• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከኦነግ ሸኔ ጀርባ ህወሃት መሪውን የያዘው መሆኑ ታወቀ

November 4, 2020 01:21 am by Editor Leave a Comment

“ከኦነግ ሸኔ ጀርባ ህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) መኖሩን የሚያሳዩ መረጃዎች በፖሊስ ተደርሶባቸዋል” ሲሉ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ መርዳሳ ገለጹ።

ጀኔራል ፖሊስ ኮሚሽነሩ በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ወረዳ የደረሰውን ጥቃት በተመለከተ ከትላንት በስቲያ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸው እንዳመለከቱት፤ “በህወሃት ስልጠና ተሰጥቷቸው በኦሮሚያ ክልል ሽብር እንዲፈጽሙ ከተላኩት መካከል የተያዙ ሰዎች እንዳሉ አረጋግጠናል” ብለዋል።

ድምጸ ወያኔ ቲቪ እና ኦኤንኤን ቲቪ ህዝብን ከህዝብ የሚያጋጩ ዘገባዎች በመስራት ላይ መሆናቸውንም ገልጸዋል።

የኦነግ ሸኔ ታጣቂ ሃይል ባለፉት ሁለት ዓመታት በክልሉ በተለያዩ ቦታዎች የመንግስት ሰራተኞችን፣ አመራሮችን፣ ነጋዴወችን ጨምሮ በንጹ ዜጎች ላይ ግድያ ሲፈጽም መቆየቱን አስታውሰዋል።

አሁንም በምዕራብ ወለጋ ጉሊሶ ወረዳ የኦነግ ሸኔ ቡድን በህወሃት ታግዞ ጥቃት ማድረሱን ገልጸዋል።

“በዜጎች ላይ ጥቃቱን ያደረሰው አካል ኦነግ ሸኔ መሆኑ ተረጋግጧል” ያሉት ኮሚሽነር ጄኔራሉ፤ ከጥቃቱ ጀርባ ህወሃት መኖሩን የሚያሳዩ መረጃዎች በፖሊስ መገኘታቸውን ገልጸዋል።

የተፈጸመውን ጥቃት የሚያካሂዱ ሰዎች በትግራይ ክልል ውስጥ ስልጠና አግኝተው በህዝብ ላይ ጥቃት እንዲፈጽሙ በህወሃት አቅጣጫ እየተሰጣቸው እንደሆነም ተናግረዋል።

“ፖሊስ በቁጥጥር ስር ካዋላቸው የጥቃት አድራሾች ያገኘው መረጃ እንደሚያሳየው ከድርጊቱ ፈጻሚዎች ጀርባ ህወሃት አለ” ብለዋል ኮሚሽነር ጄኔራሉ።

“ህወሃት አሰልጥኖ ለሽብር ድርጊት ወደ ኦሮሚያ ክልል የላካቸው ሰዎች እንዳሉ በፖሊስ ተደርሶበታል” ያሉት ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ፤ ከድርጊቱ ጀርባ ህወሃት ስለመኖሩ የሚነገረው በተጨባጭ መረጃ ላይ ተመስርቶ እንደሆነ ተናግረዋል።

በተፈጸመው ጥቃት አንድ ትምህርት ቤትን ጨምሮ ከ50 እስከ 60 የሚደርሱ ቤቶች ተቃጥለዋል።

በጥቃቱ ጉዳት ደርሶባቸው የነበሩ ሁለት ሰዎች ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን በአጠቃላይ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 34 መድረሱን አመልክተው፤ 12 ሰዎች ደግሞ የደረሱበት አለመታወቁን ገልጸዋል።

በጥቃቱ የተነሳ የተፈናቀሉ ሰዎችን የማረጋጋትና መልሶ የማቋቋም ስራ ከህብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት እየተሰራ እንደሆነም ገልጸዋል።

የደረሰውን ጥቃት ተከትሎ መንግስት አስፈላጊውን ርምጃ እንደሚወስድ መገለጹ ይታወቃል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: olf shanee, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የኦሮሞ ልሂቃንና ፖለቲከኞች በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለውን “የዘር ማጥፋት” ወንጀል እንዲያወግዙት አብን ጠየቀ July 6, 2022 01:38 pm
  • “አማራን ኦሮሚያ ውስጥ የመግደል እና የመጨፍጨፍ እቅድ የኦነግ ሳይሆን የኦሮሚያ ብልጽግና ነው” አቶ ሃንጋሳ July 6, 2022 01:53 am
  • “በኢትዮጵያዊያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” አይማን አብድልአዚዝ ግብጻዊው ፖለቲከኛ July 5, 2022 12:57 pm
  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule