• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ለሹመት ወደ ኢትዮጵያ ይመለሳሉ

November 7, 2018 12:29 pm by Editor 1 Comment

ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ መንግሥት ባደረገላቸው ጥሪ መሠረት ነገ ጠዋት 1:30 አዲስ አበባ ~ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ይደርሳሉ። ተወልደው ባደጉበት አዲስ አበባ ፈረንሳይ ሌጋሲዮን ሠፈር ለብርቱካን ደማቅ አቀባበል ለማድረግ ዝግጅቶች ተጠናቀዋል።

ሪፖርተር በዘገበው መሠረት ብርቱካን “በመንግሥት ጥሪ ወደ አገር ቤት ጠቅልለው ከተመለሱ ምናልባትም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር፣ ወይም የፌዴራል የመጀመርያ ወይም የከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ተደርገው ሊሾሙ እንደሚችሉ ከወዲሁ ትንበያዎች እየተሰሙ ነው” ብሏል።

ወ/ሪት ብርቱካን ወደ አዲስ አበባ ከመብረራቸው በፊት ለአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ በሰጡት አስተያየት “አገሪቱ ባለችበት ሁኔታ ለመርዳት ማንም ሰው የሚችለውን ነገር ለማድረግ ወደ ኋላ የሚልበት ጊዜ አለመሆኑን በመረዳት እኔም በበኩሌ ባለኝ አቅም፣ በሞያዬ፣ በልምድና በዕውቀቴ የምችለውን ለማዋጣት እና ያም ምን እንደሚሆን ለመወያየት ነው የምሄደው። በጣም ጥሩ ቀን ነው ለእኔ” ብለዋል።

ቪኦኤ ያነጋገራቸው የፌዴራሉ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ብርሃኑ ፀጋዬ “ወደ አገራቸው ተመልሰው በሕግም ሆነ በሌሎች ጉዳዮች ለአገሪቱም ለሕዝቡም ባላቸው ዕውቀትና ልምድ አስተዋጾ ማበርከት ፈልገው መምጣታቸው የሚያስመሰግናቸው ነው። … በአገሪቱ በሚካሄደው እንቅስቃሴ እንዲያግዙ እንፈልጋለን። አብረናቸው ለመስራትም ዝግጁ ነን” ብለዋል። እኛም አብረናቸው ለመስራት ዝግጁ ነን።”

ጎልጉል ያነጋገራቸው የዐቃቤ ሕግ መ/ቤት ባለሙያ ደግሞ ብርቱካን ለቪኦኤ ከሰጡት መግለጫ እና ከሌሎች ባለን መረጃ መሠረት የምርጫ ቦርድን ወይም የሰብዓዊ መብቶችን ኮሚሽንን ይመሩ ይሆናል የሚል ከፍተኛ ግምት አለ። የጠቅላይ ፍርቤት ፕሬዚዳንቷ ሴት በመሆናቸው በከፍተኛው ፍርድ ቤትም በከፍተኛ ኃላፊነት ሌላ ሴት ለመሾም የሚያስችል ክፍተት ቢኖርም ወ/ሪት ብርቱካን ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በሕግ ካለመሥራታቸው ጋር ተያይዞ ከሕግ ሥራ ለ13 ዓመታት ተለይተው በመቆየታቸው በፍርድ ቤት አካባቢ የመሾማቸውን ዕድል ያጠበዋል ይላሉ።

ሪፖርተር እንደ ዘገበው፤ “ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ1988 ዓ.ም. በሕግ ትምህርት የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ያገኙት ወ/ሪት ብርቱካን፣ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኛ በመሆንም ከ1989 ዓ.ም. እስከ 1990ዎቹ አጋማሽ ድረስ ከመሥራታቸውም በተጨማሪ፣ ለእስር እስከተዳረጉበት ጥቅምት ወር 1998 ዓ.ም. ድረስ ጠበቃና የሕግ አማካሪ ሆነው ሠርተዋል። … ወ/ሪት ብርቱካን ከእስር እንደተፈቱ ወደ አሜሪካ ሄደው ላለፉት ሰባት ዓመታት ቆይተዋል። በቆይታቸውም በታዋቂው ሀርቫርድ ዩኒቨርሲቲ በሕዝብ አስተዳደር ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ማግኘታቸው ታውቋል”።

(ፎቶዎቹ ከማኅበራዊ ሚዲያ የተገኙ ናቸው)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: birtukan, Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. gi Haile says

    November 8, 2018 03:10 am at 3:10 am

    መልካም ዜና ለወ/ሮ ብርቱካን እንኳንም ደስ ኣሎት። አገራችን ጠንካራ መሪዎች የምትፈልግበት ጊዜ ነው። በጠማማ ትውልድ ውስጥ መልካም ሥነምግባርና መልካም መሪዎች አስተማሪዎች የሚያስፈልጉበት ጊዜ ነው። የዘረፋና በለቤት ኣልባ የነበረችውን ኢትዮጵያ በንፁህ ታታሪና ታማኝ ልጆችዋ ተመልሳ በመልካም መሠረት ላይ ትታነፃለች። ሌቦችና ወንበዴዎች የአገራችን ጣላት ሆነው ሲዘርፉና ሲያዘርፉ ቆይተው ተመልሰው ወደ ጫካ ተመልሰዋል ። ዛሬ የአገር አድን ጥሪ መመለስ የሚችሉት የመከራውን ገፈት የቀመሱት ለፍትህ ሲሉ ዋጋ የከፈሉት ዛሬ ሊካሱና የተገደሉለት ፍትህ በእግሩ እንዲሄድና ለምድራችን ተሰፋ እነዲሆን ታላቅ ምኞታችን ነው። የሰላም ፣ የፍትህ፣ የዲሞክራሲና የእኩልነት ድምፅ አሁንም ፍትህ ሙሉ በሙሉ እስኪሰፍን ድረስ ትግሉን በአገርና በውጭ ይቀጥላል ። ፍትህ ለመላው የኢትዮጵያና ለሰው ልጆች በሙሉ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule