• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሓት/ኢህአዴግ “አሸባሪ” እስረኞችን እፈታለሁ አለ

January 3, 2018 10:10 am by Editor 2 Comments

ላለፉት በርካታ ዓመታት በየአደባባዩ “በኢትዮጵያ ውስጥ አንድም የፖለቲካ እስረኛ የለም” ሲል የነበረው ህወሓት/ኢህአዴግ ዛሬ በኃይለማርያም አማካኝነት “እስረኞችን እፈታለሁ፥ ማዕከላዊን እዘጋለሁ” ብሏል።

ባለፉት ዓመታት በግፍ የታሰሩት በሙሉ የተከሰሱት በአሸባሪነት መሆኑ የሚታወቅ ነው።

ይህ መግለጫ በራሱ ህወሓት/ኢህአዴግ ሲዋሽ እንደነበር የሚያሳይ ነው ወይም ይቺ ጊዜ መግዣ የህወሓት ጨዋታ ነች።

ለሁሉም በመቆየት የሚታይ ነው።

የእኛ አቋም ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በፖለቲካ አመለካከቱ መታሰር የለበትም፥ በግፍ የታሰሩት ሁሉም የፖለቲካ እና የኅሊና እሥረኞች ህወሓት/ኢህአዴግ ይቅርታ እየጠየቀ ካሣ ከፍሎ በነጻ ይልቀቃቸው ነው።

ጎልጉል!

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News, Politics Tagged With: eprdf, Right Column - Primary Sidebar, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. በለው! says

    January 3, 2018 08:44 pm at 8:44 pm

    “ሰበር ዜና፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የፖለቲካ እስረኞች በሙሉ እንደሚፈቱ ጠቅላይ ሚኒስቴር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ አስታወቁ፡
    ___________________________________________!
    ፖለቲከኛ እስረኞች የዲሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት በማሰብ ክሳቸው ተቋርጦ ወይም በይቅርታ እንዲለቀቁ ተወስኗል- ጠ/ሚ ኃይለማርያም
    ———————————————————–!
    “በፈፀሙት ወንጀል ምክንያት በፍርድ ቤት የተፈረደባቸው ወይም ደግሞ ወንጀል በመፈፀም ድርጊት ተጠርጥረው በአቃቢ ህግ ጉዳያቸው ተይዞ በእስር የሚገኙ አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲ አባላትን ጨምሮ ሌሎች ግለሰቦች የተሻለ ሃገራዊ መግባባት ለመፍጠርና የዲሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት በማሰብ ክሳቸው ተቋርጦ ወይም በምህረት ህግና ህገመንግሥቱ በሚፈቅደው መልኩ ተገቢው ማጣራት ተደርጎ እንዲፈቱ ይደረጋል::”-ጠቅላይ ሚኒስተር ሃይለማርያም ደሳለኝ
    *************************!
    *ማዕከላዊ እስር ቤት ይዘጋል ተብሏል..
    __ እርግጠኛ ነኝ ማሰር ቆሟል አላሉም። ይልቁንም ከፍተኛ ቁጥር ዕሥረኛ የሚይዝ፡ ደርጃውን የጠበቀ ዘመናዊ እሥር ቤት፡ በከፍተኛ ወጪ እንደተገነባ ተነግሯል። ዓለም በቃኝ እሥር ቤት ተዘግቶ፡ ኢትዮጵያ በቃችን የሁሉም የቁም እሥር ቤት ሲከፈት እንዲህ ጮቤ ያስረግጣል?

    * ድርድርም ከተቃዋሚዎች ጋር እንደሚካሄድ ተጠቁሟል…
    ___ አንድ መንግስትና ብዙ ፓርቲ ሰፈርተኞች ቢደረድሩ ጥቅሙና ተጠቃሚው ማነው? የፓርቲ ብዛት ያለጥራት የልዩ ጥቅማጥቅመኛ ማበርከት ተሞሳሟሽና ኪራይ ሰብሳቢ ወሮበላ፡አድርባይ መፈለፈያ እንጂ፡ ለማኅበረሰቡ የሰላም፡ የእኩል ተጠቃሚነት፡ የትምህርትና ጤና፡ የተቋማት ግንባታ ላልፉት ፳፯ ምንም አልታየም፡ የመድብለ ፓርቲ፡ አብዮታዊ ዲሞክራሲ፡ዲሞክራሲያዊ ብሔርተኝነት(ብዝሃነት) ማጣፈጫ የዜናና ለፎቶ ለማስረጃነት ጥሩ መናጆ ሆነው ከውስጥም ከውጭም እያጭበረበሩ ፡ትውልድ ሲያጥበረብሩ…ሀገርና የሕዝብ ንብረት በመበዝበር ተቃዋሚ/ተቋቋሚ ሆነው የሀገር ሀብት አብረው ሲመዝብሩ፡ ወጣቱን አላግባብ ጭዳ ሲገብሩ ኖረዋል ይኖራሉም።

    * ክሳቸው በመካሄድ ላይ ያሉ የፖለቲካ እስረኞችም ክሳቸው ይቋረጣል ተብሏል…
    ___ ሀወሓት/ኢህአዴግ ከአጋርና ተደርዳሪ ፓርቲዎቹ ይልቅ ዲያስፐሩን በደንብ ያደምጣል፡ሁሉም እሥረኛ ይፈታ ቅድመ ሁኔታ አስቀምጠው ሲያፏጩ ነበር አሁን ችግራቸው ተፈታ አርፈው ይቀመጣሉ? አጀንዳ ቀይረው ይቀወጣሉ?
    እነሱን ብሆን ቅድሚያ የሕዝብ መፈታት አስቀድም ነበር። ለነገሩ ዲያስፐሮቹ ህወሓት/ኢህአዴግ አሰልጥኖ የለቀቃቸው ግብረኅይሎች ስለሆኑ እርስ በርስ ይረዳዳሉ፡ተቃዋሚ ትብዬዎች ግን ትግል ላይ ሳይሆኑ በጎን ልፊያ ተጠምደዋል/ተጣምደዋልም ለምሳሌ፡… አዲስ አበባ አይስፋፋ ሲሉት እሺ፡ ልዩ ጥቅም ይከበር ሲሉት እሺ፡ እሥረኛ ይፈታ ሲሉት እሺ፡ ለነገሩ..ሌባ! ሌባ!…መንግስት የለም ወይ! ሲሉት በሞቀታ ተነሳስቶ ይሆናል።አሁን ያልሰማው ቅላጼ ግን ሰው ከክልል እስረኛነት እያፈተለከ፡ ኢትዮጵያ ኬኛ! ቢመችሽም ባይመችሽም ወያኔ አንለቅሽም! ይናዳል ይናዳል ገደሉ ይህ ነው የኢትዮጵያዊ ገድሉ!ብለዋል፡ ነን ሰቤ?
    ጋዜጠኞች የፖለቲካ እሥራኛ ናቸውን? በሀገሪቱ የነበረው ሰልፍ የፖለቲካ ነው የብሔር ብሔረሰብ እና ሕዝቦች ትዕይንት? የሚፈቱት ፈረንጅ ያወቃቸው ናቸው?የሀገሪቱ ሕግ አላግባብ ታስረው ነበር አላቸው? ከሆነስ ካሳያገኛሉን?

    *አገዛዙ ለመጀመሪያ ጊዜ የፖለቲካ እስረኞች መኖራቸውን አምኗል…

    __የፖለቲካ እሥረኞች እነማን ናቸው?
    *ፖለቲካ ማለት አቋም/መርህ/ርዕዮት ከሆነ ሰዎች በፖለቲካ አስተሳሰባቸው/አመለካከታቸው ልዩነት ብቻ ለምን ታሰሩ? የኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚ የሰሞኑ ማላገጫ የሚለው “ላጠፋነውና ላሰርነው ይቅርታ ለምናስረውና ለምናጠፋው ታገሱን ጭራሽም ተባብሩን” ነው፡ ታዲህ ይህ ማንን ለማስደሰት ነው? ሜ/ጄ አባዱላ ‘የተናቀው ህዝቡና ፓርቲው’ ጥያቄ የተመለሰውና ‘ወጣ ገባ’ የሆነው ለዚች ነው? እንግዲህ ኦነግ፡ ኦብነግ፡ ግንቦት ፯፡ መስከረም ፪፡ ታስረው የተፈቱ ያፈነገጡና የተባረሩ ግንቦት ፳፯ ፓርላማ ሊገቡ ነው?፡ ኢሳትና ኦሮሞ ሚዲያ ከአሸባሪነት ነጻ ሆኑ ማለት ነው? መቼም እየጻፈ ፖለቲካ የሚተች እስክሪብቶ ማምረቻን በመዝጋት ፀሐፊን መግታት ይቻላል ማለት ድድብና እንጂ ብልሃት አደለም።
    __ የፖለቲካ ምሕዳር ማስፋት ሲባልም እያሰሩ መፍታት አሮጌውን እሥር ቤት ማዕከል አድርጎ ሲዖል በመገንባት ሳይሆን የተተቹበትን ስሕተት ማመንና ማስተካከል፡ ጭራሽም መካሪ አታሳጣኝ ሲሉ ሚዲያና ተፎካካሪ ፓርቲዎችን በሕግና ሥርዓት መጥኖ (ከብዛት ጥራት) እንዲደራጁ መፍቀድና ማገዝ የግድ ነው።
    __የፖለቲካ ፓርቲዎች የራሳቸው ሚዲያ፡ የተሟላ ጽ/ቤት ተገቢውን የሕግ ከለላ፡ ተመፅዋች (አሳውቀውና አስፈቅደው) በሙሉ የዜግነት ነጻነት፡ እንዲኖራቸው ማድረግ ግን የበለጠ ለገዢው/አውራው/ ነጻ አውጭው ፓርቲ፡ ተቋማቱና ደጋፊ/ተደጋፊ አባላቱ ዋስትና ነው።ለሀገር ሠላምና ደህንነት እሥረኛ ቅነሳ፡ ከአላግባብ የሕዝብ ንብረት ብክነትና ውድመት ያድናል ።አራት ነጥብ።

    Reply
  2. Ali says

    January 3, 2018 10:33 pm at 10:33 pm

    Exactly! These prisoners & families need compensated! Imagine the damag that has taken place within the families. How many have died in the prisons? How many have lost their their income, directly or indirectly? How many have migrated, or died on the desert and sea shores?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule