• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ቄሮ አልሸባብ” ነው – ህወሓት!

January 9, 2018 07:19 pm by Editor 3 Comments

  • “ስድስት ሚሊዮን ወጣት በጠላትነት ፈርጀህ ማንን ልታስተዳድር ነው?” ለማ መገርሳ

ህወሓት/ኢህአዴግ በኢትዮጵ የተለያዩ ክፍሎች በተለይም በምሥራቅ ሐረርጌ “ቄሮ” በመባል የሚታወቅ ሕገወጥ እንቅስቃሴ እመረምራለሁ፤ ለፍርድ አቀርባለሁ ብሎ ዝቷል። “አመራሩ ብቃት የለውም” በማለት ራሱን የገመገመው ህወሓት/ኢህአዴግ ብቃት አልባነቱን ተገንዝቦ ራሱን ከሥልጣን ማግለል ሲገባው አሁንም የማሰርና የማሰቃየት ግፉን በስፋት ለመቀጠል በዕቅድ ለመቀንቀሳቀስ ማሰቡን ነው በዚህ ዜና የገለጸው።

የኢትዮጵያ ወጣቶችን በሥራ በማሰማራት ለአገር እንዲጠቅሙ ከማድረግ ይልቅ “አደገኛ ቦዘኔ” በማለት ሲፈርጅና ሲስር የነበረው ህወሓት አሁን ደግሞ በኦሮሞ ወጣቶች “ቄሮ” ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ለመሰንዘር ጎራዴውን እየሳለ ነው። ግፉ የበዛባቸው ወጣቶች ታላቁ ሩጫ በተካሄደበት ባንድ ወቅት ላይ “አደገኛ ቦዘኔ ራሱ ወያኔ” በማለት ምላሽ መስጠታቸው ይታወሳል።

“ማዕከላዊን እዘጋለሁ፤ ለአገራዊ መግባባት ሲባል እስረኞችን እፈታለሁ” በማለት በአደባባይ የለፈፈው ህወሓት/ኢህአዴግ “ቄሮ” ላይ ዘመቻ በመክፈት በርካታ ማዕከላዊ ለመክፈት ማቀዱንና በሺዎች የሚቆጠሩ ወገኖችን ለማሰቃየት መወሰኑን ይፋ አድርጓል። ይህንኑ የህወሓትን ሃሳብ የሚደግፉ አቀንቃኞቹ “ቄሮ” ማለት “አልሸባብ” ነው፤ እንደ አልሸባብ መታየት አለባቸው እያሉ ነው። የሁለቱም ቃል ትርጉም “ወጣት” ማለት ነው።

በቄሮ ላይ የተነሳውን ዘመቻ አስመልክቶ የጀርመን ድምጽ ራዲዮ ባልደረቦች መርጋ ዮናስና አርያም ተክሌ ያጠናቀሩትን ከዚህ በታች አቅርበናል።

የፌዴራል ፖሊስ የ“ቄሮ” ምርመራ በኦሮሚያ ክልል 

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን በኦሮሚያ ክልል በምሥራቅ ሐረርጌ ዉስጥ በሚንቀሳቀሰው “ቄሮ” በመባል በሚታወቀው የወጣቶች ቡድን ላይ ምርመራ እንደጀመረ የሀገር ዉስጥ ዘገባዎች አመልክተዋል።

የአሮሚያ ክልል የፍትህ ቢሮ የኮሙኒኬሼን ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ታዬ ዳንዳኣ ኮሚሽኑ ይህን ሥራ መጀመሩን የሚያሳይ ምንም መረጃ እንዳልደረሳቸዉ ይናገራሉ።

የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘገባው በእንቅስቃሴው ዉስጥ ቄሮዎቹ ብቻ ሳይሆኑ የአካባቢ ሚሊሽያዎች፣ ፖሊሶችና የወረዳ አመራሮች እንደተሳተፉ ይጠቅሳል። ኮሚሽኑም “ቄሮ” እንዴት እንደተደራጀና አላማዉም ላይ ምርመራ እንደሚያደርግ ዘገባዉ አክሎበታል። የ“ቄሮ” እንቅስቃሴ የመከላከያና የፌዴራል ፖሊስ አባላትን ተልዕኮ አስተጓጉሏል፤ በአካባቢዉ ስጋት ፈጥሯል መባሉም እንደምክንያት ተቀምጧል።

የአምቦ ዩኒቨርስቲ መምሕርና የበየነ መረብ (ኢንተርኔት) ፀሐፊ ስዩም ተሾመ ግን ወጣቶቹ ለማህበረሰቡ ጥያቄ መልስ ለማስገኘት የሚታገሉ እንደሆኑ አስረድተዋል። የኦሮሚያ ክልል መስተዳደር የወጣቶቹን ጥያቄ ተቀብሎ ለማስተናገድ ጥናት ላይ እንደሚገኝ አቶ ስዩም ይናገራሉ። ምክንያቱም አዲሱ የክልሉ መስተዳድር ወደ ስልጣን የመጣዉ ወጣቱ ትዉልድ ወይም “ቄሮ” በፈጠረዉ ጫና አማካኝነት በመሆኑ ባይ ናቸው።

የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ለማ መገርሳ የዛሬ ሁለት ወር ገደማ በድርጅታቸዉ በኦሕዴድ ጉባዔ ላይ ባደረጉት ንግግር “እኛ የፈጠርነዉ ወጣት ትዉልድ ስራ ስላጣ ብቻ ነዉ ወይስ ሌላ ጉዳይ ስላለ ነዉ የጠላን?” በማለት ተሳታፊዎቹን ጠይቀው እንደነበር ይታወሳል። ያኔም ስለ “ቄሮ” ያላቸዉን አስተያየት እንደሚከተለው ገልጸው ነበር።  “ቄሮ ቄሮ ቀሮ፣ እሺ ቄሮ ምንድነዉ? ቄሮን ጠላት አድርጋችሁ ታያላችሁ። ቄሮ ማለት ወጣት ማለት አይደል በአፋን ኦሮሞ? ቁጥሩ በተለይ እየጨመረ ያለውን ስድስት ሚሊዮን ወጣት በጠላትነት ፈርጀህ ማንን ልታስተዳድር ነው? እኛ ሁላችንም እዚህ አንቆይም። የፓርቲዉን አላማ የሚያስቀጥሉት ወጣቶቹ ናቸዉ” ብለው ነበር።

በአሮሚያ ክልል በፍትህ ቢሮ የኮሙኒኬሼን ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ታዬ ዳንዳኣ “ቄሮ” የማሕበረሰቡ ወሳኝ አካል ስለሆነ እነዚህን ወጣቶች በማግለል ወይም እንደ ወንጀለኛ በመፈረጅ እድገትና ሰላም ማምጣት እንደማይቻል የክልሉ መንግስት እንደሚረዳው ለዶይቼ ቬሌ ተናግረዋል።

እንደ አቶ ታዬ አስተሳሰብ፣ ቄሮ የሚባል የወጣት ቅንጅት በምሥራቅ ሐረርጌ ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ በክልሉና በሀገሪቱ የሚንቀሳቀስ ቡድን ነው። የሕግ በላይነት በየትም ቦታ ሊከበር እንደሚገባ ያመለከቱት አቶ ታዬ እስካሁን ቄሮ ተደራጅቶ ወንጀል አለመፈጸሙን አረጋግጠዋል።

የድምጽ መልዕክቱ ከዚህ በታች ይገኛል።

(ምስል፡ የቄሮና የአልሸባብ ምልክቶች ከኢንተርኔት የተወሰዱ)

https://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2018/01/1A876359_2_dwdownload.mp3

ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: al shabab, eprdf, Ethiopia, Full Width Top, meles, Middle Column, oromo, qeerroo, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    January 13, 2018 02:37 am at 2:37 am

    ሃገራችን በታሪኳ አሁን እንዳለችበት ያለ ፈተና ገጥሟት አያውቅም። አንድ ሌላውን በቁንጭራ የሚያባርርበት፤ የወያኔ መንግሥት እሳት በየቦታው እየጫረ ቤቱን ንብረቱንና ደኑን የሚያጋይበት ያ ህዝብ በመከራ ውስጥ ይገኛል። ጥቂቶች ጮቤ የሚረግጡባት ይህች ውድ ሃገራችን አዕላፍ ልጆቿ የደም ዋጋ ከፍለው ያቆዮትን ሃገር ዛሬ በዘር፤ በጎሳና በቋንቋ ድንበር ሰርተን አንድ ተሳዳጅ ሌላው አሳዳጅ ለነፍሱ ሯጭ፤ ደሙ በከንቱ የሚፈስባት ሃገር ሆናለች። በመሰረቱ ወያኔ ኢትዮጵያዊነት የማይሰማው ገንጣይ ድርጀት እንደነበርና አሁንም እንደሆነ ተግባሩ ይመሰክራል። በዘፈቀደ በሚለጥፈው የሽብር ህግጋቱ ብዙሃን አፈር እንደለበሱ፤ ቀሪዎች በጨለማ ቤት ሰቆቃን እንደሚቀበሉ የእለት እለት ዘገባዎች ይጠቁማሉ።
    ሃገራችን በወያኔ ሴራ ተመሳቅላለች። ለመኖር በተለሙት የፓለቲካ ትብታብ ብዙዎች እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይበቀል በማለት ህዝባችንን በማያቋርጥ የክፋት በትራቸው እያጠቁት ይገኛሉ። አሁን እንሆ የኦሮሞ ልጆች በጥቅል በመነሳት ወያኔን በቃን በማለታቸው የደረሰባቸውንና ወደፊትም ሊደርስባቸው የሚችለውን ሰቆቃ ጠንቀቀን እናውቃለን። ጊዜው እረዘመ እንጂ አስናቀ ገ/የስ የተባለ የሙዚቃ አቀንቃኝ እንዲህ ብሎ ነበር።

    መች ጠበበን ጎጆው መች ጠበበን ቤቱ
    ኢትዮጵያ፤ እማማ
    በአንድ አብሮ ለመኖር ሰፊ ነው መሬቱ
    ኢትዮጵያ!

    እንዲያው ነገ ከጊዜ ጋር አብሮ ለሚቀየር የዘርና የጎሳ ውስልትና ከመታገል ይልቅ አብሮ መኖርን የሚያጠናክርና ዘለቄታ ላለው አላማ ራስን አሳምኖና ሌሎችንም አስከትሎ በመነሳት ለተጠቃለለና ሁሉም በሰላምና በእኩልነት ለሚኖርባት ሃገርን ለመገንባት ታጥቀን እንነሳ!! በርቱ “ቄሮዎች”!!

    Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    January 26, 2018 02:14 pm at 2:14 pm

    ማንም የሚሰማችሁ የለም!!! ቄሮ! ቄሮ! እያልክ ፊንፊኔ ውስጥ በተለይም፣መጋላ(መርካቶ) ውስጥ ብትጮህ፣ የመጋላው ኪስ ኣውላቂ እንጂ፣የምንለው የለንም!! ፊንፊኔ ያደጉ ኪስ ኣውላቂዎች ናቸው!!!

    Reply
  3. kero says

    February 23, 2018 02:40 pm at 2:40 pm

    If kero has the gut, it should attack the politicians and leaders. No armed struggle in the country was directed at civilians except during the oromo migration/warriors and Ahmed Giragne. Kero is repeating same now. Destruction after destruction………………………………

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule