ኢትዮጵያ ጀግና ከመውለድ ፀሀይም በምስራቅ ከመውጣት ቦዝነው አያውቁም ሲሉ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትርና የጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በዛሬው እለት በኢፌዴሪ መከላከያ ሰላም ማስከበር ማዕከል የሁርሶ ኮንቲጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት በሶስተኛ ዙር በመሰረታዊ ውትድርና የሰለጠኑ ምልምል ወታደሮች ምረቃ ላይ ተገኝተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ምረቃ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ አገሬን አትንኳት ብለው ከመላ ኢትዮጵያ የዘመቱ ጀግኖች በግንባር አኩሪ ድል እያስመዘገቡ መሆኑን ገልፀው፤ የዛሬ ተመራቂዎችም ለአገር አንድነትና ክብር ለመዋደቅ የሰራዊቱ አባል ለመሆን መወሰናቸው የሚደነቅና የሚያኮራ ነው ብለዋል። አሸባሪው የህወሓት ቡድን የኢትዮጵያ እንቅርት … [Read more...] about “ኢትዮጵያ ጀግና ከመውለድ፤ ፀሀይም በምስራቅ ከመውጣት ቦዝነው አያውቁም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ
News
ዜና
የኢትዮጵያ የደን ሽፋን 3 በመቶ ወደ 17 በመቶ አደገ
በኢትዮጵያ ያለው የደን መጠን ሽፋን ወደ 17 በመቶ ማደጉ ተገለጸ። ይህ የተነገረው የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ሦስተኛውን ዙር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር መጠናቀቁን እሁድ ባሳወቁበት ጊዜ ነበር። የመርሀግብሩን መጠናቀቅ አስመልክቶ ባሰራጩት አጭር መልዕክት፥ የሦስተኛው ዙር የአረንጓዴ ዐሻራ በስኬት በመጠናቀቁ እንኳን ደስ ያለን" ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘንድሮው መርሀ ግብር 6.7 ቢሊየን ችግኞችን መተከላቸውን አሳውቀዋል፤ ይህም ከተቀመጠው ግብ ያለፈ መሆኑን ነው ያነሱት። ከዚህ ከ2013 የአረንጓዴ ዐሻራ መርኃ ግብር መጠናቀቅ ጋር በተያያዘ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ሉሜ ወረዳ የማጠቃለያ ስነስርዓት ዛሬ ተካሂዶ ነበር። በዚህ ስነስርአት ላይ በሶስት ዓመታት ውስጥ ከ18 ቢሊየን የሚበልጡ ችግኞች መተከላቸው ተነግሯል ፤ በአረንጓዴ … [Read more...] about የኢትዮጵያ የደን ሽፋን 3 በመቶ ወደ 17 በመቶ አደገ
መሃሪ ተከስተ ገብረኪዳን፤ ባለ 5 መታወቂያና 25 የባንክ ደብተሮች ባለቤት
የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በአዲስ አበባ አምስት የቀበሌ መታወቂያ እና 25 የተለያዩ የባንክ ደብተሮች ይዞ ሲንቀሳቀስ የነበረን ግለሰብ በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ። ግለሰቡ በያዛቸው የባንክ ደብተሮች ውስጥ 2 ሚሊየን 966 ሺህ 189 ብር እንደተገኘበት ኮሚሽኑ አስታውቋል። አቶ መሃሪ ተከስተ ገብረኪዳን የተባለው ግለሰብ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ልዩ ስሙ ናሆም አደባባይ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን ምርመራ እየተካሄደበት እንደሚገኝ የፀጥታና ህግ-ማስከበር የቀጠና 1 ሻለቃ 2 ኃይል 1 አዛዥ ኢንስፔክተር አዲሱ ተሾመ ገልፀዋል። አሁን ያለውን ወቅታዊ የፀጥታ ችግር የአሸባሪው ህወሓት ቡድን በተለያዩ ቦታዎች ጥቃት ለመፈፀም የተለያዩ ሰዎችን እየተጠቀመ መሆኑንም ተናግረዋል። ከዚህ አንጻርም የሽብር ቡድኑን ተግባር ለማስፈፀም … [Read more...] about መሃሪ ተከስተ ገብረኪዳን፤ ባለ 5 መታወቂያና 25 የባንክ ደብተሮች ባለቤት
ባንኮች ከኢኮኖሚው አበርክቶ ባለፈ በህንጻ ግንባታም የላቀ ሚና እየተጫወቱ ነው ተባለ
ባንኮች በኢኮኖሚው ላይ እያደረጉ ካሉት አስተዋጽኦ ባሻገር ዘመናዊ ህንጻ በመገንባትም የላቀ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን የብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶ/ር ይናገር ደሴ ተናገሩ። ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ በ2 ቢሊየን ብር ያስገነባውን ዘመናዊ ህንጻ ዶ/ር ይናገር ደሴ በተገኙበት ዛሬ አስመርቋል። ብሔራዊ ባንክ ለባንኮች ውጤታማነት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ የተናገሩት ገዥው ቢዘገይም የውጭ ባንኮች ወደ ሀገር ውስጥ መግባታቸው ስለማይቀር ከአሁኑ ጠንካራ መሆንና ተወዳዳሪ ለመሆን መሥራት እንደሚገባ ተናግረዋል። ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ በፋይናንሥ ዘርፉ የሚጠበቅበትን ለማበርከት የጀመረውን ፕሮጀክት በታሠበው ጊዜና ወጭ ማጠናቀቁን የባንኩ ፕሬዝዳንት አቶ ገነነ ሩጋ ተናግረዋል። የተገነባው ባለ 37 ወለል ዘመናዊ ህንጻ የንብ ባህላዊ ቀፎና የማር እንጀራን ቅርጽ እንዲኖረው … [Read more...] about ባንኮች ከኢኮኖሚው አበርክቶ ባለፈ በህንጻ ግንባታም የላቀ ሚና እየተጫወቱ ነው ተባለ
የሰሞኑ የጦር ድሎች
የወገን ጦር በወሰደው የማጥቃት ርምጃ ፍላቂትን ከአሸባሪው ትህነግ ቡድን አስለቀቀ የመከላከያ ሠራዊት፣ የአማራ ልዩ ኀይል፣ ሚሊሻና ፋኖ በአሸባሪው የህወሓት ቡድን ላይ በጥመረት በወሰዱት እርምጃ ፍላቂትን አስለቅቀዋል። የወገን ጦር የማጥቃት እርምጃውን አጠናክሮ በመቀጠል ወደፊት እየገሰገሰ መሆኑ ተገልጿል። በአሁኑ ሰዓትም በደብረዘቢጥ እና አካባቢው የቀረው የአሸባሪ ርዝራዥ ቡድን ሙሉ በመሉ ተለቅሞ የአካባቢው ነዋሪዎች መደበኛ ሥራቸውን ቀጥለዋል ሲል አሚኮ ዘግቧል። በደባርቅ አካባቢ በብና ሜዳ ሾልኮ ለመግባት የሞከረው የአሸባሪው ህወሓት ታጣቂ ቡድን ተደመሰሰ በደባርቅ አካባቢ በብና ሜዳ ሾልኮ ለመግባት የሞከረው የአሸባሪው ህወሓት ታጣቂ ቡድን በዛሬው ዕለት ተደምስሷል። ታጣቂ ቡድኑ በዝንጀሮ አፋፍ፣ ወርቅ አዝላ እና በቅሎ ማነቂያ ሾልኮ ለመግባት ተደጋጋሚ … [Read more...] about የሰሞኑ የጦር ድሎች
የአባይን ግድብ ግንባታ ለማደናቀፍ ከሱዳን ለመግባት የሞከረው የትህነግ ቅጥረኛ ኃይል ተደምስሷል
የአባይን ግድብ ግንባታ ለማደናቀፍ ከሱዳን በአልምሃል ሰርጎ ለመግባት የሞከረው የጁንታው ቅጥረኛ ኃይል መደምሰሱ የመከላከያ ሠራዊት አስታወቀ። የመተከል ዞን የተቀናጀ ግብረ ሃይል ኮማንድ ፖስት የኦፕሬሽን ዘርፍ አሰተባባሪ ኮሎኔል ሰይፈ ኢንጊ ቅጥረኛው ቡድን የተለያዩ ፀረ ሰው እና ፀረ ተሽከርካሪ ፈንጂዎችን ለማጥመድ የሞከረ ቢሆንም መቋቋም ተስኖት ተበታትኗል ሲሉ ተናግረዋል። ጠላት አሳቻ ስአት ጠብቆ አካባቢውን ለማተራመስ ቢንቀሳቀስም የጠላትን እንቅስቃሴ ከመነሻው በንቃት ሲከታተሉ የነበሩት የመከላከያ ሰራዊታችን ክፍሎች ተቀናጅተው እርምጃ ወስደውበታል ብለዋል ። የጠላት ኃይል በጀግናው ሰራዊት የበላይነት ተወስዶበት ሀምሳ የሽብር መልዕክተኞች ሲደመሰሱ ፣ከሰባ በላይ መቁሰላቸውን አስተባባሪው ገልፀዋል ።የተረፈው ኃይል ደግሞ አግሬ … [Read more...] about የአባይን ግድብ ግንባታ ለማደናቀፍ ከሱዳን ለመግባት የሞከረው የትህነግ ቅጥረኛ ኃይል ተደምስሷል
በነሐሴ ወር ብቻ 180 የሸኔ አባላት ተደምስሰዋል
በነሐሴ ወር ብቻ በተወሰደ ወታደራዊ ኦፕሬሽን 180 የሸኔ አባላት መደምሰሳቸውን በመከላከያ ሰራዊት የደቡብ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ አሰታወቀ። የዕዙ የኋላ ደጀን አሰተባባሪ ኮለኔል ግርማ አየለ እንደገለጹት፣ በተያዘው ወር ቡድኑ ይንቀሳቀስባቸው በነበሩ ምዕራብ ጉጂ፣ ምሥራቅ ጉጂ እና በቦረና ዞኖች በተካሄደ አራት ወታደራዊ ዘመቻዎች 180 አባላቱ ሲደመሰሱ 94ቱ ቆሰለዋል፣ 2ቱ ደግሞ ተማርከዋል። እርምጃው ከተወሰደባቸው የሠራዊት አባላቱ ወስጥ የህወሓት የሽብር ቡድን ያሰለፋቸው ታጣቂዎች መገኘታቸውንም ኮለኔል ግርማ አስረድተዋል። በወታደራዊ ዘመቻው የተማረከው የሼ አባል ሞርከታ ጎበና በሸኔ ጉዳይ አሰፈፃሚዎች ተመልምሎ ኬንያ ሀገር ስልጠና ወስዶ መመለሱን እና በስሩ 50 የሸኔ ሚሊሻዎችን ይመራ እንደነበር ለኢቲቪ ገልጿል። ይሁን እንጂ በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት … [Read more...] about በነሐሴ ወር ብቻ 180 የሸኔ አባላት ተደምስሰዋል
አራቱ ወንድማማች የኢትዮጵያ ዘማቾች
አራቱ የጋሽ ኑር ልጆች እኛ እያለን ሀገር አትፈርስም ብለው ብርሸለቆ ማሰልጠኛ ገብተው ወታደራዊ ስልጠና እየወሰዱ ይገኛሉ፤ ወንድማማቾቹ ቃሲም ኑር፣ ኤዳሶ ኑር፣ ታጁ ኑር እና ዘይኑ ኑር ይባላሉ። አራቱ ወንድማማቾች ጁንታው ሀገር ሊበትን ቢያስብም እኛ የኢትዮጵያ ልጆች እያለን ይህ እንዴት ይሆናል ብለው ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር በአንድነት መዝመት እንዳለባቸው ተነጋግረውና መክረው ስልጠናቸውን በሚገባ እየተከታተሉ እንደሚገኙ በሥፍራው ለሚገኙት የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘጋቢዎች ነግረዋቸዋል። አባታቸው ጋሽ ኑር 11 ወንድ ልጆች እና 6 ሴት ልጆች አሏቸው። ወደማሰልጠኛው የገቡት አራቱ ወንድማማቾች "አባታችን በሀገር ፍቅር ስሜት እና ወኔ ነው አንጾ ያሳደገን። በዚህም ምክንያት አገር ጥሪ ስታቀርብ መርቆና በአባገዳዎች አስመርቆ ሸኝቶናል" ነው ያሉት ሰልጣኞቹ … [Read more...] about አራቱ ወንድማማች የኢትዮጵያ ዘማቾች
አዲስ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል በጂጂጋ
በጅግጅጋ ዩኒቨርስቲ ሼህ ሀሰን የበሬ ሪፈራል ሆስፒታል ማዕከሉ በ27 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባው የኩላሊት እጥበት (ዳያሊሲስ) ማዕከል ዛሬ በሶማሊ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ሙስጠፋ ሙሁመድ ተመረቀ:: ከግንባታ ወጪው 40 በመቶ የሚሆነው በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት በሚኖሩ የክልሉ ተወላጆች፤ ቀሪው 60 በመቶ ደግሞ በክልሉ መንግሥት የተሸፈነ መሆኑ ታውቋል፡፡ ማዕከሉ 10 ማሽኖች እንደተገጠሙለት እና በቀን ለ20 ሕሙማን የኩላሊት እጥበት አገልግሎት እንደሚሰጥ የሶማሊ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዶ/ር ሸርማርኬ ሸሪፍ ገልፀዋል። የሶማሊ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ሙስጠፋ ሙሁመድ በበኩላቸው ማዕከሉን የማቋቋም ሃሳብ ያፈለቁ ወጣቶችን አመስግነው የክልሉ መንግስት ወደፊትም ለህዝቡ ፋይዳ ያላቸውን ሃሳቦች ለሚያፈልቁ ወጣቶች ድጋፍ እንደሚያደርግ ቃል … [Read more...] about አዲስ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል በጂጂጋ
ትህነግ ቤተ እምነቶችን እንደ ጦር ካምፕ እየተጠቀመባቸው ነው
የህወሓት የሽብር ቡድን በወረራቸው አካባቢዎች አብያተ ክርስቲያንን እና መስጅዶችን ከማውደም ባሻገር እንደ ጦር ካምፕ እየተጠቀመባቸው መሆኑን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር ተናገሩ። የአማራ ክልል የሃይማኖት ተቋማት በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የውይይት መድረክ በባህርዳር እየተካሄደ ይገኛል። በመድረኩ ንግግር ያደረጉት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ የህወሓት የሽብር ቡድን በኢትዮጵያ ግዛታዊ አንድነት ላይ የጋረጠውን የኅልውና አደጋ ለመቀልበስ ኅብረተሰቡ በኅልውና ዘመቻው እንዲሳተፍ የሃይማኖት አባቶች የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። የህወሓት የሽብር ቡድን ለመደምሰስ በሚደረገው ጥረት የሃይማኖት አባቶች የሚጠበቅባቸውን እየተወጡ መሆኑን የክልሉ መንግሥት በአድናቆት ይመለከተዋል ሲሉም ተናግረዋል። ነገር ግን ጥቂትም ቢሆኑ ሽማግሌ በመምሰል ለህወሓት … [Read more...] about ትህነግ ቤተ እምነቶችን እንደ ጦር ካምፕ እየተጠቀመባቸው ነው










