• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“በፖለቲካ ቂም” የተመሰረተ ክስ ውድቅ ሆነ

October 29, 2012 01:37 pm by Editor 1 Comment

በጋምቤላ ሁለት የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞችና ሁለት ጠበቆች “በፖለቲካ ቂም ውሳኔያችንን አናዛባም” በማለታቸው ከስራና ከሃላፊነታቸው መሰናበታቸው ታወቀ። ሁለት የክልሉ የስነ ምግባርና የጸረ ሙስና ኮሚሽን ዓቃብያነ ህግም በተመሳሳይ ውሳኔ ከሃላፊነታቸው መባረራቸው የተጠቆመ ሲሆን ውሳኔው የክልሉ ፕሬዚዳንት ወንድም የሆኑትን ዓቃቤ ህግ አላካተተም።

በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ክስ የተመሰረተባቸውን ሶስት የጋምቤላ ክልል ባለሥልጣናት የፍርድ ሂደት ያስቻለው የጠቅላይ ፍርድ ቤት ተከሳሾቹን በነጻ የለቀቀው ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ ነው። አስራ አንድ አባላት ያሉት የክልሉ አስተዳደር ስድስት ለአምስት በሆነ ውሳኔ የንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ሃላፊ በነበሩት አቶ ጀምስ ዴንግ፣ ምክትላቸው ኮንግ ጋልዎክና የክልሉ የፖሊስ ኮሚሽነር በነበሩት ኦቲየንግ ኦቻን በሙስና እንዲወነጀሉ ውሳኔ አስተላልፎ እንደነበር በማስታወስ ለጎልጉል መረጃ ያስተላለፉት ክፍሎች እንዳሉት በተጠቀሱት የቢሮ ሃላፊዎች ላይ ክስ የመሰረተው የክልሉ ጸረ ሙስና ኮሚሽን ዓቃቤ ህግ ነበር።

የክልሉ ፕሬዚዳንት ወንድም ኦቦል ኦባንግ የሚገኙበት የኮሚሽኑ አቃቤ ህግ የመሰረተውን ክስ ያስቻለው የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት “ጥፋት አላገኘሁም።የተከሰሱት የንግድ ቢሮ ሃላፊዎችና ፖሊስ ኮሚሽነር የተጨበጠ ማስረጃ አልቀረበባቸውም” በማለት በነጻ እንዲሰናበቱ ወስኗል። የጎልጉል ዘጋቢ በስልክ ያነጋገራቸው የፍርድ ቤት ምንጮች ውሳኔውን ተከትሎ የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ ኦሞት ኦባንግ ውሳኔውን በመቃወም የፍርድ ሂደቱ እንዲቀለበስ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል።

“በፖለቲካ ቂም የፍርድ ውሳኔያችንን አንቀይርም” በማለት ኦሞት ኦባንግን የተከራከሩት የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ፕሬዚዳንት አቶ ጆን ዮንግ፣ ምክትላቸው አቶ ዶል ኦኩሪ፣ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ጠበቃና የመምሪያ ኃላፊ ኒይንገው ኡጃይና ሌላው ጠበቃ ኦባንግ ኡጁሉ ከሃላፊነታቸውና ከስራቸው መባረራቸው ታውቋል፡፡ ይህ ዜና እስከተጠናከርበት ጊዜ ድረስ የተቀየረ ነገር የለም።

በተመሳሳይ በተካሳሾቹ ላይ ማስረጃ በማሰባሰብ ክስ የመሰረተው የክልሉ የጸረ ሙስና ኮሚሽን አቃብያነ ህግ ኦካች ኦሞድና ኦባንግ አብዱራዛክ “ክሱን በሚገባ አላቀነባበራችሁም” በሚል ከሃላፊነታቸው ተነስተዋል፤ ከስራቸውም ታግደዋል። በተከሳሾቹ ላይ መረጃ በማሰባሰብ ክስ ከመሰረቱት መካከል አንዱ የሆኑት የክልሉ ፕሬዚዳንት ወንድም አቃቤ ህግ ኦቦል ኦባንግ ግን በስራቸውና በሃላፊነታቸው መቀጠላቸው ታውቋል። ጎልጉል ያነጋገራቸው እንዳሉት ውሳኔው በተለያዩ ደረጃ ባሉ የክልሉን የስራ ሃላፊዎችና የአስተዳደሩን ስራ አስፈጻሚዎች መካከል መለያየት ፈጥሯል።

ከዓመታት በፊት ከአራት መቶ በላይ ለሚሆኑ አኙዋኮች መገደልና በሺዎች ለሚቆጠሩት መሰደድ በቀጥታ ተጠያቂ እንደሆኑ ከበርካታ የሰብዓዊ መብት ተቋማት ክስ የሚቀርብባቸውን የክልሉ ፕሬዚዳንት ኦሞት ኦባንግን በሙስናና በመልካም አስተዳደር በጥብቅ በመታገላቸው በፖለቲካ ቂም ሶስቱ የክልሉ ሃላፊዎች ሲታሰሩ የፋይናንስ ቢሮ ሃላፊ የነበሩት አቶ ተስፋዬ ኢሬሳ ከፍተኛ ምስጢር ያላቸውን ሰነዶች በመያዝ ከመታሰራቸው በፊት መሰወራቸውን የሚገልጹት የጎልጉል የመረጃ ምንጮች “የቢሮ ሃላፊው ይዘው የተሰወሩት መረጃ አቶ ኦሞት የፈረሙባቸው ከፍተኛ የገንዘብ ሰነዶችና ሙስና የተከናወነባቸው የኮንስትራክሽንና የተለያዩ መረጃዎች ናቸው። መረጃዎቹ አንድ ቀን ህዝብ ፍርዱን ይሰጥ ዘንድ ይፋ ይሆናሉ” ሲሉ ተናግረዋል።

የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ነጻ የለቀቃቸው ሶስቱ ተከሳሾች ለጊዜው ከእስር ቢለቀቁም ከዛሬ ነገ ተመልሰው ይታሰራሉ የሚል ስጋት እንዳለ ለማወቅ ተችሏል።

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: DOL OKURI, Full Width Top, JAMES DENG, JOHN YONG, KONG GALWAK, Middle Column, Obang, obang abdarazak, OKACH OMOD, omot, OTHIENG OCHAN, TESFAE RESO

Reader Interactions

Comments

  1. Moses Anengi Atei says

    October 29, 2012 02:18 pm at 2:18 pm

    any way to work for people, is kindly better to think back under the bed.
    do the best for the sake of people but not for your sake

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule