• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ለሹመት ወደ ኢትዮጵያ ይመለሳሉ

November 7, 2018 12:29 pm by Editor 1 Comment

ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ መንግሥት ባደረገላቸው ጥሪ መሠረት ነገ ጠዋት 1:30 አዲስ አበባ ~ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ይደርሳሉ። ተወልደው ባደጉበት አዲስ አበባ ፈረንሳይ ሌጋሲዮን ሠፈር ለብርቱካን ደማቅ አቀባበል ለማድረግ ዝግጅቶች ተጠናቀዋል።

ሪፖርተር በዘገበው መሠረት ብርቱካን “በመንግሥት ጥሪ ወደ አገር ቤት ጠቅልለው ከተመለሱ ምናልባትም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር፣ ወይም የፌዴራል የመጀመርያ ወይም የከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ተደርገው ሊሾሙ እንደሚችሉ ከወዲሁ ትንበያዎች እየተሰሙ ነው” ብሏል።

ወ/ሪት ብርቱካን ወደ አዲስ አበባ ከመብረራቸው በፊት ለአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ በሰጡት አስተያየት “አገሪቱ ባለችበት ሁኔታ ለመርዳት ማንም ሰው የሚችለውን ነገር ለማድረግ ወደ ኋላ የሚልበት ጊዜ አለመሆኑን በመረዳት እኔም በበኩሌ ባለኝ አቅም፣ በሞያዬ፣ በልምድና በዕውቀቴ የምችለውን ለማዋጣት እና ያም ምን እንደሚሆን ለመወያየት ነው የምሄደው። በጣም ጥሩ ቀን ነው ለእኔ” ብለዋል።

ቪኦኤ ያነጋገራቸው የፌዴራሉ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ብርሃኑ ፀጋዬ “ወደ አገራቸው ተመልሰው በሕግም ሆነ በሌሎች ጉዳዮች ለአገሪቱም ለሕዝቡም ባላቸው ዕውቀትና ልምድ አስተዋጾ ማበርከት ፈልገው መምጣታቸው የሚያስመሰግናቸው ነው። … በአገሪቱ በሚካሄደው እንቅስቃሴ እንዲያግዙ እንፈልጋለን። አብረናቸው ለመስራትም ዝግጁ ነን” ብለዋል። እኛም አብረናቸው ለመስራት ዝግጁ ነን።”

ጎልጉል ያነጋገራቸው የዐቃቤ ሕግ መ/ቤት ባለሙያ ደግሞ ብርቱካን ለቪኦኤ ከሰጡት መግለጫ እና ከሌሎች ባለን መረጃ መሠረት የምርጫ ቦርድን ወይም የሰብዓዊ መብቶችን ኮሚሽንን ይመሩ ይሆናል የሚል ከፍተኛ ግምት አለ። የጠቅላይ ፍርቤት ፕሬዚዳንቷ ሴት በመሆናቸው በከፍተኛው ፍርድ ቤትም በከፍተኛ ኃላፊነት ሌላ ሴት ለመሾም የሚያስችል ክፍተት ቢኖርም ወ/ሪት ብርቱካን ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በሕግ ካለመሥራታቸው ጋር ተያይዞ ከሕግ ሥራ ለ13 ዓመታት ተለይተው በመቆየታቸው በፍርድ ቤት አካባቢ የመሾማቸውን ዕድል ያጠበዋል ይላሉ።

ሪፖርተር እንደ ዘገበው፤ “ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ1988 ዓ.ም. በሕግ ትምህርት የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ያገኙት ወ/ሪት ብርቱካን፣ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኛ በመሆንም ከ1989 ዓ.ም. እስከ 1990ዎቹ አጋማሽ ድረስ ከመሥራታቸውም በተጨማሪ፣ ለእስር እስከተዳረጉበት ጥቅምት ወር 1998 ዓ.ም. ድረስ ጠበቃና የሕግ አማካሪ ሆነው ሠርተዋል። … ወ/ሪት ብርቱካን ከእስር እንደተፈቱ ወደ አሜሪካ ሄደው ላለፉት ሰባት ዓመታት ቆይተዋል። በቆይታቸውም በታዋቂው ሀርቫርድ ዩኒቨርሲቲ በሕዝብ አስተዳደር ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ማግኘታቸው ታውቋል”።

(ፎቶዎቹ ከማኅበራዊ ሚዲያ የተገኙ ናቸው)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: birtukan, Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. gi Haile says

    November 8, 2018 03:10 am at 3:10 am

    መልካም ዜና ለወ/ሮ ብርቱካን እንኳንም ደስ ኣሎት። አገራችን ጠንካራ መሪዎች የምትፈልግበት ጊዜ ነው። በጠማማ ትውልድ ውስጥ መልካም ሥነምግባርና መልካም መሪዎች አስተማሪዎች የሚያስፈልጉበት ጊዜ ነው። የዘረፋና በለቤት ኣልባ የነበረችውን ኢትዮጵያ በንፁህ ታታሪና ታማኝ ልጆችዋ ተመልሳ በመልካም መሠረት ላይ ትታነፃለች። ሌቦችና ወንበዴዎች የአገራችን ጣላት ሆነው ሲዘርፉና ሲያዘርፉ ቆይተው ተመልሰው ወደ ጫካ ተመልሰዋል ። ዛሬ የአገር አድን ጥሪ መመለስ የሚችሉት የመከራውን ገፈት የቀመሱት ለፍትህ ሲሉ ዋጋ የከፈሉት ዛሬ ሊካሱና የተገደሉለት ፍትህ በእግሩ እንዲሄድና ለምድራችን ተሰፋ እነዲሆን ታላቅ ምኞታችን ነው። የሰላም ፣ የፍትህ፣ የዲሞክራሲና የእኩልነት ድምፅ አሁንም ፍትህ ሙሉ በሙሉ እስኪሰፍን ድረስ ትግሉን በአገርና በውጭ ይቀጥላል ። ፍትህ ለመላው የኢትዮጵያና ለሰው ልጆች በሙሉ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule