ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ መንግሥት ባደረገላቸው ጥሪ መሠረት ነገ ጠዋት 1:30 አዲስ አበባ ~ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ይደርሳሉ። ተወልደው ባደጉበት አዲስ አበባ ፈረንሳይ ሌጋሲዮን ሠፈር ለብርቱካን ደማቅ አቀባበል ለማድረግ ዝግጅቶች ተጠናቀዋል። ሪፖርተር በዘገበው መሠረት ብርቱካን “በመንግሥት ጥሪ ወደ አገር ቤት ጠቅልለው ከተመለሱ ምናልባትም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር፣ ወይም የፌዴራል የመጀመርያ ወይም የከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ተደርገው ሊሾሙ እንደሚችሉ ከወዲሁ ትንበያዎች እየተሰሙ ነው” ብሏል። ወ/ሪት ብርቱካን ወደ አዲስ አበባ ከመብረራቸው በፊት ለአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ በሰጡት አስተያየት “አገሪቱ ባለችበት ሁኔታ ለመርዳት ማንም ሰው የሚችለውን ነገር ለማድረግ ወደ ኋላ የሚልበት ጊዜ አለመሆኑን በመረዳት እኔም በበኩሌ … [Read more...] about ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ለሹመት ወደ ኢትዮጵያ ይመለሳሉ
birtukan
ከሳምንቱ አጫጭር ዜናዎች
አቶ ግርማ ለጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ዘለፋ መልስ ሰጡ በተወካዮች ምክር ቤት ብቸኛው የተቃዋሚ ፓርቲ መድረክ ተወካይ አቶ ግርማ ሰይፉ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ መድረክ የምርጫ ስነምግባር ኮዱን ላለመፈረሙ ያቀረቡትን ምክንያትና ዘለፋ አጣጣሉት። አቶ ግርማ ኦክቶበር 22 ቀን 2005 ዓ ም ከሪፖርተር ከጋዜጠኛ ዮሐንስ አምበርብር ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት “ከአይ ዲ ኤ በቀጥታ ተቀዳ የተባለው የምርጫ ስነ ምግባር ኮድ ሁለት ፓኬጆች የተካተቱበት አይደለም” ብለዋል። “ኢሕአዴግ ግን ነጥሎ ያመጣው አንዱን ነው፤ ቀሪ ሁለት ፓኬጆች አሉ፤ እነሱ ይጨመሩ ነው የምንለው፡፡ ምክንያቱም በጣም ጠቃሚ ስለሆኑ ጉዳዮች ነው የሚያስረዱት፡፡ ስለ ምርጫ አስተዳደር የመሳሰሉ፤ ነገር ግን አይፈልጉም፤ ምክንያቱም ምርጫ ቦርድ ወንድማቸውን ሊነካባቸው ነው፡፡ ምርጫ ቦርድ ጠንካራ አስተዳደር … [Read more...] about ከሳምንቱ አጫጭር ዜናዎች