• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ቄሮ አልሸባብ” ነው – ህወሓት!

January 9, 2018 07:19 pm by Editor 3 Comments

  • “ስድስት ሚሊዮን ወጣት በጠላትነት ፈርጀህ ማንን ልታስተዳድር ነው?” ለማ መገርሳ

ህወሓት/ኢህአዴግ በኢትዮጵ የተለያዩ ክፍሎች በተለይም በምሥራቅ ሐረርጌ “ቄሮ” በመባል የሚታወቅ ሕገወጥ እንቅስቃሴ እመረምራለሁ፤ ለፍርድ አቀርባለሁ ብሎ ዝቷል። “አመራሩ ብቃት የለውም” በማለት ራሱን የገመገመው ህወሓት/ኢህአዴግ ብቃት አልባነቱን ተገንዝቦ ራሱን ከሥልጣን ማግለል ሲገባው አሁንም የማሰርና የማሰቃየት ግፉን በስፋት ለመቀጠል በዕቅድ ለመቀንቀሳቀስ ማሰቡን ነው በዚህ ዜና የገለጸው።

የኢትዮጵያ ወጣቶችን በሥራ በማሰማራት ለአገር እንዲጠቅሙ ከማድረግ ይልቅ “አደገኛ ቦዘኔ” በማለት ሲፈርጅና ሲስር የነበረው ህወሓት አሁን ደግሞ በኦሮሞ ወጣቶች “ቄሮ” ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ለመሰንዘር ጎራዴውን እየሳለ ነው። ግፉ የበዛባቸው ወጣቶች ታላቁ ሩጫ በተካሄደበት ባንድ ወቅት ላይ “አደገኛ ቦዘኔ ራሱ ወያኔ” በማለት ምላሽ መስጠታቸው ይታወሳል።

“ማዕከላዊን እዘጋለሁ፤ ለአገራዊ መግባባት ሲባል እስረኞችን እፈታለሁ” በማለት በአደባባይ የለፈፈው ህወሓት/ኢህአዴግ “ቄሮ” ላይ ዘመቻ በመክፈት በርካታ ማዕከላዊ ለመክፈት ማቀዱንና በሺዎች የሚቆጠሩ ወገኖችን ለማሰቃየት መወሰኑን ይፋ አድርጓል። ይህንኑ የህወሓትን ሃሳብ የሚደግፉ አቀንቃኞቹ “ቄሮ” ማለት “አልሸባብ” ነው፤ እንደ አልሸባብ መታየት አለባቸው እያሉ ነው። የሁለቱም ቃል ትርጉም “ወጣት” ማለት ነው።

በቄሮ ላይ የተነሳውን ዘመቻ አስመልክቶ የጀርመን ድምጽ ራዲዮ ባልደረቦች መርጋ ዮናስና አርያም ተክሌ ያጠናቀሩትን ከዚህ በታች አቅርበናል።

የፌዴራል ፖሊስ የ“ቄሮ” ምርመራ በኦሮሚያ ክልል 

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን በኦሮሚያ ክልል በምሥራቅ ሐረርጌ ዉስጥ በሚንቀሳቀሰው “ቄሮ” በመባል በሚታወቀው የወጣቶች ቡድን ላይ ምርመራ እንደጀመረ የሀገር ዉስጥ ዘገባዎች አመልክተዋል።

የአሮሚያ ክልል የፍትህ ቢሮ የኮሙኒኬሼን ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ታዬ ዳንዳኣ ኮሚሽኑ ይህን ሥራ መጀመሩን የሚያሳይ ምንም መረጃ እንዳልደረሳቸዉ ይናገራሉ።

የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘገባው በእንቅስቃሴው ዉስጥ ቄሮዎቹ ብቻ ሳይሆኑ የአካባቢ ሚሊሽያዎች፣ ፖሊሶችና የወረዳ አመራሮች እንደተሳተፉ ይጠቅሳል። ኮሚሽኑም “ቄሮ” እንዴት እንደተደራጀና አላማዉም ላይ ምርመራ እንደሚያደርግ ዘገባዉ አክሎበታል። የ“ቄሮ” እንቅስቃሴ የመከላከያና የፌዴራል ፖሊስ አባላትን ተልዕኮ አስተጓጉሏል፤ በአካባቢዉ ስጋት ፈጥሯል መባሉም እንደምክንያት ተቀምጧል።

የአምቦ ዩኒቨርስቲ መምሕርና የበየነ መረብ (ኢንተርኔት) ፀሐፊ ስዩም ተሾመ ግን ወጣቶቹ ለማህበረሰቡ ጥያቄ መልስ ለማስገኘት የሚታገሉ እንደሆኑ አስረድተዋል። የኦሮሚያ ክልል መስተዳደር የወጣቶቹን ጥያቄ ተቀብሎ ለማስተናገድ ጥናት ላይ እንደሚገኝ አቶ ስዩም ይናገራሉ። ምክንያቱም አዲሱ የክልሉ መስተዳድር ወደ ስልጣን የመጣዉ ወጣቱ ትዉልድ ወይም “ቄሮ” በፈጠረዉ ጫና አማካኝነት በመሆኑ ባይ ናቸው።

የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ለማ መገርሳ የዛሬ ሁለት ወር ገደማ በድርጅታቸዉ በኦሕዴድ ጉባዔ ላይ ባደረጉት ንግግር “እኛ የፈጠርነዉ ወጣት ትዉልድ ስራ ስላጣ ብቻ ነዉ ወይስ ሌላ ጉዳይ ስላለ ነዉ የጠላን?” በማለት ተሳታፊዎቹን ጠይቀው እንደነበር ይታወሳል። ያኔም ስለ “ቄሮ” ያላቸዉን አስተያየት እንደሚከተለው ገልጸው ነበር።  “ቄሮ ቄሮ ቀሮ፣ እሺ ቄሮ ምንድነዉ? ቄሮን ጠላት አድርጋችሁ ታያላችሁ። ቄሮ ማለት ወጣት ማለት አይደል በአፋን ኦሮሞ? ቁጥሩ በተለይ እየጨመረ ያለውን ስድስት ሚሊዮን ወጣት በጠላትነት ፈርጀህ ማንን ልታስተዳድር ነው? እኛ ሁላችንም እዚህ አንቆይም። የፓርቲዉን አላማ የሚያስቀጥሉት ወጣቶቹ ናቸዉ” ብለው ነበር።

በአሮሚያ ክልል በፍትህ ቢሮ የኮሙኒኬሼን ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ታዬ ዳንዳኣ “ቄሮ” የማሕበረሰቡ ወሳኝ አካል ስለሆነ እነዚህን ወጣቶች በማግለል ወይም እንደ ወንጀለኛ በመፈረጅ እድገትና ሰላም ማምጣት እንደማይቻል የክልሉ መንግስት እንደሚረዳው ለዶይቼ ቬሌ ተናግረዋል።

እንደ አቶ ታዬ አስተሳሰብ፣ ቄሮ የሚባል የወጣት ቅንጅት በምሥራቅ ሐረርጌ ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ በክልሉና በሀገሪቱ የሚንቀሳቀስ ቡድን ነው። የሕግ በላይነት በየትም ቦታ ሊከበር እንደሚገባ ያመለከቱት አቶ ታዬ እስካሁን ቄሮ ተደራጅቶ ወንጀል አለመፈጸሙን አረጋግጠዋል።

የድምጽ መልዕክቱ ከዚህ በታች ይገኛል።

(ምስል፡ የቄሮና የአልሸባብ ምልክቶች ከኢንተርኔት የተወሰዱ)

https://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2018/01/1A876359_2_dwdownload.mp3

ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: al shabab, eprdf, Ethiopia, Full Width Top, meles, Middle Column, oromo, qeerroo, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    January 13, 2018 02:37 am at 2:37 am

    ሃገራችን በታሪኳ አሁን እንዳለችበት ያለ ፈተና ገጥሟት አያውቅም። አንድ ሌላውን በቁንጭራ የሚያባርርበት፤ የወያኔ መንግሥት እሳት በየቦታው እየጫረ ቤቱን ንብረቱንና ደኑን የሚያጋይበት ያ ህዝብ በመከራ ውስጥ ይገኛል። ጥቂቶች ጮቤ የሚረግጡባት ይህች ውድ ሃገራችን አዕላፍ ልጆቿ የደም ዋጋ ከፍለው ያቆዮትን ሃገር ዛሬ በዘር፤ በጎሳና በቋንቋ ድንበር ሰርተን አንድ ተሳዳጅ ሌላው አሳዳጅ ለነፍሱ ሯጭ፤ ደሙ በከንቱ የሚፈስባት ሃገር ሆናለች። በመሰረቱ ወያኔ ኢትዮጵያዊነት የማይሰማው ገንጣይ ድርጀት እንደነበርና አሁንም እንደሆነ ተግባሩ ይመሰክራል። በዘፈቀደ በሚለጥፈው የሽብር ህግጋቱ ብዙሃን አፈር እንደለበሱ፤ ቀሪዎች በጨለማ ቤት ሰቆቃን እንደሚቀበሉ የእለት እለት ዘገባዎች ይጠቁማሉ።
    ሃገራችን በወያኔ ሴራ ተመሳቅላለች። ለመኖር በተለሙት የፓለቲካ ትብታብ ብዙዎች እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይበቀል በማለት ህዝባችንን በማያቋርጥ የክፋት በትራቸው እያጠቁት ይገኛሉ። አሁን እንሆ የኦሮሞ ልጆች በጥቅል በመነሳት ወያኔን በቃን በማለታቸው የደረሰባቸውንና ወደፊትም ሊደርስባቸው የሚችለውን ሰቆቃ ጠንቀቀን እናውቃለን። ጊዜው እረዘመ እንጂ አስናቀ ገ/የስ የተባለ የሙዚቃ አቀንቃኝ እንዲህ ብሎ ነበር።

    መች ጠበበን ጎጆው መች ጠበበን ቤቱ
    ኢትዮጵያ፤ እማማ
    በአንድ አብሮ ለመኖር ሰፊ ነው መሬቱ
    ኢትዮጵያ!

    እንዲያው ነገ ከጊዜ ጋር አብሮ ለሚቀየር የዘርና የጎሳ ውስልትና ከመታገል ይልቅ አብሮ መኖርን የሚያጠናክርና ዘለቄታ ላለው አላማ ራስን አሳምኖና ሌሎችንም አስከትሎ በመነሳት ለተጠቃለለና ሁሉም በሰላምና በእኩልነት ለሚኖርባት ሃገርን ለመገንባት ታጥቀን እንነሳ!! በርቱ “ቄሮዎች”!!

    Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    January 26, 2018 02:14 pm at 2:14 pm

    ማንም የሚሰማችሁ የለም!!! ቄሮ! ቄሮ! እያልክ ፊንፊኔ ውስጥ በተለይም፣መጋላ(መርካቶ) ውስጥ ብትጮህ፣ የመጋላው ኪስ ኣውላቂ እንጂ፣የምንለው የለንም!! ፊንፊኔ ያደጉ ኪስ ኣውላቂዎች ናቸው!!!

    Reply
  3. kero says

    February 23, 2018 02:40 pm at 2:40 pm

    If kero has the gut, it should attack the politicians and leaders. No armed struggle in the country was directed at civilians except during the oromo migration/warriors and Ahmed Giragne. Kero is repeating same now. Destruction after destruction………………………………

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule