቢያ ግድም ዘረኛውንና አምባ ገነኑን፤ እንዲሁም ለኢትዮጵያ ህዝብ ምንም አይነት ደንታ የሌለውን፥ ህዝቡን በዘር የከፋፈለውን ፥ አረመኔ መሪ መለስ ዜናዊንና ቋሚ የሲኖዶስን ህግ ጥሶ በአጉራዘለልነት  በራሱ ፈቃድ የሾማቸውን ጭፍራውን አባ ጳውሎስን ጨምሮ ከምድረ ገዕ እንዲጠፉ አድርጓቸዋል። ሎሚ ተራ ፥ ተራ ነውና ሌሎቹንም ተራ በተራ  እንደሚጠርጋቸው አልጠራጠርም፡፡ በቅርብ የምናየው ይሆናል ።

ለሃያ አንድ ዓመታት ግራ – ሸቅብ ብለው በሃገሪቷ ላይ የጨበጠትን መዳፋቸውን አዲሱ አመት አስፈልቅቆ ጠላቶቿን ስለቀነሰላት  አዚማቸው ከሽፎ ፣ ብሄራዊ ቡድናችን ብቻ ሳይሆን ፥ የወጣት ቡድኑም ሆነ ፥ የሴቶቹ ሉሲ የእግር ኳስ ቡድን ጭምር ኢትዮጵያን ወክለው በአፍሪቃ ውድድሮች ውስጥ ዘንድሮ እንዲካተቱ አምላክ ፈቅዷል ፡፡

በቅድሚያ ግን ለስፖርት ቤተሰቦችና ለመላው የኢትዮጵያ ስፖርት አፍቃሪ ህዝብ  በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ እላለሁ ። መጨረሻውንም እንዲያሳምርልን እየተመኘሁ ፣ አንድ ቅር ወደተሰኘሁበት ጉዳይ ላይ ግን በቀጥታ ላምራ ፡፡ ድሉን ያስጨበጡን ዋልያዎቻችንና  የወቅቱ የብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝን ጨምሮ፣  ለጋዜጠኞች የሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ግን እጅግ አስተዛዛቢ ነበር ፡፡ እማን ላይ ቆመሽ ማንን ታሚያለሽ ሆኖባቸው እንደሆነም ልቦናዬ ጠንቅቆ ያውቃል ፡፡  ልማታዊ እስፖርተኝነትና የካድሬ ሥራ ሆኖባቸው ተጫዋቾቻን ፣ አቶ መለስ በህይወት ዘመናቸው የኢትዮጵያ የግር ኳስ ቡድን ላይ የተዛበቱትን በመርሳት መታሰቢያነቱ ለአቶ መለስ ይሁንልን ማለታቸው ግን አንጀቴን  ነው ያቃጠለው ።

መሬት ይቅለላቸውና ክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ እንኳንም በዚህ ዘመን  ያልኖሩ ፡፡ በህይወት ቢኖሩ ኖሮ ኳስ ተጨዋች አይብቀልብሽ ብለው አገሪቷን ይረግሟት ነበር ፡፡  አቶ መለስ በአንድ ወቅት ስለ ብሔራዊ ቡድናችን ተጠይቀው የመለሱትን መልስ ላስታውሳችሁ ፡፡ በዚያን ወቅት  አቶ መለስ የጦር ኃይላችንን ወደ ሶማሌ ለማዝመት ደፋ ቀና የሚሉበት ወቅት ነበር ፡፡ አንድ ጋዜጠኛ ፦ ወደ ሶማሌ ተልኮ የሄደውን የኢትዮጵያ ወታደር እንደከዚህ በፊቱ አሜሪካዊ ወታደር  ሬሳውን በመኪና ሲጎትቱት  የኢትዮጵያ ህዝብ ቢያይ ምን የሚልዎት ይመስሎታል ? ብሎ ለጠየቃቸው ጥያቄ  የመለሱት መልስ ፦ ለጦርነት የሚሄደው እኮ ጀግናው የኢሕአዴግ ሠራዊት እንጂ የኢትዮጲያ ብሔራዊ ቡድን አይደለም በማለት አሳዝነውናል።

በሌላ ወቅት ደግሞ ብሔራዊ ቡድናችን ከሀገር ውጪ ሊጫወት ሄዶ በሙሉ ተጫዋቾቹ ሳይመለሱ ቀሩ ተብለው ሲጠየቁ ፦ መንገዱን ጨርቅ ያርግላቸው ይህ እኔን አያሳስበኝም ፡፡ እኔን የሚያሳስበኝ አንድ ገበሬ ቢጠፋ ነው ብለው መልሰዋል።  እንደውም ስታዲየሙን ቢለቁልን ማዳበሪያ ፋብሪካ እንከፍትበታለን በማለትም ጭምር በብሄራዊው ቡድን ላይ ተዛብተውበታል ፡፡  ታዲያ እንግዲህ ጎበዝ ለዚሁ በብሔራዊ ቡድናችን ላይ በሞራሉ የተረማመደበትንና በቡድኑ አናት ላይ ቀለበት መንገድ የሰራበትን መሪ ነው መታሰቢያነቱ ለሱ ይሁን ብለውአሰልጣኝና ተጨዋቾች ያስደመሙን።

ማን ያውቃል ! ከእጅ አይሻል ዶማ እንዲሉ አቶ ሀይለማሪያምና ጭፍሮቻቸውም አስገድደዋቸው ይሆናል ስፖርተኞቻችን ልማታዊ ስፖርተኞች የሆኑብን ፡፡ እንደኔ እንደኔ ግን መታሰቢያነቱ ለአቶ ይድነቃቸው ተሰማና ቤተሰቦቻቸው እንዲሁም ለመላው የኢትዮጵያ እግር ኳስ አፍቃሪ በሙሉ ቢሆን በጣም ደስ ይለኝ ነበር ግና አልሆነም ። እንግዲህ ገዢው የኢሕአዴግ ፓርቲ ሲገረሰስና ሙሉ ለሙሉ ከስልጣን ሲወገድ የብሔራዊ ቡድናችን ዝናና ክብረ ሞገስ ልክ እንደ ሶስተኛው የአፍሪቃ ዋንጫ ጀግንነታችን መመለሱ አይቀርም ፡፡ ጅምሩንም በዚህ አዲስ አመት አይተናልና ፡፡ ለአለም ዋንጫም አገራችን እንደምትደርስ አንጠራጠርም ፡፡  ያኔ ታዲያ ማስታወሻነቱ ለማን ይሆን ? ቸር እንሰንብት ።

ውድቀት ለወያኔና ጭፍሮቹ እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ !!
ዳዊት አበበ / ኦስሎ ኖርዌይ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Comments

  1. elias bekele says

    November 1, 2012 01:50 am at 1:50 am

    bertu

    Reply
  2. እስከመቼ says

    November 1, 2012 11:40 pm at 11:40 pm

    ወንድሜ ዳዊት አበበ ከኖርዌይ፤
    ጥሩ ብለሃል።
    የእግር ኳስ ቡድናችን ባደረገው ጉዞ የተሰማን ደስታና ያሳየነው ፍንደቃ፤ የአንድነት ምንነታችን መግለጫ ነው። አንድነታችን የተደበቀ፣ የማይታይ፣ የተሰረዘ፣ ወይንም የጠፋ አይደለም። አንድነታችን በውስጣችን ያለ ሀቅ ነው። ብቅ የሚለው ሲፈተን ነው። የእግር ኳስ ቡድናችን ለረጂም ዘመን ርቆት ከነበረው የአፍሪካ ዋንጫ ድግስ መግባቱ፤ ሁላችንንም ቀሰቅሰን። አንድነን ብለን ዓይናችንን አፈጠጥን። ጠላት መጣ ሲባል፤ ያለ የሌለውን መሳሪያ አንግቦ፤ ካገኘው ኢትዮጵያዊ ጋር ባንድነት ተሠልፎ፤ ሀገሩን ለመከላከል እንደሚነሳው ሁሉ፤ አንድነን ብለን ተነሳን። በአንድነታችን ኮራን። ፈነደቅን። ዘርዓይ ድረስን፣ አቡነ ጴጥሮስን፣ በላይ ዘለቀን፣ ባልቻ አባ ነፍሶን፣ ገብርዬን፣ ሽብሬ ደሳለኝን፣ እቴጌ ጣይቱን፣ ዘርዓያቆብን፣ አበበ በቂላን፣ ፋጡማ ሮባን፣ አቢቹን፣ የኛ ብለን ባቀፍነው እጆቻችን፤ የአባይን ወንዝ፣ የአዋሽን ወንዝ፣ የራስ ደጀንን ተራራ፣ የአክሱምን ሀውልት፣ የላሊበላን ገዳም፣ ሶደሬን፣ ኦሞን፣ የኛ እንዳልነው ሁሉ፤ ኮራንባቸው፤ የኛ ብለን አቀፍናቸው። ምንም እንኳ ማስታወሻነቱን ያሉት ባለሥልጣናት ለፈለጉት ቢሠጡትም፤ ማስታወሻነቱ እስከዛሬ በእግር ኳስ ታሪካችን አስተዋፅዖዋቸው ከፍ ላሉት ለይድነቃቸው ተሰማ፣ ለነመንግሥቱ ወርቁ መሆኑን ነጋሪ አንፈልግም። የተለጠፈው ማስታወሻ ይቀረፋል።
    ወደፊት የበለጠ እንጠብቃለን
    የወደፊታችን ያማረ ነው
    ወያኔን አያካትትምና
    እስከመቼ

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule