• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“አውሬውን አቁስለነዋል፤ ይህ ግን በቂ አይደለም” ለማ መገርሳ

December 27, 2017 12:57 pm by Editor 1 Comment

“አውሬው ቆስሏል*። ቆስሎ ስላልተኛ፣ ማቁሰሉ ብቻ በቂ አይደለም። ተመልሶ እንዳይመጣ እርግጠኞች መሆን አለብን።” የሚለው ቃል የወጣው ከ”ጽንፈኛው ዲያስፖራ” ወይንም ከተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች አይደለም። ከአውሬው ጋር አጋር ሆኖ ከሚሰራ ድርጅት መሪ ነው። ያውም በገዥው ፓርቲ ልሳን። የ26 ዓመቱ ፖለቲካ እየተንከባለለ እዚህ ላይ ደርሷል። አንድ ሰው እውነትን በመናገሩ ጀርባው ተጠንቶ፣ ደሙ ተለክቶ፣ ግንባሩ ተገላልጦ፣ በሽብር በሚፈረጅባት ሃገር ውስጥ፣ ጥቂቶች የእድሜ-ልክ ፈራጅ ሆነው በተሰየሙበት ሃገር ይህ ተከሰት። እነ እስክንድር ነጋ፣ ተመስገን ደሳለኝ፣ አንዷለም አራጌ ከዚህ የባስ ነገር አልተናገሩም። በፍትህ ስም የሚቀለድባቸው እነ ፕ/ር መረራ ጉዲና እና በቀለ ገርባ ይህችን ያህል እንኳን አልተነፈሱም።

መቀሌ ላይ በዝግ ስብሰባ፣ አዲስ አበባ ላይ በዝግ ስብሰባ፣ ፓርላማውም በዝግ ስብሰባ። ሁሉም ተዘጋግቷል። በሃገሪቱ እና በህዝቧ ላይ በዝግ ይዶለታል። ለመፍትሄ ሳይሆን ስልጣን ይዶለታል። በግልጽ ሳይሆን በድብቅ ይዶለታል። መቶ በመቶ መርጦናል ላሉት ሕዝብ ችግሩን ለመደበቅ ይሞክሩ እንጂ፣ ምጣድ ላይ እንዳለ ቡና የሚያምሳቸው ነገር አደባባይ ላይ እንደተሰጣ እንኳ አልባነኑም። ስውር ድርጊታቸው እየገዙት ላለው ሕዝብ ባይተዋር ስለመሆናቸው ማስረገጫ ይሆናል።

ለ35 ቀናት መቀሌ ላይ ዘግተው የዶለቱት፣ ከዚያም አልፈው የነቀሉት እና የተከሉት ነገር፣ መስመር እንደያዘላቸው ተናግረዋል። የህልውናቸው መሰረት የሆነው የመደምሰስ እና የመቆጣጠር ፖሊሲ፣ የህወሃት ስብሰባ ላይ ሰርቶላቸው ሊሆን ይችላል። ሰሜን ላይ ያበጠውን ጎማ አተንፍሰው ሲያበቁ፣ ስንቅ እና ትጥቅ ይዘው ወደ ሸገር ነበር የዘመቱት። እነ ለማን ለማንበርከክ፣ እነ ገዱን ለመጠምዘዝ።

የሸገሩ ዱለታ እንደታሰበው አልሄደም። የመቀሌውን የፖለቲካ ፎርሙላ የአዲስ አበባው ኢህአዴግ ስብሰባ ላይ ለመተግበር መጣራቸው ጅል ያደረጋቸው ነው የሚመስለው። ወትሮውን እንደሮቦት የሚታዘዙ አጋሮቻቸው ባትሪያቸውን እንደጨረሱ አላስተዋሉትም። በሞግዚት አስተዳደሩን ቀጥሉበት-አንቀጥልም ትንቅንቅ፤ በቀድሞው የኢህአዴግኛ  ቋንቋ መግባባት አልቻሉም። እነ ለማ መገርሳን እንደ ቀድሞው ለማዘዝ የማይችሉበት ቅርቃር ውስጥ ተሸንቁረዋል።

የትርምሳቸው ክብደት በኪሎ ባይመዘንም፣ ከጥልቅ ተሃድሶ ወደ ጥልቅ ዝቅጠት መግባታቸውን ግን በይፋ ነግረውናል። ትላንት በስብሰናል ብለው ነበር፣ ዛሬ ዘቅጠናል ብለዋል። ነገ ደግሞ ተልተናል ማለታቸው የሚጠበቅ ነው። የበሰበሰ ነገር የሚያዘግመው ወደዚያው ነው።

እዚያ አካባቢ ነገሮች በፍጥነት ተቀያይረዋል። እንደ ጅብ ከተሰበሰቡበት ዋሻ ለአፍታ ወጣ አሉና  በብሄራዊ ቴሌቪዥን፣ “ሰላም ነን” ለማለት ሞክረው ነበር። “ውስጡን ለቄስ” አሉ። በዚህ አባባላቸው፤ ጉልበታቸውና ፀጋቸዉ እንደበግ ቆዳ ከላያቸው ተገፍፎ እንደሄደ ለማወቅ የፖለቲካ ተንባይ መሆን አያስፈልግም።

“በመሃላችን የርስበርስ መተማመን ጠፍቷል!” ይላል በዝጉ ስብሰባ መሃል የተሰጠው መግለጫ። ይህንን መግለጫ በገለልተኛ ሜዲያ ብንሰማው ኖሮ ላይደንቀን ይችላል። እንግዳ የሆነብን ይህንን መግለጫ በራሳቸው ልሳን መስማታችን ብቻ ሳይሆን፣ ስብሰባው ገና ሳያልቅ መግለጫ መልቀቃቸው ነው። አሁንም ሃገሪቱ የገባችበት ችግር ያስጨነቃቸው አይመስልም። እነሱን እንቅልፍ የነሳቸው አይበገሬ ብለው ያሰቡት የስልጣን ግንዳቸው መንገዳገዱ ነው። ይህንን ሕዝብ መቶ አመት ለመግዛት የወጣው የባለ ራዕዩ እቅድ መሃል ላይ መክሸፉ ነው ይበልጥ የሚያሳስባቸው።

በመግለጫቸው እርስበርስ ተከፋፍለናል ማለትን በመጸየፋቸው፤ አደባባይ የወጣ ክፍፍሉን “መተማመን ጠፋ” በሚል ቃል ሊያሽሞነሙኑት ሞከሩ። መዝቀጣቸውን ግን አልካዱትም። ታዲያ ምን ይጠብቃሉ? የዘቀጠ እና የበሰበሰ ነገር ነፍስ ስለማይዘራ መፍትሄው ልክ እንደ እንቦጭ አራሙቻ መነቀል ብቻ ነው።

ኢትዮጵያ ዛሬ እነ ሚሚ ስብሃቱ የሚቀልዱባት ሃገር ለመሆን መብቃትዋ የመዝቀጣቸው ምልክት ለመሆኑ ቀድሞውንም ወለል ብሎ ይታይ ነበር። አንድ ሺህ ኦሮሞ ሲገደል ለነሱ ዜና አይደለም፣ አስር ሺህ አማራ ሲፈናቀልም ዜና አይደለም፣ ኮንሶ እንደባርያ ንግድ በሰንሰለት እየታሰረ ሲገረፍም የነዚህ ሰዎችን ትኩረት አይስብም። አንድ የትግራይ ተወላጅ ሲገደል ግን ሰበር ዜና ሆኖ ሃገር ይደበላለቃል። የሰው ልጅ ሁሉ እኩል ነው ካሉን፣ ስብእናቸውን ጥያቄ ውስጥ የሚጨምረው ይህ ነው። ማንነታቸው ጫፍ የሚፈተነው እዚህ ላይ ነው። የሰው ዘር ደሙ በካራት እየተለካ፣ የወርቅ፣ መዳብና ነሃስ ስያሜ ካመጣብን አገዛዝ ከዚህ የተሻለ ነገር አንጠብቅም።

አንዱን ዘር ከፍ ሌላውን ደግሞ ዝቅ በማድረጋቸው የተወደዱ በሚመስላቸው አድርባዮችና አሽቃባጮች ታጭቀው ረጅም መዝለቅ እንደማችሉ ይመስላል አዲስ ዘመን ጋዜጣ በርዕሰ አንቀፁ “የአገር ጠንቆችን ይዞ ማዝገም ለህዝብ እና ለመንግስት አደገኛ” መሆኑን የገለጸው። “አይጥ ርሃብ ሲጠናባት የራስዋን ጅራት ትበላለች” ይባል የለ።

ለማ መገርሳ በኦሮምኛ ቋንቋ በተደረገ አንድ ዘጋቢ ፊልም ላይ ነው “አውሬውን አቁስለነዋል” ያሉት። ምን ለማለት እና፣ ማንን ለማለትም እንደፈለጉ ግልጽ ነው። አንድን ዘር ከሌላ ዘር እያጋጨ፣ ጎሳን ከጎሳ እያተራመሰ፣ ሃይማኖትና ከሃይማኖት እንዳይተማመን እያደረገ የነበረው አውሬ ቆስሏል። ከ26 ዓመታት ስራው በኋላ ይህ ትውልድ የባነነበት አውሬ። የቆሰለ፣ በሞት እና በህይወት መካከል ያለ አውሬ፣  መፍጨርጨሩ የግድ ነው። መሬት ልሶም የመነሳት እድል ይኖረዋል። ጣልያናዊው ማኪያቬሊ የሚለውም ከዚህ ጋር ይመሳሰላል። አልጋወራሹ ላይ ከተኮስክበት ጨርሰው፤ ካልጨረስከው ይመለስብሃል። በሳል ፖለቲከኞች የማይጨርሱትን አይጀምሩትም።

በሽፍታ የምትተዳደር ሃገር፣ በሽፍቶች የሚገዛ ሕዝብ፤ …       ስብዕናቸውን ባዋረዱ በፖለቲካ ዘገምተኛ ምሁራን ጭምብል ውስጥ ተጠቅልለው፣ ኢትዮጵያን እንደምስጥ እየቦረቦሩ፣ እንደ መዥገርም እየመጠጡ እስካሁን ዘልቀዋል። አሁን ግን ቆስለው እየተወራጩ ይገኛሉ። “ሌባ ተብሎ ከመፈረጅ የበለጠ ውርደት በታሪክ ሊኖር አይችልም” ይሉናል ለማ መገርሳ።

እስካሁን የፖለቲካ ንግድ የሸቀሉበትን የሙት ራዕይም መቀሌ ላይ ቀብረውት መጥተዋል። የሟቹን መነጽር በሮቦቱ ሰው ላይ አድርገው፣ የጀመሩት ‘የመለስ ራዕይ’፣ ‘የመለስ ቅርስ’፣ ‘የመለስ ሌጋሲ’፣ ‘የመለስ ሕልም’ እና ‘የመለስ ውርስ’ ሁሉ ብዙ አላስኬደም። እንዲያው ያልተሳካ ተውኔት ሆኖ አለፏል። ይልቁንም ሰውዬው የአዜብን ደጅ ጠንተው ያገኟት የቤተ መንግስት ወንበር ዛሬ እሾህ ሆና እየወጋቻቸው መሆኑን እየተናገሩ ነው።

ብዙዎች ሃገሪቱ መስቀለኛ መንገድ ላይ መሆንዋን ሲናገሩ ይሰማል። አቅጣጫው በውል የማይታወቅ ግራ የሚያጋባ መንገድ። መስቀለኛ ሚሆነው መንገዱ ሲኖር አይደል? በእኔ እይታ ግን መንገድ የለም። ሁሉም ተዘጋግቷል። በሁሉም አቅጣጫ የተዘጋጋ መንገድ መጓዝ ቅርቃር ውስጥ መግባት እንጂ መስቀለኛ ሊሆን አይችም።

ከዚህም ከዚያም ብሶት እና ሕዝባዊ ማዕበል እንሰማለን። አመጹ፣ ስርዓቱን አላፈናፍን ያለው ይመስላል። ውጥረቱ ሊላላ የማይችልበት፣ እሳቱ ሊጠፋም የማይችልበት ደረጃ ደርሷል። ግን የህወሃት ቀብር እስከመጨረሻው የሚፈጸመው፣ አዲስ አበባ ሲያምጽ ብቻ መሆኑ ግልጽ ነው። መታሰር፣ መሰቃየት እና መገደልን ለምዶታል፣ መታረዝ እና መራብ አዲስ አይደለም። ውሃ፣ መብራት፣ ስልክ፣ … ሲፈልጉ የሚሉቅቁት ሲያሻቸው ደግሞ የሚከለክሉት ሕዝብ፣ አይቶ እንዳላየ ይምሰል እንጂ ልቡ ሸፍቷል። ይህ ህዝብ ጽዋው ሞልቶ እለት የት እንደሚገቡ እናያለን።

 አመጽ በቀጠሮ አይነሳም። መምጫው ባይታወቅም፣ ምልክቶች ግን ይታያሉ።

“መጀመሪያ ይንቁሃል። ከዚያ ቀጥሎ ይስቁብሃል። ገፋ ብለው ይጣሉሃል። … በመጨረሻ ግን ታሸንፋቸዋለህ!” ማህተመ ጋንዲ።

* ከዚህ ላይ የተወሰደ ነው (ፎቶ: ከግራ ወደቀኝ ፓስተር ገመቺስ ቡባ፣ ጌታቸው ረዳ፣ የኦሮሞዎች መገደል ትክክል ነው ያለ አዲሱ ገብረእግዚአብሔር እና ለማ መገርሳ)

ክንፉ አሰፋ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: eprdf, gimgema, Left Column, legacy, lemma, meles, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Abdisa says

    December 28, 2017 12:08 pm at 12:08 pm

    I think he threw this phrase to indicate the fighting with contraband dealers. I hope he did mean that he has wounded TPLT, OPDO’s Godfather.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule