• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሓት/ኢህአዴግ “አሸባሪ” እስረኞችን እፈታለሁ አለ

January 3, 2018 10:10 am by Editor 2 Comments

ላለፉት በርካታ ዓመታት በየአደባባዩ “በኢትዮጵያ ውስጥ አንድም የፖለቲካ እስረኛ የለም” ሲል የነበረው ህወሓት/ኢህአዴግ ዛሬ በኃይለማርያም አማካኝነት “እስረኞችን እፈታለሁ፥ ማዕከላዊን እዘጋለሁ” ብሏል።

ባለፉት ዓመታት በግፍ የታሰሩት በሙሉ የተከሰሱት በአሸባሪነት መሆኑ የሚታወቅ ነው።

ይህ መግለጫ በራሱ ህወሓት/ኢህአዴግ ሲዋሽ እንደነበር የሚያሳይ ነው ወይም ይቺ ጊዜ መግዣ የህወሓት ጨዋታ ነች።

ለሁሉም በመቆየት የሚታይ ነው።

የእኛ አቋም ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በፖለቲካ አመለካከቱ መታሰር የለበትም፥ በግፍ የታሰሩት ሁሉም የፖለቲካ እና የኅሊና እሥረኞች ህወሓት/ኢህአዴግ ይቅርታ እየጠየቀ ካሣ ከፍሎ በነጻ ይልቀቃቸው ነው።

ጎልጉል!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: eprdf, Right Column - Primary Sidebar, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. በለው! says

    January 3, 2018 08:44 pm at 8:44 pm

    “ሰበር ዜና፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የፖለቲካ እስረኞች በሙሉ እንደሚፈቱ ጠቅላይ ሚኒስቴር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ አስታወቁ፡
    ___________________________________________!
    ፖለቲከኛ እስረኞች የዲሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት በማሰብ ክሳቸው ተቋርጦ ወይም በይቅርታ እንዲለቀቁ ተወስኗል- ጠ/ሚ ኃይለማርያም
    ———————————————————–!
    “በፈፀሙት ወንጀል ምክንያት በፍርድ ቤት የተፈረደባቸው ወይም ደግሞ ወንጀል በመፈፀም ድርጊት ተጠርጥረው በአቃቢ ህግ ጉዳያቸው ተይዞ በእስር የሚገኙ አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲ አባላትን ጨምሮ ሌሎች ግለሰቦች የተሻለ ሃገራዊ መግባባት ለመፍጠርና የዲሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት በማሰብ ክሳቸው ተቋርጦ ወይም በምህረት ህግና ህገመንግሥቱ በሚፈቅደው መልኩ ተገቢው ማጣራት ተደርጎ እንዲፈቱ ይደረጋል::”-ጠቅላይ ሚኒስተር ሃይለማርያም ደሳለኝ
    *************************!
    *ማዕከላዊ እስር ቤት ይዘጋል ተብሏል..
    __ እርግጠኛ ነኝ ማሰር ቆሟል አላሉም። ይልቁንም ከፍተኛ ቁጥር ዕሥረኛ የሚይዝ፡ ደርጃውን የጠበቀ ዘመናዊ እሥር ቤት፡ በከፍተኛ ወጪ እንደተገነባ ተነግሯል። ዓለም በቃኝ እሥር ቤት ተዘግቶ፡ ኢትዮጵያ በቃችን የሁሉም የቁም እሥር ቤት ሲከፈት እንዲህ ጮቤ ያስረግጣል?

    * ድርድርም ከተቃዋሚዎች ጋር እንደሚካሄድ ተጠቁሟል…
    ___ አንድ መንግስትና ብዙ ፓርቲ ሰፈርተኞች ቢደረድሩ ጥቅሙና ተጠቃሚው ማነው? የፓርቲ ብዛት ያለጥራት የልዩ ጥቅማጥቅመኛ ማበርከት ተሞሳሟሽና ኪራይ ሰብሳቢ ወሮበላ፡አድርባይ መፈለፈያ እንጂ፡ ለማኅበረሰቡ የሰላም፡ የእኩል ተጠቃሚነት፡ የትምህርትና ጤና፡ የተቋማት ግንባታ ላልፉት ፳፯ ምንም አልታየም፡ የመድብለ ፓርቲ፡ አብዮታዊ ዲሞክራሲ፡ዲሞክራሲያዊ ብሔርተኝነት(ብዝሃነት) ማጣፈጫ የዜናና ለፎቶ ለማስረጃነት ጥሩ መናጆ ሆነው ከውስጥም ከውጭም እያጭበረበሩ ፡ትውልድ ሲያጥበረብሩ…ሀገርና የሕዝብ ንብረት በመበዝበር ተቃዋሚ/ተቋቋሚ ሆነው የሀገር ሀብት አብረው ሲመዝብሩ፡ ወጣቱን አላግባብ ጭዳ ሲገብሩ ኖረዋል ይኖራሉም።

    * ክሳቸው በመካሄድ ላይ ያሉ የፖለቲካ እስረኞችም ክሳቸው ይቋረጣል ተብሏል…
    ___ ሀወሓት/ኢህአዴግ ከአጋርና ተደርዳሪ ፓርቲዎቹ ይልቅ ዲያስፐሩን በደንብ ያደምጣል፡ሁሉም እሥረኛ ይፈታ ቅድመ ሁኔታ አስቀምጠው ሲያፏጩ ነበር አሁን ችግራቸው ተፈታ አርፈው ይቀመጣሉ? አጀንዳ ቀይረው ይቀወጣሉ?
    እነሱን ብሆን ቅድሚያ የሕዝብ መፈታት አስቀድም ነበር። ለነገሩ ዲያስፐሮቹ ህወሓት/ኢህአዴግ አሰልጥኖ የለቀቃቸው ግብረኅይሎች ስለሆኑ እርስ በርስ ይረዳዳሉ፡ተቃዋሚ ትብዬዎች ግን ትግል ላይ ሳይሆኑ በጎን ልፊያ ተጠምደዋል/ተጣምደዋልም ለምሳሌ፡… አዲስ አበባ አይስፋፋ ሲሉት እሺ፡ ልዩ ጥቅም ይከበር ሲሉት እሺ፡ እሥረኛ ይፈታ ሲሉት እሺ፡ ለነገሩ..ሌባ! ሌባ!…መንግስት የለም ወይ! ሲሉት በሞቀታ ተነሳስቶ ይሆናል።አሁን ያልሰማው ቅላጼ ግን ሰው ከክልል እስረኛነት እያፈተለከ፡ ኢትዮጵያ ኬኛ! ቢመችሽም ባይመችሽም ወያኔ አንለቅሽም! ይናዳል ይናዳል ገደሉ ይህ ነው የኢትዮጵያዊ ገድሉ!ብለዋል፡ ነን ሰቤ?
    ጋዜጠኞች የፖለቲካ እሥራኛ ናቸውን? በሀገሪቱ የነበረው ሰልፍ የፖለቲካ ነው የብሔር ብሔረሰብ እና ሕዝቦች ትዕይንት? የሚፈቱት ፈረንጅ ያወቃቸው ናቸው?የሀገሪቱ ሕግ አላግባብ ታስረው ነበር አላቸው? ከሆነስ ካሳያገኛሉን?

    *አገዛዙ ለመጀመሪያ ጊዜ የፖለቲካ እስረኞች መኖራቸውን አምኗል…

    __የፖለቲካ እሥረኞች እነማን ናቸው?
    *ፖለቲካ ማለት አቋም/መርህ/ርዕዮት ከሆነ ሰዎች በፖለቲካ አስተሳሰባቸው/አመለካከታቸው ልዩነት ብቻ ለምን ታሰሩ? የኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚ የሰሞኑ ማላገጫ የሚለው “ላጠፋነውና ላሰርነው ይቅርታ ለምናስረውና ለምናጠፋው ታገሱን ጭራሽም ተባብሩን” ነው፡ ታዲህ ይህ ማንን ለማስደሰት ነው? ሜ/ጄ አባዱላ ‘የተናቀው ህዝቡና ፓርቲው’ ጥያቄ የተመለሰውና ‘ወጣ ገባ’ የሆነው ለዚች ነው? እንግዲህ ኦነግ፡ ኦብነግ፡ ግንቦት ፯፡ መስከረም ፪፡ ታስረው የተፈቱ ያፈነገጡና የተባረሩ ግንቦት ፳፯ ፓርላማ ሊገቡ ነው?፡ ኢሳትና ኦሮሞ ሚዲያ ከአሸባሪነት ነጻ ሆኑ ማለት ነው? መቼም እየጻፈ ፖለቲካ የሚተች እስክሪብቶ ማምረቻን በመዝጋት ፀሐፊን መግታት ይቻላል ማለት ድድብና እንጂ ብልሃት አደለም።
    __ የፖለቲካ ምሕዳር ማስፋት ሲባልም እያሰሩ መፍታት አሮጌውን እሥር ቤት ማዕከል አድርጎ ሲዖል በመገንባት ሳይሆን የተተቹበትን ስሕተት ማመንና ማስተካከል፡ ጭራሽም መካሪ አታሳጣኝ ሲሉ ሚዲያና ተፎካካሪ ፓርቲዎችን በሕግና ሥርዓት መጥኖ (ከብዛት ጥራት) እንዲደራጁ መፍቀድና ማገዝ የግድ ነው።
    __የፖለቲካ ፓርቲዎች የራሳቸው ሚዲያ፡ የተሟላ ጽ/ቤት ተገቢውን የሕግ ከለላ፡ ተመፅዋች (አሳውቀውና አስፈቅደው) በሙሉ የዜግነት ነጻነት፡ እንዲኖራቸው ማድረግ ግን የበለጠ ለገዢው/አውራው/ ነጻ አውጭው ፓርቲ፡ ተቋማቱና ደጋፊ/ተደጋፊ አባላቱ ዋስትና ነው።ለሀገር ሠላምና ደህንነት እሥረኛ ቅነሳ፡ ከአላግባብ የሕዝብ ንብረት ብክነትና ውድመት ያድናል ።አራት ነጥብ።

    Reply
  2. Ali says

    January 3, 2018 10:33 pm at 10:33 pm

    Exactly! These prisoners & families need compensated! Imagine the damag that has taken place within the families. How many have died in the prisons? How many have lost their their income, directly or indirectly? How many have migrated, or died on the desert and sea shores?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule