• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ለሹመት ወደ ኢትዮጵያ ይመለሳሉ

November 7, 2018 12:29 pm by Editor 1 Comment

ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ መንግሥት ባደረገላቸው ጥሪ መሠረት ነገ ጠዋት 1:30 አዲስ አበባ ~ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ይደርሳሉ። ተወልደው ባደጉበት አዲስ አበባ ፈረንሳይ ሌጋሲዮን ሠፈር ለብርቱካን ደማቅ አቀባበል ለማድረግ ዝግጅቶች ተጠናቀዋል።

ሪፖርተር በዘገበው መሠረት ብርቱካን “በመንግሥት ጥሪ ወደ አገር ቤት ጠቅልለው ከተመለሱ ምናልባትም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር፣ ወይም የፌዴራል የመጀመርያ ወይም የከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ተደርገው ሊሾሙ እንደሚችሉ ከወዲሁ ትንበያዎች እየተሰሙ ነው” ብሏል።

ወ/ሪት ብርቱካን ወደ አዲስ አበባ ከመብረራቸው በፊት ለአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ በሰጡት አስተያየት “አገሪቱ ባለችበት ሁኔታ ለመርዳት ማንም ሰው የሚችለውን ነገር ለማድረግ ወደ ኋላ የሚልበት ጊዜ አለመሆኑን በመረዳት እኔም በበኩሌ ባለኝ አቅም፣ በሞያዬ፣ በልምድና በዕውቀቴ የምችለውን ለማዋጣት እና ያም ምን እንደሚሆን ለመወያየት ነው የምሄደው። በጣም ጥሩ ቀን ነው ለእኔ” ብለዋል።

ቪኦኤ ያነጋገራቸው የፌዴራሉ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ብርሃኑ ፀጋዬ “ወደ አገራቸው ተመልሰው በሕግም ሆነ በሌሎች ጉዳዮች ለአገሪቱም ለሕዝቡም ባላቸው ዕውቀትና ልምድ አስተዋጾ ማበርከት ፈልገው መምጣታቸው የሚያስመሰግናቸው ነው። … በአገሪቱ በሚካሄደው እንቅስቃሴ እንዲያግዙ እንፈልጋለን። አብረናቸው ለመስራትም ዝግጁ ነን” ብለዋል። እኛም አብረናቸው ለመስራት ዝግጁ ነን።”

ጎልጉል ያነጋገራቸው የዐቃቤ ሕግ መ/ቤት ባለሙያ ደግሞ ብርቱካን ለቪኦኤ ከሰጡት መግለጫ እና ከሌሎች ባለን መረጃ መሠረት የምርጫ ቦርድን ወይም የሰብዓዊ መብቶችን ኮሚሽንን ይመሩ ይሆናል የሚል ከፍተኛ ግምት አለ። የጠቅላይ ፍርቤት ፕሬዚዳንቷ ሴት በመሆናቸው በከፍተኛው ፍርድ ቤትም በከፍተኛ ኃላፊነት ሌላ ሴት ለመሾም የሚያስችል ክፍተት ቢኖርም ወ/ሪት ብርቱካን ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በሕግ ካለመሥራታቸው ጋር ተያይዞ ከሕግ ሥራ ለ13 ዓመታት ተለይተው በመቆየታቸው በፍርድ ቤት አካባቢ የመሾማቸውን ዕድል ያጠበዋል ይላሉ።

ሪፖርተር እንደ ዘገበው፤ “ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ1988 ዓ.ም. በሕግ ትምህርት የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ያገኙት ወ/ሪት ብርቱካን፣ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኛ በመሆንም ከ1989 ዓ.ም. እስከ 1990ዎቹ አጋማሽ ድረስ ከመሥራታቸውም በተጨማሪ፣ ለእስር እስከተዳረጉበት ጥቅምት ወር 1998 ዓ.ም. ድረስ ጠበቃና የሕግ አማካሪ ሆነው ሠርተዋል። … ወ/ሪት ብርቱካን ከእስር እንደተፈቱ ወደ አሜሪካ ሄደው ላለፉት ሰባት ዓመታት ቆይተዋል። በቆይታቸውም በታዋቂው ሀርቫርድ ዩኒቨርሲቲ በሕዝብ አስተዳደር ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ማግኘታቸው ታውቋል”።

(ፎቶዎቹ ከማኅበራዊ ሚዲያ የተገኙ ናቸው)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: News Tagged With: birtukan, Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. gi Haile says

    November 8, 2018 03:10 am at 3:10 am

    መልካም ዜና ለወ/ሮ ብርቱካን እንኳንም ደስ ኣሎት። አገራችን ጠንካራ መሪዎች የምትፈልግበት ጊዜ ነው። በጠማማ ትውልድ ውስጥ መልካም ሥነምግባርና መልካም መሪዎች አስተማሪዎች የሚያስፈልጉበት ጊዜ ነው። የዘረፋና በለቤት ኣልባ የነበረችውን ኢትዮጵያ በንፁህ ታታሪና ታማኝ ልጆችዋ ተመልሳ በመልካም መሠረት ላይ ትታነፃለች። ሌቦችና ወንበዴዎች የአገራችን ጣላት ሆነው ሲዘርፉና ሲያዘርፉ ቆይተው ተመልሰው ወደ ጫካ ተመልሰዋል ። ዛሬ የአገር አድን ጥሪ መመለስ የሚችሉት የመከራውን ገፈት የቀመሱት ለፍትህ ሲሉ ዋጋ የከፈሉት ዛሬ ሊካሱና የተገደሉለት ፍትህ በእግሩ እንዲሄድና ለምድራችን ተሰፋ እነዲሆን ታላቅ ምኞታችን ነው። የሰላም ፣ የፍትህ፣ የዲሞክራሲና የእኩልነት ድምፅ አሁንም ፍትህ ሙሉ በሙሉ እስኪሰፍን ድረስ ትግሉን በአገርና በውጭ ይቀጥላል ። ፍትህ ለመላው የኢትዮጵያና ለሰው ልጆች በሙሉ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule