• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ባለፉት 24 ሰዓታት የትህነግ የሽብር ቡድን ላይ በተወሰደ እርምጃ ጀብዱ ተፈጽሟል፡- የአማራ ክልል

August 19, 2021 09:45 am by Editor Leave a Comment

አሸባሪው የትህነግ ቡድን በኃይል በወረራቸው አካባቢዎች ላይ በተሰወሰደ ወታደራዊ እርምጃ ታላላቅ ጀብዱዎች መፈጸማቸውን የአማራ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ገለፁ፡፡

ዋና ዳይሬክተሩ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ባለፉት 24 ሰዓታት በወልድያና አካባቢው፣ ጋይትና አካባቢው፣ ዛሬማና አካባቢው፣ ሰቆጣና አካባቢው፣ ጋሸናና አካባቢው በትህነግ የሽብር ቡድን ላይ በተወሰደ ወታደራዊ እርምጃ ታላላቅ ጀብዱዎች መፈጸማቸውን ተናግረዋል፡፡

በዚህም የሽብር ቡድኑ የደረሰበት ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ ከባድ መሆኑንም ነው አቶ ሙሉነህ የገለፁት፡፡

ይህ ሆኖ ሳለ የማህበረሰብ አንቂዎች በማወቅም ይሁን ባለማወቅ በማህበራዊ ተስስር ገፆች የትህነግ የሽብር ቡድንን ለመደምሰስ የሚደረገውን ጥረት የሚያደናቅፉ መረጃዎችን ከማሰራጨት እንዲታቀቡ አቶ ግዛቸው አሳስበዋል፡፡

በጦርነቱ ምክንያት ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ዜጎች ተፈናቅለዋል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ ለዜጎች ሰብዓዊ እርዳታ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

አሁን ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ እንደመልካም አጋጣሚ በመጠቀም ኢኮኖሚያዊ ምክንያት ሳይኖር የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ ነጋዴዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ዋና ዳይሬክተሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በሌላ በኩል አሸባሪው ትህነግ ወረራ በፈፀመባቸው የአማራ ክልል አካባቢዎች እያደረሰ ካለው ሰብዓዊና ቁሳዊ ጥፋት ባሻገር የአርሶ አደሩን የግብርና ምርት እንቅስቃሴ እያደናቀፈ መሆኑን የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡

በሰሜን ወሎ፣ ዋግ ኽምራ፣ ሰሜን እና ምእራብ ጎንደር ዞኖች በአሸባሪው ትህነግ ወረራ ምክንያት በዚህ ክረምት ለማከናወን በታሰበው ልክ የእርሻ ስራን መፈፀም እንዳልተቻለ ቢሮው ገልጿል፡፡

በአማራ ክልል በዚህ የመኽር ወቅት 4.5 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ የነበረ ቢሆንም እስከአሁን በዘር የተሸፈነው 3.8 ሚሊዮን ሄክታር ብቻ መሆኑን የቢሮው ኃላፊ ዶክተር መለስ መኮንን ገልፀዋል፡፡

ይህም በአሸባሪው የትህነግ ቡድን የወረራ እንቅስቃሴ ምክንያት መሆኑን ነው ኃላፊው የገለጹት፡፡

በሌላ በኩል በ12 ዞኖችና 112 ወረዳዎች ከ10 ሺህ ሄክታር በላይ የዘማች አርሶ አደሮች ማሳ በህብረተሰቡ ትብብር በዘር እንዲሸፈን ተደርጓል ብለዋል፡፡

ከ5ሺ ሄክታር መሬት በላይ የዘማች እርስ አደሮች ሰብል የማረም ስራ መከናወኑንም አክለዋል፡፡ የግብርና ስራው ለተራዘመ ጊዜ ተስተጓጉሎ እንዳይቆይ አርሶ አደሩ በተባበረ ክንዱ አሸባሪው ትህነግን ለመደምሰስ እያደረገው ያለውን ተጋድሎ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪ ቀርቧል፡፡ ©አማራ ኮሚዩኒኬሽን እና ኢብኮ

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News, Politics, Slider Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule