ይህ ቃለ ምልልስ “መለስ የቆፈሩት ጉድጓድ” በሚል ርዕስ የዛሬ ስምንት ዓመት May 20, 2013 አትመነው ነበር። የኢትዮጵያን የውድቀት ጉድጓድ ሲቆፍር የነበረውና በአገዛዝ ሥልጣን ላይ በነበረበት ጊዜ ጉድጓዱን በጥልቀት ሲቆፍር የነበረው መለስ ዜናዊ “ካልበላኋት አፈርሳታለሁ” ከሚለው የትህነግ ምኞት ቀድሞ ጥልቁ ጉድጓድ ውስጥ ከገባ እነሆ 9 ዓመት ሆነው። ዛሬ በሙት መንፈስ የሚመሩት “ተዝካራቸውን” የሚያወጡበት ቀን ነው። ለዝክሩ እንዲሆናቸው ይህንን ቃለምልልስ ደግመን አቅርበነዋል። ከዚያ በፊት ዘና እንድትሉ ይቺን አጭር ቪዲዮ ይመልከቱ፤ ይህ ቃለ ምልልስ “መለስ የቆፈሩት ጉድጓድ” በሚል ርዕስ May 20, 2013 አትመነው ነበር። የኢትዮጵያን የውድቀት ጉድጓድ ሲቆፍሩ የነበሩትና በአገዛዝ ሥልጣን ላይ በነበሩበት ጊዜ ጉድጓዱን በጥልቀት ሲቆፍሩ የነበሩት መለስ … [Read more...] about መለስ ዜናዊ በመሞት የሠራልን ውለታ 9ኛ ዓመት ሲታሰብ
Archives for August 2021
ትህነግ በሰሜን ወሎ የፈጸመው ጭፍጨፋ የሳተላይት መረጃ
ከሰሞኑን በእንግሊዙ የቴሌግራፍ ጋዜጣ የወጣው የምርመራ ሪፖርት መነጋገሪያ ሆኗል። ሪፖርቱ በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ አከባቢ አጋምሳ ተብላ የምትጠራ ከአፋር ክልል የጥቂት ኪሎሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ መንደር ሙሉ በሙሉ መውደሙን በሳተላይት ምስል በታገዘ ሁኔታ ቀርቧል። ሪፖርቱን ያዘጋጀው ጋዜጠኛ ዘካሪያስ ዘላለም፥ በተደረገው የምርመራ ስራና ከአከባቢው ወደ ደሴ የተፈናቀሉት ንጹሃኖች በማነጋገር የጦር ወንጀል የተፈጸመው በአከባቢው ይንቀሳቀሱ የነበሩት የ "ትግራይ ሃይሎች" መሆኑን ደርሰንበታል ብሏል። በተጠቃው አከባቢ ላይ አብዛኛው ነዋሪ በግብርና ስራ የሚተዳደሩ ሲሆኑ ከሳተላይት ምስሎችን በመመልከት ከ50 በላይ ጎጆ ቤቶች መቃጠላቸውንና ቃጠሎዉ ከሃምሌ 26 እለት ጀምሮ መፈጸሙንም ማረጋገጥ መቻሉን የጋዜጣው ሪፖርት ያስረዳል። ጋዜጠኛው፥ የሳተላይት ምስል … [Read more...] about ትህነግ በሰሜን ወሎ የፈጸመው ጭፍጨፋ የሳተላይት መረጃ
ባለፉት 24 ሰዓታት የትህነግ የሽብር ቡድን ላይ በተወሰደ እርምጃ ጀብዱ ተፈጽሟል፡- የአማራ ክልል
አሸባሪው የትህነግ ቡድን በኃይል በወረራቸው አካባቢዎች ላይ በተሰወሰደ ወታደራዊ እርምጃ ታላላቅ ጀብዱዎች መፈጸማቸውን የአማራ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ገለፁ፡፡ ዋና ዳይሬክተሩ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ባለፉት 24 ሰዓታት በወልድያና አካባቢው፣ ጋይትና አካባቢው፣ ዛሬማና አካባቢው፣ ሰቆጣና አካባቢው፣ ጋሸናና አካባቢው በትህነግ የሽብር ቡድን ላይ በተወሰደ ወታደራዊ እርምጃ ታላላቅ ጀብዱዎች መፈጸማቸውን ተናግረዋል፡፡ በዚህም የሽብር ቡድኑ የደረሰበት ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ ከባድ መሆኑንም ነው አቶ ሙሉነህ የገለፁት፡፡ ይህ ሆኖ ሳለ የማህበረሰብ አንቂዎች በማወቅም ይሁን ባለማወቅ በማህበራዊ ተስስር ገፆች የትህነግ የሽብር ቡድንን ለመደምሰስ የሚደረገውን ጥረት የሚያደናቅፉ መረጃዎችን ከማሰራጨት እንዲታቀቡ አቶ ግዛቸው … [Read more...] about ባለፉት 24 ሰዓታት የትህነግ የሽብር ቡድን ላይ በተወሰደ እርምጃ ጀብዱ ተፈጽሟል፡- የአማራ ክልል
በክምር ድንጋይ የተሠራ ጀብድ
በክምር ድንጋይ አንድ የአማራ ጀግና 11 የአሸባሪው ትህነግ ታጣቂዎችን ደመሰሰ። የአሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድን ታጣቂዎች በክምር ድንጋይ ከተማ ወደ አንድ ግለሰብ ቤት በመሄድ ለማጥቃትና ለመዝረፍ ተዘጋጁ። ታጣቂዎች ግለሰቡ ቤት ደረሱ። ይህንን ቀድሞ የተረዳው ግለሰብም በጥበብና በብልሃት የመጡትን የአሸባሪውን ቡድን ታጣቂዎች አዘናጋቸው። ሌላ ኃይል አብሯቸው እንደሌለ ወደ ውጪ ወጣ በማለት ካረጋገጠ በኋላ ወደ ጓዳው በመግባት ተቀባብሎ የነበረውን መሣሪያ ይዞ በመውጣት እርምጃ ወስዶባቸዋል። ሊያጠቁትና ሊዘርፉት እንደመጡ የተረዳው ይህ ግለሰብ ያለውን መሣሪያ በመጠቀም በቤቱ የተሰበሰቡትን 11 የአሸባሪውን ትህነግ ታጣቂዎች እንዳልሆኑ በማድረግ ጀግንነቱን አሳይቷል። አሁን ላይም ይህ ጀግና ቀሪ የአሸባሪውን ቡድን አባላትን እያሳደደ ይገኛል። ጠላትን አይቀጡ … [Read more...] about በክምር ድንጋይ የተሠራ ጀብድ
የሁርሶ ሠልጣኞች በብቃት እየተዘጋጁ ነው
"ሀገርን ለማዳን እዘምታለሁ የትም መቼም በምንም" በሚል መሪ ቃል ፀረ ሰላም ሀይሎችን ለመፋለም ቆርጠው የተነሱ የቁርጥ ቀን ልጆች በሀገሪቷ በሚገኙ የውትድርና ማሰልጠኛ ትምህርት ቤቶች በመግባት ስልጠናቸውን እየተከታተሉ ይገኛሉ፡፡ የሁርሶ ኮንቲጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ከዚህ ቀደም በርካታ የሰራዊት አባላትን በሁለት ዙሮች አሰልጥኖ ያስመረቀ ሲሆን÷ በአሁኑ ጊዜም የ3ኛ ዙር ሰልጣኞችን በማሰልጠን ላይ ይገኛል፡፡ አሰልጣኝ የ22ኛ ሻለቃ ዘመቻ ሀላፊ መቶ አለቃ ዲኔ መሀመድ የዚህ ዙር ሰልጣኞች ከሁለቱ ዙር ሰልጣኞች ለየት የሚያደርገው ሀገርን ለማፈራረስ የተነሱት የሀገር ሀዲዎች የህወሓት እና የሸኔ የሽብር ቡድኖችን ለመፋለምና ሀገርን ከመፈራረስ ታድጎ አንድነቷን ለማስቀጠል ለሀገሬ እዘምታለሁ በማለት ሀገራዊ ጥሪውን ተቀብለው ወደ ስልጠናው የተካተቱ መሆናቸው ነው … [Read more...] about የሁርሶ ሠልጣኞች በብቃት እየተዘጋጁ ነው
ሀብትና የገቢ ምንጫቸውን ያላስመዘገቡ በህግ ሊጠየቁ ነው
ሀብትና የገቢ ምንጫቸውን ለማስመዝገብ ፈቃደኛ ያልሆኑ 62 የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራንና ሰራተኞች በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን የፌደራል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ በኮሚሽኑ የፀረ-ሙስና ህግ ምክር፣ ትግበራና ልምድ ቅመራ ዳይሬክተር አቶ ገዛኸኝ ጋሻው እንደገለፁት ሀብትና የገቢ ምንጫቸውን ለማስመዝገብ ፈቃደኛ ያልሆኑት 16 የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ የኒቨርሲቲና 46 የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና ሠራተኞች ናቸው፡፡ ማንኛውም የመንግስት ተሿሚ፣ የህዝብ ተመራጭ እና የመንግስት መስሪያ ቤቶችና የልማት ድርቶች እንዲሁም የህዝባዊ ድርጅት ሰራተኞች የቤተሰቦቻቸውን ጨምሮ ሀብትና የገቢ ምንጫቸውን ማስመዝገብ እንዳለባቸው ቢደነገግም ህጉን የሚተላለፉ በመኖራቸው ተጠያቂ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ዳይሬክተሩ … [Read more...] about ሀብትና የገቢ ምንጫቸውን ያላስመዘገቡ በህግ ሊጠየቁ ነው
በጁባ የተበጣጠሰው የጁንታው የሽብር መረብ
ኢትዮጵያ ባለብዙ ጀግኖች ሃገር ናት ኢትዮጵያ ሃገራችን ኢትዮጵያ በሰላም ማስከበር ተግባር ከ1951 በኮርያ የጀመረው የሰላም አምባሳደርነት በሩዋንዳ በኮንጎ በቡርንዲ በላይቤርያ በዳርፉር በአብዬ በሱማሊያ እና ደቡብ ሱዳን ሰላም ላጡ ህዝብ ሰላምን አስፍኖ ለተራበው አጉርሶ ለተጠማው አጠጥቶ ዛሬም በአለም አደባባይ የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ከፍ ብሎ ለሰላም ተመራጭ የሆነ ሃይል የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ነው። ታድያ ዛሬም በቡዙ ሺዎች የሚቆጠር የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በአለም ሰላም ማስከበር ላይ ተሰማርቶ በጀግንነትና በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። ይህንን በከፍታ ማማ ላይ ያለ ሠራዊትን ሊነቀንቁት አስበው በደቡብ ሱዳን ጁባ የሚገኝውን የ13ኛ ሞተራይዝድ ሰላም አስከባሪ ሻለቃን ላይ ደም ለማፋሰስ የሽብር ተግባር ለመፈፀምና የኢትዮጵያ ሃገራችንን ገፅታ ለማበላሸት … [Read more...] about በጁባ የተበጣጠሰው የጁንታው የሽብር መረብ
ቢያንስ 1564 የተጨፈጨፉበት የማይካድራ ግፍ
የምዕራባውያን ሚዲያዎች በማይካድራ የተፈፀመውን የዘር ጭፍጨፋ አስመልክቶ እውነቱን መዘገብ እንደሚገባቸው ጋዜጠኛ ጄፍ ፒርሰን ተናገረ https://www.youtube.com/watch?v=q7mjD3_ucUw … [Read more...] about ቢያንስ 1564 የተጨፈጨፉበት የማይካድራ ግፍ
አሸባሪዎቹ ሸኔ እና ህወሓት መደምሰስ አለባቸው፡- ዶ/ር ዓለሙ
በወሎ ግንባር የተገኙት በሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ዶክተር ዓለሙ ስሜ አሸባሪዎቹ ሸኔ እና ህወሓት ለኢትዮጵያ የማይጠቅሙ በመሆናቸው መደምሰስ አለባቸው ብለዋል። የወያኔ እና ሸኔ ጥምረት ለኦሮሞና ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያላቸውን ንቀት የሚያሳይ ነው ያሉት ዶ/ር ዓለሙ ስሜ ትህነግም ሸኔን በአንድ ላይ መደምሰስ አለባቸውም ነው ያሉት። የሸኔና የህወሓት ጋብቻ አዲስ ሳይሆን ህወሓት መንግሥት ሆኖም ሳለ ኦሮሞን ለማተራመስ ሲፈልግ ሸኔን ይመሩት እንደነበር ነው ያስታወሱት። አሸባሪው ህወሓት በግንባር ጀግንነት እንደሌለው የገለጹት ዶክተር ዓለሙ ለሚያሠራጨው የሐሰት ፕሮፖጋንዳ ጆሮ ሳይሰጥ ህብረተሰቡ እንዲታገል ጥሪ አቅርበዋል። አሸባሪው ህወሓት ወጣቶችን በሀሽሽ እያደነዘዘ እየላከ መሆኑን የገለጹት ዶ/ር ዓለሙ ስሜ ብዙ የአሸባሪው … [Read more...] about አሸባሪዎቹ ሸኔ እና ህወሓት መደምሰስ አለባቸው፡- ዶ/ር ዓለሙ
ሕገ-ወጥ የዶላር መንዛሪዎች ተያዙ፤ ዳያስፖራው እንዳይተባበር ጥሪ ቀረበ
በሀገራችን ላይ የተለያዩ ሴራዎችን ሲያካሂድ የቆየው የአሸባሪው የህወሃት ጁንታ ቡድንና ተላላኪዎቹ ፊት ለፊት ከሚያካሂዱት ሀገር የማፍረስ ሴራ ጎን ለጎን በሀገሪቱ ከፍተኛ የኑሮ ውድነት እንዲፈጠርና ህዝብ በመንግስት ላይ እንዲማረር የተቻላቸውን ሁሉ እያደረጉ መሆናቸው ተደርሶበታል። በዚህ መሰረት የሽብር ቡድኑ ስልጣን ላይ በነበረባቸው አመታት በዘረጋቸው ኔትዎርኮችና ቅጥረኞች አማካኝነት ከአዲስ አበባ ቶጎ ውጫሌን፣ ሞያሌን፣ መተማንና ሌሎች የመውጫ በሮችን በመጠቀም ኮንትሮባንድ ዝውውር ላይ በመሳተፍና ዶላርን በጥቁር ገበያ እየገዛ የዶላር እጥረት እንዲከሰት ከማድረግ ባሻገር በርካታ የጥፋት ተግባራትን ሲያካሄድ የቆየ መሆኑን ቀደም ሲል በህገ-ወጥ ተግባር ላይ ተሰማርተው የተገኙ ስድስት ድርጅቶች ቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው ስለመሆኑ ባስተላለፍነው መረጃ ተደራሽ … [Read more...] about ሕገ-ወጥ የዶላር መንዛሪዎች ተያዙ፤ ዳያስፖራው እንዳይተባበር ጥሪ ቀረበ