• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አራቱ ወንድማማች የኢትዮጵያ ዘማቾች

September 4, 2021 01:36 pm by Editor Leave a Comment

አራቱ የጋሽ ኑር ልጆች እኛ እያለን ሀገር አትፈርስም ብለው ብርሸለቆ ማሰልጠኛ ገብተው ወታደራዊ ስልጠና እየወሰዱ ይገኛሉ፤  ወንድማማቾቹ ቃሲም ኑር፣ ኤዳሶ ኑር፣ ታጁ ኑር እና ዘይኑ ኑር ይባላሉ።

አራቱ ወንድማማቾች ጁንታው ሀገር ሊበትን ቢያስብም እኛ የኢትዮጵያ ልጆች እያለን ይህ እንዴት ይሆናል ብለው ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር በአንድነት መዝመት እንዳለባቸው ተነጋግረውና መክረው ስልጠናቸውን በሚገባ እየተከታተሉ እንደሚገኙ በሥፍራው ለሚገኙት የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘጋቢዎች ነግረዋቸዋል።

አባታቸው ጋሽ ኑር 11 ወንድ ልጆች እና 6 ሴት ልጆች አሏቸው። ወደማሰልጠኛው የገቡት አራቱ ወንድማማቾች “አባታችን በሀገር ፍቅር ስሜት እና ወኔ ነው አንጾ ያሳደገን። በዚህም ምክንያት አገር ጥሪ ስታቀርብ መርቆና በአባገዳዎች አስመርቆ ሸኝቶናል” ነው ያሉት ሰልጣኞቹ የኢትዮጵያ ወታደሮች።

“ጁንታውን ሳንቀብር ደግሞ ወደቤታችን አንመለስም” ብለዋል ወንድማማቾቹ።

ወንድማማቾቹ ሀገር አፈርሳለሁ ብሎ የመጣ እራሱ ይፈርሳል እንጂ ኢትዮጵያ በልጆቿ ጸንታ ትኖራለች የሚል መልዕክትም አስተላልፈዋል።

“ወራሪውን እዚሁ ቀብረን የትግራይን ህዝብ ነጻ እናወጣለን” – የአማራ ልዩ ሀይልና ፋኖ

ለመላው ኢትዮጵያውያን ጠላት የሆነውን ወራሪ አሸባሪ ትህነግ በገባባት አካባቢዎች በመቅበር የትግራይን ወገን ጭምር ነጻ ለማውጣት እንደሚፋለሙ በደብረ ዘቢጥ ግምባር የተሰለፉ የአማራ ልዩ ሀይልና ፋኖ አስታወቁ።

የፋኖ አባል የሆነው ወጣት ታደለ አምባቸው በተለይ ለአዲስ ዘመን ባስተላለፈው መልዕክት፤ ያለበት የደብረ ዘቢጥ ግምበር ከባድ ውጊያ የተካሄደበት ቢሆንም ወኔና እልህ በተሞላበት ሀይል ጠላት ድል መደረጉን አስታውቋል።

ድሉ ገና እንደሚቀጥልና አሸባሪውን ለማጥፋት መሽጎበት እስከነበረው ቆላ ተንቤይ ድረስ ተጉዞ የትግራይን ህዝብ ነጻ ለማውጣት ፍላጎት እንዳለው ጠቁሟል።

ጠላትን ለማጥፋት የተሰለፈው ሁሉም ኢትዮጵያዊ አገራዊ ተልዕኮውን በሚገባ እየተወጣ ነው የሚለው ወጣት ታደለ፤ የአማራ ፋኖ ከሌሎች የሰራዊቱ አባላት ጋር በመሆን በታላቅ ወኔና ጀብድ ጠላትን እየተፋለመ መሆኑን አስታውቋል። ጠላትን በመቅበር የጭቆና ቀንበር የተጫነበትን የትግራይ ህዝብ ጭምር ነጻ እናወጣለን ብሏል።

የአማራ ልዩ ሀይል አባል ረዳት ሳጅን ሀብታሙ ደርሶ በበኩሉ፤ ከጠላት ሀይል ጋር በሚደረገው ፍልሚያ የመከላከያ ሰራዊቱ፣ ልዩ ሀይሉ፤ የሚሊሻ አባላትና ፋኖ ጥምረት ውጤታማ መሆኑን አመልክቷል። (ኢ ፕ ድ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: endf, ethiopian defesne force, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule