አሁን የሚፈለገው የሚያሻገሩ መሪዎችን ማግኘት ብቻ ነው። ሕዝብ በፖለቲካ መሪዎች ሃፍረትን እየተግሞጠሞጠና ደሙ ደመ ከልብ እየሆነ የሚኖርበት ዘመን እንዲያከትምለት ይፈልጋል። የአንተ ደም የእኔ ደም ነው በማለት የችግሩ ጉያ ውስጥ ሆኖ አጋርነቱን፣ አንድነቱን ሲያሰማ ሩቅ ተቀምጦ እንደ ቅጥረኛ የወገንን ሞራል ማላመጥ አግባብ አይሆንም። ውሎ አድሮ ከገዳዮቹ በላይ ያስጠይቃል። በቅጥረኛነትም ያስመድባል። ከአገራችንም ሆነ ከዓለም ዘመን የማይረሳቸው የውብ ስብእና ባለቤቶች ሕዝባቸውን አሻግረዋል። ክፉዎች የቀበሩትን የቂምና የጥላቻ ገመድ በጣጥሰው አገራቸው በልዕልና፣ ሕዝባቸው በሰላም እንዲኖር አስችለዋል። በቀናነት ጀምረው፣ በቀናነት ጨርሰዋል። በታማኝነት ሃላፊነትን ተረከበው በታማኝነት አለፈዋል። ዝርዝር ውስጥ ባንገባም በህይወት ያሉም አሉ። እንዲህ ያሉትን የሚያስቡ “እኛንስ ማን … [Read more...] about ሕዝብ ላይ የሚፈጸም የፖለቲካ ውርጃ!!
Politics
Ato Emmanuel Abraham (1913-2016)
Ato Emmanuel Abraham who had served his country in a number of important diplomatic and ministerial posts for nearly four decades and half (1931-1974) has died at a great age of 103 on Wednesday. Emmanuel was ambassador to Britain and Italy and cabinet minister and director general at the Ministry of Foreign Affairs and director general of the Ministry of Education and Fine Arts, Minister of Posts, Telegraphs and Telephones; Minister of communications and Transport; and finally, minister of … [Read more...] about Ato Emmanuel Abraham (1913-2016)
ኢንተርኔት በመዘጋቱ በትንሹ 9 ሚሊዮን ኪሣራ ደርሷል
ኢትዮጵያ በአንድ ዓመት ውስጥ ለ30 ቀናት የኢንተርኔት አገልግሎትን በማቋረጧ ወደ 9 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ማጣቷን መቀመጫውን በዩናይትድ ስቴትስ ያደረገው ብሮኪንግስ የፖሊሲ ጥናት ተቋም ባለፈው ሳምንት ይፋ ያደረገው ጥናት ጠቋሟል። የብሩኪንግስ የፖሊሲ ጥናት ተቋም ምክትል ፕሬዝዳንት ዳረል ዌስት ባቀረቡት ጥናት በቅርብ ዓመታት ተጠቃሚዎች የሚገለገሉባቸውን የተወሰኑ አፕልኬሽኖች፤ የሞባይል ኢንተርኔት አገልግሎት አሊያም መላውን የኢንተርኔት አገልግሎት መንግስታት ማቋረጥ እና መዝጋት እየተለመደ የመጣ ክስተት መሆኑን አትተዋል። ከእነዚህ አገራት መካከል አንዷ ኢትዮጵያ ነች። ከሰኔ 24 ቀን 2007 ዓ.ም. እስከ ሰኔ 23 ቀን 2008 ዓ.ም. ባሉት ጊዜያት ለ30 ቀናት በኢትዮጵያ የኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጡን ይኸው ጥናት ጠቁሟል። «መንግስታት ብሔራዊ እና የሕብረተሰብ … [Read more...] about ኢንተርኔት በመዘጋቱ በትንሹ 9 ሚሊዮን ኪሣራ ደርሷል
INTERNATIONAL ALERT REGARDING ETHIOPIA TO WESTERN POLICY MAKERS, DONORS AND STAKEHOLDERS
Open letter to the Western Governments and Donor Countries concerning the deteriorating situation of human rights and political instability in Ethiopia that is shifting from bad to worse day after day. Your Excellency, The State of Emergency declared by the ruling ethnic apartheid regime of the TPLF/EPRDF, which is an attempt to enforce draconian measures to repress the emerging vocalization of discontent by the people of Ethiopia, will undoubtedly fail, with unknown results. Some of these … [Read more...] about INTERNATIONAL ALERT REGARDING ETHIOPIA TO WESTERN POLICY MAKERS, DONORS AND STAKEHOLDERS
ላም እሳት ወለደች!
አጉል ዘመን ገጥሟት በረት ብትከሳ፤ ከብቶች በመዥገሮች አዩ ብዙ አበሳ፡፡ ጡቶቿን አቃጣይ የነበልባል ጥጃ ላም እሳት ወለደች፤ ብ’ተው በማይተዋ ዘልለው ባልጠገቡ ወይፈኖች ነደደች፡፡ የከበረው ባህል ባለጌ ረጋግጦት እንደጨው ቀለለ፤ ወፍ ዘራሾች ነግሠው ባጥለቀለቁት ደም ምድር ተበከለ፡፡ አዎ፣ ላም እሳት ወለደች! እንደዮዲት ጉዲት እቶኑ የሚፋጅ፤ ዕረፍት በማያ’ቅ ሠይፍ እንደነደርቡሾች እንደግራኝ አህመድ፤ ጭንቅላትን ገምሶ አንገትን ቆራርጦ ዜጎችን የሚያነድ፡፡ “አጥንትና ደሜ ይሄው የናንተው ነው፤ እኔ ከሌለሁኝ እናተም እንዲያው ነው፤ እርቧችሁ ጠግቤ፣ ብድንም ሞታችሁ፤ ማንም ስለሌለ ከኔ ‘ሚለያችሁ፤ እስከመጨረሻው አጅቡኝ ባካችሁ፡፡ ” እያለ እሳት ጥጃው ሕዝብን ይማጠናል፤ መስሎት የማናውቀው ቁርበት ዘርጉ ይላል፡፡ ክፋትና ተንኮል ተፈጥሮው የሆነ፤ ሕግና … [Read more...] about ላም እሳት ወለደች!
የኦሮሚያ ሰነድ – አዲሱ ቃል ኪዳን?
ጊዜ ገድቦ መናገር ይከብድ ካልሆነ በቀር በኢትዮጵያ የስርዓት ለውጥ አይቀሬ ስለመሆኑ ክርክር የለም (አንዳንድ የወያኔ አንጋሽ ምዕራባውያን ባለሙያዎች በጥቂት ወራት ይተምኑታል)። ይህ እውነት ቢሆንም አንዳንድ “የፖለቲካ መክለፍለፎች” ሊወድቅ የተቃረበውን አገዛዝ እንዲውተረተር ዕድል ሊሰጠው ይችላል የሚል ስጋት ያላቸው ወገኖች ከያቅጣጫው ብቅ እያሉ ነው። የስጋታቸው መንስኤ ደግሞ በዋናነት የግልጽነት፣ ያለመተማመን፣ የውድድርና “ጊዜን” የመጠቀም ተራ እሽቅድምድም እንደሆነ እነዚሁ ስጋት የገባቸው ክፍሎች ይናገራሉ። ከየአቅጣጫው የሚሰሙት የ“ሽግግር” ዜናዎች፣ ዳር ዳሩን በለሆሳስ ይሰማ የነበረው “የሃሜት በሽታ” ገልጠውታል። በዚሁ መነሻ ይመስላል ለኦሮሚያ የሽግግር ሰነድ እንደሚዘጋጅ ይፋ መሆኑንን ተከትሎ ሰፊና ግልጽ ያለ መልስ ከሚመለከታቸው የእነ በቀለ ገረባ ወኪሎች ህዝብ እየጠበቀ … [Read more...] about የኦሮሚያ ሰነድ – አዲሱ ቃል ኪዳን?
ህወሃት “አስከሬን ልግዛችሁ” አለ!
በሙት መንፈስ አገር እየገዛ ያለው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) በይስሙላነት ባስቀመጠው ፕሬዚዳንት አማካኝነት ፓርላማ ብሎ በሰየመው የራሱ ስብስብ በኢትዮጵያ ያለ አንዳች ልዩነት ለገደላቸው ወገኖች አስከሬን መግዣ ብር ሰይሜአለሁ ብሏል፡፡ ከዚህ በፊት በኦሮሚያ ላፈሰሰው መድቤአለሁ ያለው 2.4 ቢሊዮን ብር እስካሁን የት እንደገባ አይታወቅም፡፡ የሙት (መለስ ዜናዊን) ፎቶ ከፊት አስቀምጦ አሁንም በአስከሬን አገሪቱን እንደሚመራ በገሃድ ያሳየው ህወሃት ለመለወጥም ሆነ ስለ ለውጥ ለማሰብ ፍላጎት እንደሌለው ነው በጥቅሉ ያመላከተው፡፡ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችን በእስር እያማቀቀ ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር ውይይት፣ ፓርቲዎች እንዳንቀሳቀሱና ኅልውና እንዳኖራቸው በርካታ መዋዕለ ንዋይ እያፈሰሰ ምርጫ ኮሚሽን ማዋቀር፣ … የሚሉ የጥገናዊ ለውጦች ስሜት እንኳን የሌላቸውን ጉዳዮች … [Read more...] about ህወሃት “አስከሬን ልግዛችሁ” አለ!
በጌድዮ ዞን ፖሊስ አዛዥ በአጋዚ ተገደለ
በጌድዮ ዞን የምትገኘው ዲላ ወረዳ ፖሊስ ዋና አዛዥ በአጋዚ ተገደለ ሲሉ በስልክ ያነጋገርናቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸውልናል። ከሶስት ቀናት ቃጠሎ፣ ዘረፋ እና ውድመት በኋላ አጋዚ በትላንትናው እለት ዲላ እንደገባ ነዋሪዎቹ ተናግረዋል። አጋዚ የጦር ቀጠና ምትመስለው ዲላ ከተማ እንደገባ አቶ ከበደ የተባሉትን የዞኑን ፖሊስ አዛዥ በጥይት ደብድቦ ገድሏቸዋል። ላለፉት ሶስት ቀናት በዲላ፣ ይርጋጨፌ፣ ወናጎ እና ፍሰሀ-ገነት የተነሳው አመጽ ያነጣጠረው በጉራጌ እና አማሮች ላይ ነበር። የጌዲዮ ተወላጆች ከአካባቢው ካድሬዎች እየታዘዙ አብያተ-ክርስትያናትን እና መስጊዶችን ጨምሮ 60 የሚሆኑ መኖርያ ቤቶችን አቃጥለዋል። ህወሃት ሕዝባዊ አመጹን መቋቋም ስላልቻለ ከ10 አመታት በፊት የነበረውን ቁርሾ በመቀስቀስ የጌዲዮ ተወላጆች በአማራ እና በስልጤ ተወላጆች ላይ ዘመቻ እንዳስነሳ ነው … [Read more...] about በጌድዮ ዞን ፖሊስ አዛዥ በአጋዚ ተገደለ
ህወሃት/ኢህአዴግ ዕድሜዬ ከ6 ወር አይበልጥም አለ
ኢትዮጵያን በነጻ አውጪ ስም የሚገዛው ህወሃት ላለፉት 25ዓመታት መብት በገፍ ሲሰጥ የቆየ ይመስል ህገመንግሥታዊ መብቶችን የሚገፍ ያስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጇል። አዋጁ ለስድስት ወር ይቆያል ማለቱ የህወሃት ዕድሜ ከስድስት ወር እንደማይቆይ ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል፡፡ ከህወሃት በተሰጠው ትዕዛዝ መሠረት ኃይለማርያም ደሳለኝ ትላንት እሁድ በሃገሪቱ “ያንዣበበውን አደጋ ለመቀልበስ” በሚል ሚኒስትሮች ምክር ቤት ለስድስት ወራት የሚዘልቅ የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ማወጁን አስታውቋል። እንደ ኃይለማርያም ንግግር ህገመንግሥታዊ መብቶች የማይጣሱ መሆናቸው ቢነገርም እዚያው የኃይለማርያም ካቢኔ አባል የሆነው የጠቅላይ አቃቤ ሹመኛው ጌታቸው አምባዬ ህወሃት በቀጣይ እንደፈለገ የሚያደርጋቸውንና የሚገድባቸውን መብቶች በዝርዝር ተናግሯል። እነዚህም:- 1) ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ ማንኛውንም ሰው ይታሰራል፤ … [Read more...] about ህወሃት/ኢህአዴግ ዕድሜዬ ከ6 ወር አይበልጥም አለ
የትግራይ ተወላጆች በሙሉ ከቢሾፍቱ ተጭነው ተወሰዱ
በደብረዘይት (ቢሾፍቱ) ይኖሩ የነበሩ የትግራይ ተወላጆች ዛሬ ቅዳሜ (8 ኦገስት) ሙሉ በሙሉ ከተማዋን ለቀው መውጣታቸውን በስልክ ካነጋገርናቸው የከተማዋ ነዋሪዎች ማረጋገጥ ችለናል። የትግራይ ተወላጆቹ ከተማዋን ለቅቀው የወጡት በቢሾፍቱ የኢሬቻ በዓል የሰዎች ሕይወት መጥፋቱን ተከትሎ የአካባቢው ሕዝብ ከጫፍ እስከጫፍ ነቅሎ በወውጣት እያካሄደ ባለው ሕዝባዊ አመጽ ሊመጣ ካለው አደጋ ለማምለጥ ነው። ህወሃት በዜጎች ላይ እየፈጸመ ያለውን ግድያ በከተማዋ ያሉ ሁሉ ሲቃወም የትግራይ ተወላጆች ግን ዝም ማለታቸው ሕዝቡን በእጅጉ እንዳስቆጣው ነዋሪዎቹ ተናግረዋል። የትግራይ ተወላጆቹ ሃብት ንብረታቸውን እየጣሉ ከተማዋን ለቅቀው ወዴት እንደሄዱ የታወቀ ነገር የለም። ላለፉት አራት ቀናት በደብረዘይት እንደ አብዛኞቹ ከተሞች የንግድ እና የስራ እንቅስቃሴ ቆሟል። ሱቆች ተዘግተዋል፣ ሕዝብም … [Read more...] about የትግራይ ተወላጆች በሙሉ ከቢሾፍቱ ተጭነው ተወሰዱ