• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከሲና የተረፉት የሲኦል ነዋሪዎች ጩኸት!!

October 26, 2012 12:29 pm by Editor 6 Comments

“ላለፉት ሶስት ዓመታት ማንም ሳያውቀን ታስረናል። አሁን ጉዳያችን ለዓለም መድረሱን ሰማን።የተፈታን መስሎናል” የሚሉት እስራኤል ራምሌ በሚባ እስርቤት ከሶስት ዓመት በላይ ታስረው ያሉት ወገኖች ናቸው። ይህ የሆነው የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር በርዕስ ለእስራኤል ጠ/ሚኒስትር በግልባጭ ደግሞ ከጉዳዩ ጋር አግባብ ላላቸው ለተለያዩ የአገሪቱ ባለስልጣናት፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣ ሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችና የመገናኛዎች አውታሮች ያሰራጩትን ደብዳቤ ተከትሎ በእስር ላይ ያሉት ኢትዮጵያዊያን ጉዳይ በመንቀሳቀሱ ነው።

በእስራኤል የኢትዮጵያን እናድን አንድነት ማኅበር ሊቀመንበር አቶ ሳሙኤል አለባቸው አድማሱ ለጎልጉል እንዳስታወቁት ከእስር ቤት በስልክ ያነጋገሯቸው ወገኖች የደብዳቤውን መልዕክት ሰምተው አስታዋሽ በማግኘታቸው ደስታቸውን ገልጸዋል። አቶ ኦባንግ ሜቶ በበኩላቸው “ማድረግ የሚገባንን ማከናወን ጀምረናል የሚሆነውን እናያለን” በማለት በቅርቡ ከእስራኤል መንግስት ባለስልጣናት ጋር ለመነጋገር ወደ ስፍራው እንደሚያመሩና እስር ላይ የሚገኙትን ወገኖቻቸውን እንደሚጎበኙ አስታውቀዋል።

ኦክቶበር 16 ቀን 2012ዓም በኢትዮጵያ ወቅታዊ የመወያያ (ECADF) የፓልቶክ መድረክ አንድ እንግዳ ቀርቦ ነበር። ጠያቂዋ ሙያዬ ምስክር መናገርና መጠየቅ ተስኗት አምላኳን እየተማጸነች ድምጿ ጠፋ። በሱዳን በኩል በስደት ካገራቸው የሚወጡ ኢትዮጵያዊያን በሲና በረሃ የደረሰባቸውን አሰቃቂ ግፍ የሚናገረው ወጣት ፍቅሩ፣ በረሃ ላይ ስለሚደርስባቸው ዘግናኝ ግፍ ሶስት ዓመት ከሶስት ወር ከታሰረበት እስር ቤት ውስጥ የኑዛዜ ያህል የወገኖቹን ስቃይ አስተጋባ።

ራምሌ እስር ቤት

በረሃ ውስጥ የሚያገኟቸው አረቦች ገንዘብ ሲያጡ ኩላሊታቸውን ይወስዳሉ። አንዳንዴም አራትና ሶስት በመሆን “የኔን ውሰደው እነሱን ተዋቸው” በማለት ራስን ለእርድ የሚያቀርቡ ወገኖች አሉ። ኩላሊትና ልብ ለመልቀም ከጎረቤት አካባቢ እንደሚመጡ የተቆሙት የህክምና ባለሙያዎች የአካል ክፍላቸውን አውልቀው የወሰዱባቸው ወገኖቻችንን አካላቸው ተወስዶ ሲያበቃ አምጥተው ይዘረግፏቸዋል። ከአስራ አራት እስከ አስራ ስድስት ዓመት የሚሆናቸውን ታዳጊ እህቶቻችንን ክብራቸውን በመከራ ውስጥ ተገስሰዋል። ከዚህ ሁሉ መከራና ሞት ተርፈው ከለላ ፍለጋ እስራኤል የገቡት ወገኖች የገጠማቸው ህይወት እጅግ አሳዛኝ ነው።

አቶ ሳሙኤል እንደሚሉት የኢትዮጵያውያኑ መታሰር እንዲታወቅ አይፈለግም ነበር። ተገደው ማመልከቻ በመጻፍ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ከተደረጉት ውጪ በእናታቸው እቅፍ ላይ ያሉትን ጨምሮ ከሶስት መቶ በላይ ወገኖች በጠረፍ ድንኳን ውስጥ ከታሰሩ አራትና ሶስት ዓመታትን አስቆጥረዋል።

አቶ ኦባንግ ከሁሉም በፊት የሚያነሱት ነጥብ “ለኢትዮጵያዊያን አዲስ ኢትዮጵያ ትሰራለች።አሁን ስደት ላይ ያሉት ወገኖች የጠየቁት ጊዜያዊ ከለላ ነው። በ1997 የጄኔቫ ኮንቬንሽን መሰረት ጉዳያቸው ሊጣራ ይገባል” የሚል የህግ ጥያቄ ነው። አቶ ሳሙኤልም አቶ ኦባንግ የሚሉትን ይጋራሉ።

በእስር የሚማቅቁት ወገኖች ድምጽ ይፋ መሆኑን ተከትሎ አቶ ኦባንግ የጻፉት ግልጽ ደብዳቤ ግልባጭ የተደረገላቸው ታዋቂ የሚዲያ አካላት ስፍራው ድረስ ይደርሳሉ፣ እስረኞቹን አነጋግረውና ጎብኝተው የደረሰባቸውን በደል ለዓለም ያጋልጣሉ የሚል ፍርሃት መፈጠሩን፣ ለዚህም አንዳንድ ምልክቶች መታየታቸውን አቶ ሳሙኤል አለባቸው ይናገራሉ። ለጉዳዩ ቅድሚያ የሰጡትን ሚዲያዎችና ተቋማት በማመስገን ጥሪ የሚያስተላልፉት አቶ ሳሙኤል “በኢትዮጵያ ጉዳይ የሚሰሩ ታዋቂ ግለሰቦች፣ ድርጅቶች፣ ተቋማት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች፣ አገርና ወገን ወዳዶች…” ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ያሰራጨውን ግልጽ ደብዳቤ በመደገፍ ጫናውን እንዲያበረቱ ጥሪ አቅርበዋል። አቶ ኦባንግ በጋራ ንቅናቄው በኩል አቤቱታ (ፒቴሽን) እንዲያስፈርሙም ተጠይቀዋል። በግል መልዕክት የላኩላቸው ክፍሎች እንዳሉም ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያዊ ስደተኞች በኬንያ፣ በጃፓን፣ ደቡብ አፍሪካ፣ እስራኤል፣ ኖርዌይ፣ ስዊድን፣ … በመሳሰሉት አገሮች ለሚደርስባቸው በደል “አገራችሁ እንደ ሶማሊያና ኤርትራ አይደለችም እያሉ የተባበሩት መንግስታትን መመሪያ ይጠቅሳሉ” የሚሉት አቶ ኦባንግ ድርጅታቸው (አኢጋን) ወደ ጃፓን፣ ሜክሲኮ፣ ኖርዌይ፣ ማልታ፣ ስዊድን፣ ደቡብ አፍሪካ፣ … የተጓዘውና መልዕክተኛ የላከው ይህንን የተዛባ አመለካከት ለመቀየር እንደሆነ አመልክተዋል።

በሌሎች የዓለም ክፍሎች እንዳደረጉት ሁሉ በቅርቡ የጋራ ንቅናቄው በአካባቢው ከሚገኙ ቅርንጫፍ (ቻፕተር) አመራሮች ጋር በመነጋገር ወደ እስራኤል በመጓዝ ከሚመለከታቸው የእስራኤል ባለስልጣናት ጋር እንደሚነጋገሩ ያስታወቁት አቶ ኦባንግ “የትም ይሁን የትም፣ የየትኛውም ብሄር አባል ቢሆን፣ ህጻናትም ሆኑ አዋቂዎች ኢትዮጵያዊያን ሁላችንም አንድ አካል ነን። ከታሰሩ ሁላችንም ታስረናል፣ ከተገረፉ ሁላችም ያመናል፣ ከተራቡ ሁላችንም ይርበናል፣ ሲጠሙ ሁላችንም ይጠማናል። የአንድ ወገናችን ስቃይ የሁላችንም ስቃይ በመሆኑ አቅማችን በፈቀደ ሁሉ የሚቻለንን ለማድረግ ዝግጁ ነን” ብለዋል። ይህ አስተሳሰብ “ሁላችንም ነጻ ካልወጣን ማንም ነጻ አይወጣም” ከሚለው የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ መሰረታዊ መርህ የሚነሳ መሆኑንም አመልክተዋል።

በተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች ወገኖቻችን እየተሰቃዩ መሆኑን ያመለከቱት አቶ ኦባንግ በቅርቡ ታላላቅ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማት፤ ሂውማን ራይትስንም ጨምሮ ወደ እስራኤል፣ ሲና በረሃና ኬንያ እንደሚጓዙ አመልክተዋል፡፡ አቶ ኦባንግ ከተቋማቱ ጋር ድርጅታቸው በተለይ ስለሚሰራው ሥራ አላብራሩም።

የተጀመረውን ዘመቻ ተከትሎ “ትምህርት እናስተምራቸዋለን” በሚል ህጻናትን ወደ ሌላ ስፍራ ማዘዋወር መጀመሩን፣ የእስራኤል ባለስልጣናት የጉብኝት ቀጠሮ መያዛቸውን፣ ያመለከቱት አቶ ሳሙኤል፣ አቡነ መርቆሪዎስ ስደተኞቹን ባሉበት ቦታ በመገኘት ለመጎብኘት ጊዜ መያዛቸውን ተናግረዋል። በልዩ ሁኔታ ጉብኝታቸውን ለማዘጋጅት ሙከራ እያደረጉ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
“በፍርድ ቤት የተፈረደበት እስረኛ ፍርዱን ሲጨርስ እንደሚለቀቅ ስለሚያውቅ ቀኑን ይጠብቃል። የእኛ አይታወቅም። እኛ ያለነው መደበኛ እስር ቤት አይደለም። ዓለም በቃኝ ነው…” ፍቅሩ ከሙያዬ ምስክር ጋር ባደረገው አሳዛኝ ቃለ መጠይቅ ወቅት የተናገረው ቃል ነው። ከሲና በረሃ ስቃይ በኋላ ሌላ ሲኦል!! ኦባንግ ሜቶ “ለሁላችንም መፍትሄ የምትሰጥ አገር አለችን። እሷም አዲሲቷ ኢትዮጵያ ናት። መሰረቷም ቅድሚያ ለሰብዓዊነት ይሆናል። አዲሲቷ ኢትዮጵያ እስክትሰራ ባለንበት ልንከበርና ችግራችንን ተገንዝበው ሊያስተናግዱን ይገባል” ይላሉ።

በተመሳሳይ ዜና አቶ ኦባንግ በኖርዌይ ስለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖች ለመነጋገር ወደ ኦስሎ ያመራሉ። በኖርዌይ የሚገኙ ስደተኞች ወደ አገራቸው እንዲመለሱ በየጊዜው የሚደረግባቸው ጫና እንዲቆም በየአቅጣጫው ጥረት ሲደረግ መቆየቱ በተለያዩ መገናኛዎች መገለጹ አይዘነጋም።

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Ethiopia, Full Width Top, israel, Middle Column, Obang, refugees, SMNE

Reader Interactions

Comments

  1. Tariku says

    October 27, 2012 01:08 am at 1:08 am

    i just want to say thank you for this article!
    b/c i am one of them!

    Reply
  2. Jibrel says

    October 27, 2012 07:31 am at 7:31 am

    Meche new yeethiopiawi enba emikomew?nafekegn hizebu nuro almola bilot akalu eyegodele beyebereha yikeratetal yeweyane balesiltan lijoch chaina..europa..america talalak timehiret bet wist yimaralu minew habesha?edih fezezin lemin 1honen aninesam?bianes nege lijochachin emaysededubat ethiopian enifter …..

    Reply
  3. dawit says

    October 27, 2012 10:04 am at 10:04 am

    አቶ ኦባንግ ምስጋና ይሁንልዎ! በዚህ አሳዛኝ ጽሁፍ ውስጥ የተጠቀሱት ወገኖች ይህ ሁሉ መከራ ሲደርስባቸው፣ለአራትና ከዚያም በላይ ዓመታት ባስከፊ ሁኔታ መታሰራቸው አለመሰማቱ ልብ ያደማል። አንደኛው ተናጋሪ እንደተናገሩት ሁሉም በሚችለው መጠን፣ መድረስ በሚችልበት ቦታና ማድረግ የሚችለውን በማድረግ ለወገኖቹ ይጩህ፣እንጩህ፣ አንድ ነገር ተደርጎ ባስቸኳይ የሚጎበኙበት ሁኔታ የሚመቻችበትን ሁኔታ ማፈላለግ ይቻል ዘንድ ሚዲያዎች ይበልጥ ትኩረት ሊሰጡት ይገባል። አቶ ኦባንግ ሜቶ ብቻቸውን ላደረጉትና እያደረጉ ላሉት ትግል በድጋሚ አክብሮቴን ለመግለጽ እወዳለሁ።

    Reply
  4. solo says

    October 28, 2012 12:09 am at 12:09 am

    አቶ ኦባንግ በርታ ሁላችንም ድምጻችንን እናስማለን !

    Reply
  5. Hager says

    October 28, 2012 04:46 pm at 4:46 pm

    It is heart touching news. Thank you Mr. Obang

    Reply
  6. yeshitela zenebe says

    October 31, 2012 12:47 pm at 12:47 pm

    Dear Ato Obang Metho, we thank you very much for all the efforts you are putting for the respect and freedom of all Ethiopians inside and outside Ethiopia. You have shown a decisive leadreship for the respect of human rights. Ethiopians respect your patriotic actions to defend our god given rights. As you always spoke about “no one is free untill all are free” and “Humanity befor ethnicity” are clearly defines that we all need to unit and fight for. We stand beside you for the respect of our basic human rights. God Bless you Ato Obang.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule