• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሰሞኑ የጦር ድሎች

September 4, 2021 02:33 pm by Editor Leave a Comment

የወገን ጦር በወሰደው የማጥቃት ርምጃ ፍላቂትን ከአሸባሪው ትህነግ ቡድን አስለቀቀ

የመከላከያ ሠራዊት፣ የአማራ ልዩ ኀይል፣ ሚሊሻና ፋኖ በአሸባሪው የህወሓት ቡድን ላይ በጥመረት በወሰዱት እርምጃ ፍላቂትን አስለቅቀዋል።

የወገን ጦር የማጥቃት እርምጃውን አጠናክሮ በመቀጠል ወደፊት እየገሰገሰ መሆኑ ተገልጿል።

በአሁኑ ሰዓትም በደብረዘቢጥ እና አካባቢው የቀረው የአሸባሪ ርዝራዥ ቡድን ሙሉ በመሉ ተለቅሞ የአካባቢው ነዋሪዎች መደበኛ ሥራቸውን ቀጥለዋል ሲል አሚኮ ዘግቧል።

በደባርቅ አካባቢ በብና ሜዳ ሾልኮ ለመግባት የሞከረው የአሸባሪው ህወሓት ታጣቂ ቡድን ተደመሰሰ

በደባርቅ አካባቢ በብና ሜዳ ሾልኮ ለመግባት የሞከረው የአሸባሪው ህወሓት ታጣቂ ቡድን በዛሬው ዕለት ተደምስሷል።

ታጣቂ ቡድኑ በዝንጀሮ አፋፍ፣ ወርቅ አዝላ እና በቅሎ ማነቂያ ሾልኮ ለመግባት ተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርግም በርካታ አባላቱ መደምሰሳቸውን አውደ ውጊያውን የመሩት የመከላከያ ሠራዊት አመራሮች ገልጸዋል።

የሽብር ቡድኑ በመከላከያ ሠራዊት፣ በአማራ ልዩ ኃይል እና ሚሊሺያ፣ በኦሮሚያ ሚሊሺያ እንዲሁም በፋኖ አከርካሪው መመታቱ ነው የተገለጸው።

አሸባሪ ቡድኑን ሙሉ ለሙሉ በመደምሰስ ከወረራቸው የሰሜን ጎንደር አካባቢዎች ጠራርጎ ለማጥፋት በመከላከያ ሠራዊቱ እና በሌሎች የፀጥታ ኃይሎች የተጠናከረ እርምጃ እየተወሰደበት መሆኑንም አመራሮቹ ተናግረዋል።

በዛሬው ውጊያ በርካቶቹ የአሸባሪ ቡድኑ አባላት ከመደምሰሳቸው ባሻገር በርካታ የጦር መሳሪያ እና የቡድኑ ታጣቂዎችም ተማርከዋል።

ሰቆጣ ከአሸባሪው የህወሓት ታጣቂዎች ነፃ ወጣች

ሰቆጣ በአማራ ልዩ ኃይል ከአሸባሪው የህወሓት ቡድን ነፃ መውጣቷን የክልሉ የሰላምና የሕዝብ ደህንነት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሰማ ጥሩነህ አስታወቁ።

በደቡብ ወሎ ዞን የወጣቶች የክተት መድረክ ላይ ንግግር ያደረጉት ኃላፊው ቀጣይ አዲስ ዓመትን የምንቀበለው የሕዝብ እና የሀገር ጠላትን በመቅበር ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ሐይቅ ከተማ ለመግባት ቋምጦ የመጣው የአሸባሪው ኃይልም ሙት እና ቁስለኛ ሆኖ ተመልሷል ብለዋል።

በሌሎች አካባቢዎችም የወገን ጦር ቁልፍ ወታደራዊ ስትራቴጂክ ቦታዎችን ስለያዘ የሸብር ቡድኑን በገባበት ሁሉ መቀበሪያው እያደረገው እንደሆነ ኃላፊው ገልጸዋል።

በቀጣይም ጠንካራ የመከላከያ ኃይል ለመገንባት ወጣቱ መከላከያን እና ልዩ ኃይልን ሊቀላቀሉ ይገባል ብለዋል ዶ/ር ሰማ ጥሩነህ።

የልዩ ኃይሉን አደረጃጀት ለማጠናከር ልዩ ትኩረት በመስጠትም የአማራ ክልል መንግሥት የማሰልጠኛ ካምፖችን በማዘጋጀት የወጣቶችን መግባት እየተጠባበቀ ነው ብለዋል።

የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት፣ የሰቆጣ ወጣቶች እና መላው የዋግ ጀግኖች ለከፈሉት መሥዋዕትነት ታላቅ የክብር ምስጋናቸውን አቀርበዋል።

በሰሜን ወሎ የገባው አሸባሪው ህወሓት በመከላከያ ሰራዊት እርምጃ ተወሰደበት

በሰሜን ወሎ በኩል ሰርጎ የገባው ወራሪው የህወሓት አሸባሪ ሃይል በጀግናው መከላከያ ሰራዊት አፀፋዊ እርምጃ ተወሰደበት።

በዚህ ስምሪት 142 የሽብር ቡድኑ ታጣቂ ሃይል ሲደመሰስ 4 ስናይፕር፣ 6 የሞርተር ቅንቡላ፣ 1 ብሬን፣ 18 የእጅ ቦምብ፣ 15 ክላሽ፣ 7 ሺህ የብሬን ጥይት፣ 5 ሺህ የክላሽ ጥይት፣ 1 የመገናኛ ሬዲዬ (1187 አይኮም)፣ 1 የዋይፋይ ሪሲቨር፣ 6 የብሬን ሻንጣና 10 የነፍስ ወከፍ ወታደራዊ የወገብ ሻንጣ ከጠላት ሃይል ተማርኳል።

ከግንባሩ አመራሮች መካከል የክ/ጦር ም/አዛዥ ለኦፕሬሽናል እንደተናገሩት፣ ጠላት አሁን ላይ በሰራዊታችን እየደረሰበት ባለው ኪሳራና ባጋጠመው ሽንፈት የተስፋ መቁረጥ እንቅስቃሴዎችን ቢያደርግም ከገባበት መግደያ ወረዳ መውጣት እንደማይቻለው ገልፀዋል።

ወራሪውን ሃይል በገባበት አስቀርተን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለህዝባችን የድል ዜና እናሰማለንም ብለዋል።

በግዳጅ ቀጣናው የብርጌድ ዋና አዛዥ በበኩላቸው  በጭፍን ሃገራዊ ጥላቻ ተነሳስቶ የማይሞከረውን መከላከያ ሰራዊት በመፃረር ህዝብን የተዳፈረው አሸባሪ የህወሓት ቡድን በፈፀመው ስህተት የእጁን እያገኘ ነው ብለዋል።

ሰራዊታችን በተሰለፈበት የወሎ ግንባር በሰርጎ ገቡ ሽብርተኛ ቡድን ላይ እየወሰደ ያለው አሁናዊ እርምጃና በጠላት በኩል የተመለከትነው መፍረክረክ የፍፃሜውን መቃረብ የሚያመላክት ነው ያሉት ደግሞ በግንባሩ የብርጌድ ም/አዛዥ ለኦፕሬሽናል ናቸው።

ምንጭ፡- መከላከያ ሰራዊት

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Left Column, News Tagged With: operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule