አዲሱ ህወሃት በአሮጌ አቁማዳ በትግራይ መቀሌ መሽገው የ13 አመት ልጅ እየመለመሉ ስልጠና ሲሰጡ የከረሙትና ትላንት በመከላከያ ሠራዊት ላይ ጥቃት እንዲፈፀም ያደረጉት ሁለቱ ሙሰኛና የትግራይ ህዝብ ደመኛ ጠላት ጄኔራሎች በፎቶው የሚታዩት ናቸው! ብ/ጄ ተክለብርሃን ወ/አረጋይ፤ የዶ/ር ዐቢይ አስተዳደር ወደ ስልጣን ሲመጣ “ተደምሪያለሁ” በማለት ጊዜ ገዝቶ፤ ሚስቱንና ሶስት ሴት ልጆቹን አሜሪካ ወስዶ፤ ቤት ገዝቶ፤ አመቻችቶ፤ እንዲሁም ከመጀመሪያ ሚስቱ የወለደው ዳንኤል የተባለውን ልጁ በካናዳ እንዲኖር ያደረገው ተክለብርሃን፤ ከአሜሪካ ከተመለሰ በኋላ ወደ መቀሌ ሸሸ። ሁለት ትላልቅ ህንፃዎች በመገናኛ ወደ ሃያት በሚወስደው መንገድ ያሉት (ተገትረው የቀሩ) በኦሮሚያ በርካታ መሬቶች የሸጠ፣ ለበርካታ ዘመዶቹ በሃብት ጥግ ያደረሰ ሙሰኛ ነው! ሁለተኛው ብ/ጀነራል ኃ/ሥላሴ … [Read more...] about ህጻናትን የሚማግደው የሌቦቹ ጀርባ
tplf
መንግሥት ከዜጎች የተግባር ድጋፍ ጠየቀ
ባለፉት 29ዓመታት ከተቃዋሚ ፓርቲዎችም ሆነ ከሲቪክና ሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ተሰምቶ በማያውቅ በሚያስብል ቁመና እና ክብደት፤ ወደፊት በታሪክ በሚጠቀስ መልኩ የዜጎችን የተግባር ድጋፍ የሚጠይቅ መግለጫ ከመንግሥት ተሰምቷል። የመግለጫው ሙሉ ቃል እንዲህ ይነበባል፤ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከመንግሥት የተሰጠ መግለጫ የኢትዮጵያ ህዝቦች ከሁለት ዓመታት በፊት ግንባራቸውን ለጥይት፣ ደረታቸውን ለጦር ሰጥተው አደባባይ የወጡት የይስሙላ ፌዴራሊዝም ወገባቸውን አጉብጦት፣ ተስፋቸውን አጨልሞት ነው። ጥቂቶች ዜጎችን እያፈኑና እነርሱ እየከበሩ መምጣታቸው ቁጣቸውን አገዘፈው። ኢትዮጵያዊያን አገራቸው ሆና ለማየት ከሚያልሙት እጅግ እየራቀ መምጣት የቁጣቸውን ኃይል አገዘፈው። እውነተኛ የፌዴራል ስርዓትን ለመተግበር ጉዞ ከመጀመሩ በፊት ዜጎች በጋራ የሚሳተፉበትና ተጠቃሚ የሚሆኑበት … [Read more...] about መንግሥት ከዜጎች የተግባር ድጋፍ ጠየቀ
በአሶሳ ከተማ ከአሸባሪው ህወሃት ጋር በመሆን በድብቅ ጥቃት ሊፈጽሙ የነበሩ 20 ግለሰቦች ተያዙ
ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት/ትህነግ) በማለት የሚጠራውና በኢትዮጵያ እጅግ አስከፊ የሚባልና ትውልድን ያወደመ ርዕዮት በመከተል አገር ያፈረሰው የወንበዴዎች ጥርቅም፤ እስካሁንም በዓለምአቀፍ የአሸባሪዎች የመረጃ ቋት በአሸባሪነት ተመዝግቦ የሚገኝ ድርጅት ከህወሃት ጋር ድብቅ ግንኙነት በመፍጠር በአሶሳ ከተማ ጥፋት ለመፈጸም በዝግጅት ላይ እንደሆኑ የተጠረጠሩ 20 ግለሰቦች ዛሬ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር አብዱላዚዝ መሐመድ ተናገሩ። ኮሚሽነሩ ለኢዜአ እንዳሉት፤ግለሰቦቹ በአሶሳ ከተማ ኢንቨስትመንትን ሽፋን በማድረግ ጥፋት ለመፈጸም ከህወሃት ድብቅ ትልዕኮ ተቀብለው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ናቸው። ከዚህ ቀደም በክልሉ መተከል ዞን የተፈጸመውን ጥቃት ያስታወሱት ኮሚሽነሩ ግለሰቦቹ ይህንን ጥፋት ዳግም ማስቀጠል ዋነኛ ግባቸው … [Read more...] about በአሶሳ ከተማ ከአሸባሪው ህወሃት ጋር በመሆን በድብቅ ጥቃት ሊፈጽሙ የነበሩ 20 ግለሰቦች ተያዙ
ትህነግ የኤርትራን ወታደራዊ ዩኒፎርሞች አልሜዳ በማሰፋት ሻዕቢያ ወረርህ ለማስባል ተዘጋጅቷል
የትህነግን ትንኮሳ ቀልብሶ ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ ሥራ መጀመሩን ርእሰ መሥተዳድር ተመሥገን ጥሩነህ አስታወቁ። ትህነግ በትግራይ ክልል በሚገኘው የሀገር መከላከያ ካምፕ ላይ ጥቃት ማድረሱን ተከትሎ መንግሥት የማያዳግም ርምጃ በመውሰድ ላይ መሆኑን የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ተመሥገን ጥሩነህ አስታወቁ። ይህንን ኃይል ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለመደምሰስ በሚደረገው ርምጃ ሕዝቡ ከመንግሥት ጎን ቆሞ ሊያግዝና አካባቢውን ነቅቶ ሊጠብቅ እንደሚገባም አሳስበዋል። አቶ ተመስገን ከተናገሩት የሚከተሉት ይገኙባቸዋል፤ በየጊዜው የሸረሪት ድር ስናፀዳ አንኖርም፤ ትህነግ አልመዳ በሚባለው የጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ውስጥ የኤርትራ የመከላከያ ሰራዊት አልባሳትን በማምረት የኤርትራ ሰራዊት ወረረህ ለማለት ዝግጅት ያደረገ ነው፤ በአማራ ክልል በሶሮቃና ቅርቃር አካባቢ ትህነግ … [Read more...] about ትህነግ የኤርትራን ወታደራዊ ዩኒፎርሞች አልሜዳ በማሰፋት ሻዕቢያ ወረርህ ለማስባል ተዘጋጅቷል
ከኦነግ ሸኔ ጀርባ ህወሃት መሪውን የያዘው መሆኑ ታወቀ
“ከኦነግ ሸኔ ጀርባ ህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) መኖሩን የሚያሳዩ መረጃዎች በፖሊስ ተደርሶባቸዋል” ሲሉ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ መርዳሳ ገለጹ። ጀኔራል ፖሊስ ኮሚሽነሩ በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ወረዳ የደረሰውን ጥቃት በተመለከተ ከትላንት በስቲያ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸው እንዳመለከቱት፤ “በህወሃት ስልጠና ተሰጥቷቸው በኦሮሚያ ክልል ሽብር እንዲፈጽሙ ከተላኩት መካከል የተያዙ ሰዎች እንዳሉ አረጋግጠናል” ብለዋል። ድምጸ ወያኔ ቲቪ እና ኦኤንኤን ቲቪ ህዝብን ከህዝብ የሚያጋጩ ዘገባዎች በመስራት ላይ መሆናቸውንም ገልጸዋል። የኦነግ ሸኔ ታጣቂ ሃይል ባለፉት ሁለት ዓመታት በክልሉ በተለያዩ ቦታዎች የመንግስት ሰራተኞችን፣ አመራሮችን፣ ነጋዴወችን ጨምሮ በንጹ ዜጎች ላይ ግድያ ሲፈጽም መቆየቱን አስታውሰዋል። አሁንም … [Read more...] about ከኦነግ ሸኔ ጀርባ ህወሃት መሪውን የያዘው መሆኑ ታወቀ
ህወሃት በአማራ ክልል የሰነዘረው ጥቃት ሙሉ በሙሉ ከሸፈ
በአማራ ክልል በሶሮቃና ቅርቃር አካባቢ ትህነግ ያደረገው የጦርነት ሙከራ በአማራ ልዩ ኃይል ሙሉ በሙሉ መክሸፉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ተመስገን ጥሩነህ ገለፁ። ርዕሰ መስተዳደሩ በመንግስት እየተወሰደ ያለውን እርምጃ አስመልከቶ በሰጡት መግለጫ ምሽቱን በሰሜን ዕዝ መከላከያ ካንፖችና የተለያዩ መሰረተ ልማት ያሉባቸው አካባቢዎች የትግራይ ልዩ ኃይልና ሚሊሻ የተቀናጀ ጥቃት ማድረሳቸውን ገልፀዋል። በአማራ ክልል በሶሮቃና ቅርቃር አካባቢ ትህነግ የጦርነት ሙከራ ማድረጉንና በአማራ ልዩ ኃይል ሙሉ በሙሉ መክሸፉንም ነው የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ተመስገን የገለፁት። ትህነግን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለመደምሰስ ለሚደረገው ርምጀ ህዝብ ከመንግስት ጎን ቆሞ ሊያግዝ ና አካባቢውን ሊጠብቅ እንደሚገባም አቶ ተመስገን ጥሪ … [Read more...] about ህወሃት በአማራ ክልል የሰነዘረው ጥቃት ሙሉ በሙሉ ከሸፈ
የትህነግ አዲሱ ሤራ – አማራን በውክልና እልህ ውስጥ መክተት
* የአማራ ክልል ሰላም መሆን ለትህነግ ሤራ ስኬት ዕንቅፋት መሆኑ ተገመገመ ስብሃት ነጋ የሚባለው የትህነግ (ህወሃት) ማፊያ ቡድን አውራ ገና ወደ በረሃ ከመግባቱ በፊት አዲስ አበባ ፒያሳ ከገብረ ትንሳኤ ኬክ ቤት ዝቅ ብሎ ፍሎሪዳ ቡና ቤት መጠጥ ጠግቦ ሲወጣ ሽንት ያዘው። ከዚያም ከፍሎሪዳ እንደወጣ ያለው አደባባይ ላይ ለመሽናት አብሮት ከነበረው ባልደረባው ጋር በመሆን በሞቅታ እያወጋ ተጠጋ። አደባባዩ ላይ ሲሸና እየገለፈጠ “አማራ ላይ እንሽና” ማለቱን በወቅቱ አብሮት ከነበረው ሰው በጀብድ ሲወራ መስማቱን የመረጃ ምንጫችን ይናገራል። ራሱን የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ብሎ በመሰየም አገር ሲያተራምስና ሲዘርፍ ኖሮ መንግሥት እንዲሆን ባዕዳን ኢትዮጵያ አናት ላይ አስቀምጠውት የነበረው የጥቂት ወንበዴዎች ጥርቅም ከጅምሩ የአማራን ሕዝብ በጠላትነት ፈርጆ ለማጥፋት … [Read more...] about የትህነግ አዲሱ ሤራ – አማራን በውክልና እልህ ውስጥ መክተት
ለ6 የህወሓት ተጧሪዎች በ150 ሚሊዮን ብር የተገነቡት ቤቶች በ1.2 ቢሊዮን ብር ሊሸጡ ነው
ወሳኔው የተላለፈው በዚያን ጊዜው ህወሓት እንደፈለገ በሚዘውረው ፓርላማ ነበር። ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ “የኢህአዴግ ከፍተኛ ሹሞችን ልዩ ልዩ ጥቅማጥቅም የሚያስከብር አዋጅ ጸደቀ” በሚል ርዕስ (February 13, 2017) ባተመው ዜና መረጃውን ሲዘግብ ይህንን ብለን ነበር፤ ከሁለት ዓመት በፊት በጭምጭምታ ደረጃ ወሬዉ ወደ አደባባይ የወጣዉ ባለሥልጣናት “ጡረታ” ሲወጡ የሚከበርላቸዉ ጥቅማጥቅም አሁን “ህጋዊ ዕዉቅና” አግኝቷል። ሐሙስ ዕለት በዋለዉ የኢህአዴግ “ፓርላማ” የህወሃት/ኢህአዴግ ከፍተኛ ባለሥልጣናት በልዩ ልዩ ምክንያቶች ከኃለፊነታቸዉ ሲነሱ ጥቅማጥቅማቸዉን የሚያስከብር አዋጅ ተሸሽሎ እንዲጸድቅ ተደርጓል። የተሻሻለዉ አዋጅ ከኃላፊነታቸዉ የሚነሱ የመንግስት ባለሥልጣናት እንደ የኃላፊነት ደረጃቸዉ የመቋቋሚያ አበል፣ የሥራ ስንብት ክፍያ፣መኖሪያ … [Read more...] about ለ6 የህወሓት ተጧሪዎች በ150 ሚሊዮን ብር የተገነቡት ቤቶች በ1.2 ቢሊዮን ብር ሊሸጡ ነው
የፌዴሬሽን ም/ቤት ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ ስለ ህወሃት ማብራሪያ ሰጠ
የፌዴሬሽን ምክር ቤት ህወኃትን በተመለከተ ባሳለፈው ውሳኔዎች ዙሪያ ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ ማብራሪያ ሰጥቷል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባዘጋጀው በዚህ መድረክ በአዲስ አበባ የሚገኙ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች እና የቆንስላ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል። የፌዴሬሽን ምክር ቤት የትግራይ ክልል ምርጫን በሚመለከት ባሳለፈው ውሳኔ ዙሪያ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የሕገ መንግሥት ትርጉምና የማንነት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጸሐፊ ወርቁ አዳሙ ማብራሪያ አቅርበዋል። በማብራሪያው በ2012ዓ.ም በኢትዮጵያ ሊደረግ የነበረው ሀገራዊ ምርጫ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ስጋት ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ እንዲራዘም ምክር ቤቱ በሕገ መንግሥት ትርጉም ተመሥርቶ ውሳኔ ማሳለፉ ተነስቷል፤ የትግራይ ክልልን የሚመራው ፓርቲ ህወሀት ውሳኔውን ወደ ጎን በመተው ኢ-ሕገ መንግሥታዊ በሆነ መንገድ ምርጫ በማድረግ ወደ መንግሥት … [Read more...] about የፌዴሬሽን ም/ቤት ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ ስለ ህወሃት ማብራሪያ ሰጠ
ከ2.3 ሚሊዮን ብር በላይ የሀሰተኛ ብር ኖት ሲያዘጋጁ የነበሩ ተያዙ
በቦሌ ክፍለ ከተማ 2 ሚሊዮን 3 ሺህ 407 የሀሰተኛ ብር ኖት ሲያዘጋጁ የነበሩ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል። ለአቤቱታ ወደ ፖሊስ በመጡ ሰዎች ጥቆማ ሰጪነት ነው ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ያስታወቀው። የቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የወንጀልን ትራፊክ አደጋ ምርመራ ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ያሬድ ታረቀኝ መስከረም 20 ቀን 2013 ዓ.ም ሁለት ተጠርጣሪዎች በአጠቃላይ 2 ሚሊዮን 3 ሺህ 407 ሀሰተኛ የብር ኖት፤ የአሜሪካ ዶላር እና የተለያዩ ሐገራትን ገንዘቦችን በመኖሪያ ቤታቸው ሲያዘጋጁ መያዛቸውን ገልጸዋል። ከሚጠቀሙበት የተለያዩ ቁሳቁሶች ጋርም እጅ ከፍንጅ በቁጥጥር ስር መዋላቸውንና ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ አስረድተዋል። ተጠርጣሪዎቹ የኮትዲዩቫር ተወላጆች … [Read more...] about ከ2.3 ሚሊዮን ብር በላይ የሀሰተኛ ብር ኖት ሲያዘጋጁ የነበሩ ተያዙ










