• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ቄሮ አልሸባብ” ነው – ህወሓት!

January 9, 2018 07:19 pm by Editor 3 Comments

  • “ስድስት ሚሊዮን ወጣት በጠላትነት ፈርጀህ ማንን ልታስተዳድር ነው?” ለማ መገርሳ

ህወሓት/ኢህአዴግ በኢትዮጵ የተለያዩ ክፍሎች በተለይም በምሥራቅ ሐረርጌ “ቄሮ” በመባል የሚታወቅ ሕገወጥ እንቅስቃሴ እመረምራለሁ፤ ለፍርድ አቀርባለሁ ብሎ ዝቷል። “አመራሩ ብቃት የለውም” በማለት ራሱን የገመገመው ህወሓት/ኢህአዴግ ብቃት አልባነቱን ተገንዝቦ ራሱን ከሥልጣን ማግለል ሲገባው አሁንም የማሰርና የማሰቃየት ግፉን በስፋት ለመቀጠል በዕቅድ ለመቀንቀሳቀስ ማሰቡን ነው በዚህ ዜና የገለጸው።

የኢትዮጵያ ወጣቶችን በሥራ በማሰማራት ለአገር እንዲጠቅሙ ከማድረግ ይልቅ “አደገኛ ቦዘኔ” በማለት ሲፈርጅና ሲስር የነበረው ህወሓት አሁን ደግሞ በኦሮሞ ወጣቶች “ቄሮ” ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ለመሰንዘር ጎራዴውን እየሳለ ነው። ግፉ የበዛባቸው ወጣቶች ታላቁ ሩጫ በተካሄደበት ባንድ ወቅት ላይ “አደገኛ ቦዘኔ ራሱ ወያኔ” በማለት ምላሽ መስጠታቸው ይታወሳል።

“ማዕከላዊን እዘጋለሁ፤ ለአገራዊ መግባባት ሲባል እስረኞችን እፈታለሁ” በማለት በአደባባይ የለፈፈው ህወሓት/ኢህአዴግ “ቄሮ” ላይ ዘመቻ በመክፈት በርካታ ማዕከላዊ ለመክፈት ማቀዱንና በሺዎች የሚቆጠሩ ወገኖችን ለማሰቃየት መወሰኑን ይፋ አድርጓል። ይህንኑ የህወሓትን ሃሳብ የሚደግፉ አቀንቃኞቹ “ቄሮ” ማለት “አልሸባብ” ነው፤ እንደ አልሸባብ መታየት አለባቸው እያሉ ነው። የሁለቱም ቃል ትርጉም “ወጣት” ማለት ነው።

በቄሮ ላይ የተነሳውን ዘመቻ አስመልክቶ የጀርመን ድምጽ ራዲዮ ባልደረቦች መርጋ ዮናስና አርያም ተክሌ ያጠናቀሩትን ከዚህ በታች አቅርበናል።

የፌዴራል ፖሊስ የ“ቄሮ” ምርመራ በኦሮሚያ ክልል 

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን በኦሮሚያ ክልል በምሥራቅ ሐረርጌ ዉስጥ በሚንቀሳቀሰው “ቄሮ” በመባል በሚታወቀው የወጣቶች ቡድን ላይ ምርመራ እንደጀመረ የሀገር ዉስጥ ዘገባዎች አመልክተዋል።

የአሮሚያ ክልል የፍትህ ቢሮ የኮሙኒኬሼን ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ታዬ ዳንዳኣ ኮሚሽኑ ይህን ሥራ መጀመሩን የሚያሳይ ምንም መረጃ እንዳልደረሳቸዉ ይናገራሉ።

የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘገባው በእንቅስቃሴው ዉስጥ ቄሮዎቹ ብቻ ሳይሆኑ የአካባቢ ሚሊሽያዎች፣ ፖሊሶችና የወረዳ አመራሮች እንደተሳተፉ ይጠቅሳል። ኮሚሽኑም “ቄሮ” እንዴት እንደተደራጀና አላማዉም ላይ ምርመራ እንደሚያደርግ ዘገባዉ አክሎበታል። የ“ቄሮ” እንቅስቃሴ የመከላከያና የፌዴራል ፖሊስ አባላትን ተልዕኮ አስተጓጉሏል፤ በአካባቢዉ ስጋት ፈጥሯል መባሉም እንደምክንያት ተቀምጧል።

የአምቦ ዩኒቨርስቲ መምሕርና የበየነ መረብ (ኢንተርኔት) ፀሐፊ ስዩም ተሾመ ግን ወጣቶቹ ለማህበረሰቡ ጥያቄ መልስ ለማስገኘት የሚታገሉ እንደሆኑ አስረድተዋል። የኦሮሚያ ክልል መስተዳደር የወጣቶቹን ጥያቄ ተቀብሎ ለማስተናገድ ጥናት ላይ እንደሚገኝ አቶ ስዩም ይናገራሉ። ምክንያቱም አዲሱ የክልሉ መስተዳድር ወደ ስልጣን የመጣዉ ወጣቱ ትዉልድ ወይም “ቄሮ” በፈጠረዉ ጫና አማካኝነት በመሆኑ ባይ ናቸው።

የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ለማ መገርሳ የዛሬ ሁለት ወር ገደማ በድርጅታቸዉ በኦሕዴድ ጉባዔ ላይ ባደረጉት ንግግር “እኛ የፈጠርነዉ ወጣት ትዉልድ ስራ ስላጣ ብቻ ነዉ ወይስ ሌላ ጉዳይ ስላለ ነዉ የጠላን?” በማለት ተሳታፊዎቹን ጠይቀው እንደነበር ይታወሳል። ያኔም ስለ “ቄሮ” ያላቸዉን አስተያየት እንደሚከተለው ገልጸው ነበር።  “ቄሮ ቄሮ ቀሮ፣ እሺ ቄሮ ምንድነዉ? ቄሮን ጠላት አድርጋችሁ ታያላችሁ። ቄሮ ማለት ወጣት ማለት አይደል በአፋን ኦሮሞ? ቁጥሩ በተለይ እየጨመረ ያለውን ስድስት ሚሊዮን ወጣት በጠላትነት ፈርጀህ ማንን ልታስተዳድር ነው? እኛ ሁላችንም እዚህ አንቆይም። የፓርቲዉን አላማ የሚያስቀጥሉት ወጣቶቹ ናቸዉ” ብለው ነበር።

በአሮሚያ ክልል በፍትህ ቢሮ የኮሙኒኬሼን ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ታዬ ዳንዳኣ “ቄሮ” የማሕበረሰቡ ወሳኝ አካል ስለሆነ እነዚህን ወጣቶች በማግለል ወይም እንደ ወንጀለኛ በመፈረጅ እድገትና ሰላም ማምጣት እንደማይቻል የክልሉ መንግስት እንደሚረዳው ለዶይቼ ቬሌ ተናግረዋል።

እንደ አቶ ታዬ አስተሳሰብ፣ ቄሮ የሚባል የወጣት ቅንጅት በምሥራቅ ሐረርጌ ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ በክልሉና በሀገሪቱ የሚንቀሳቀስ ቡድን ነው። የሕግ በላይነት በየትም ቦታ ሊከበር እንደሚገባ ያመለከቱት አቶ ታዬ እስካሁን ቄሮ ተደራጅቶ ወንጀል አለመፈጸሙን አረጋግጠዋል።

የድምጽ መልዕክቱ ከዚህ በታች ይገኛል።

(ምስል፡ የቄሮና የአልሸባብ ምልክቶች ከኢንተርኔት የተወሰዱ)

https://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2018/01/1A876359_2_dwdownload.mp3

ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: al shabab, eprdf, Ethiopia, Full Width Top, meles, Middle Column, oromo, qeerroo, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    January 13, 2018 02:37 am at 2:37 am

    ሃገራችን በታሪኳ አሁን እንዳለችበት ያለ ፈተና ገጥሟት አያውቅም። አንድ ሌላውን በቁንጭራ የሚያባርርበት፤ የወያኔ መንግሥት እሳት በየቦታው እየጫረ ቤቱን ንብረቱንና ደኑን የሚያጋይበት ያ ህዝብ በመከራ ውስጥ ይገኛል። ጥቂቶች ጮቤ የሚረግጡባት ይህች ውድ ሃገራችን አዕላፍ ልጆቿ የደም ዋጋ ከፍለው ያቆዮትን ሃገር ዛሬ በዘር፤ በጎሳና በቋንቋ ድንበር ሰርተን አንድ ተሳዳጅ ሌላው አሳዳጅ ለነፍሱ ሯጭ፤ ደሙ በከንቱ የሚፈስባት ሃገር ሆናለች። በመሰረቱ ወያኔ ኢትዮጵያዊነት የማይሰማው ገንጣይ ድርጀት እንደነበርና አሁንም እንደሆነ ተግባሩ ይመሰክራል። በዘፈቀደ በሚለጥፈው የሽብር ህግጋቱ ብዙሃን አፈር እንደለበሱ፤ ቀሪዎች በጨለማ ቤት ሰቆቃን እንደሚቀበሉ የእለት እለት ዘገባዎች ይጠቁማሉ።
    ሃገራችን በወያኔ ሴራ ተመሳቅላለች። ለመኖር በተለሙት የፓለቲካ ትብታብ ብዙዎች እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይበቀል በማለት ህዝባችንን በማያቋርጥ የክፋት በትራቸው እያጠቁት ይገኛሉ። አሁን እንሆ የኦሮሞ ልጆች በጥቅል በመነሳት ወያኔን በቃን በማለታቸው የደረሰባቸውንና ወደፊትም ሊደርስባቸው የሚችለውን ሰቆቃ ጠንቀቀን እናውቃለን። ጊዜው እረዘመ እንጂ አስናቀ ገ/የስ የተባለ የሙዚቃ አቀንቃኝ እንዲህ ብሎ ነበር።

    መች ጠበበን ጎጆው መች ጠበበን ቤቱ
    ኢትዮጵያ፤ እማማ
    በአንድ አብሮ ለመኖር ሰፊ ነው መሬቱ
    ኢትዮጵያ!

    እንዲያው ነገ ከጊዜ ጋር አብሮ ለሚቀየር የዘርና የጎሳ ውስልትና ከመታገል ይልቅ አብሮ መኖርን የሚያጠናክርና ዘለቄታ ላለው አላማ ራስን አሳምኖና ሌሎችንም አስከትሎ በመነሳት ለተጠቃለለና ሁሉም በሰላምና በእኩልነት ለሚኖርባት ሃገርን ለመገንባት ታጥቀን እንነሳ!! በርቱ “ቄሮዎች”!!

    Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    January 26, 2018 02:14 pm at 2:14 pm

    ማንም የሚሰማችሁ የለም!!! ቄሮ! ቄሮ! እያልክ ፊንፊኔ ውስጥ በተለይም፣መጋላ(መርካቶ) ውስጥ ብትጮህ፣ የመጋላው ኪስ ኣውላቂ እንጂ፣የምንለው የለንም!! ፊንፊኔ ያደጉ ኪስ ኣውላቂዎች ናቸው!!!

    Reply
  3. kero says

    February 23, 2018 02:40 pm at 2:40 pm

    If kero has the gut, it should attack the politicians and leaders. No armed struggle in the country was directed at civilians except during the oromo migration/warriors and Ahmed Giragne. Kero is repeating same now. Destruction after destruction………………………………

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule