• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ባለፉት 24 ሰዓታት የትህነግ የሽብር ቡድን ላይ በተወሰደ እርምጃ ጀብዱ ተፈጽሟል፡- የአማራ ክልል

August 19, 2021 09:45 am by Editor Leave a Comment

አሸባሪው የትህነግ ቡድን በኃይል በወረራቸው አካባቢዎች ላይ በተሰወሰደ ወታደራዊ እርምጃ ታላላቅ ጀብዱዎች መፈጸማቸውን የአማራ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ገለፁ፡፡

ዋና ዳይሬክተሩ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ባለፉት 24 ሰዓታት በወልድያና አካባቢው፣ ጋይትና አካባቢው፣ ዛሬማና አካባቢው፣ ሰቆጣና አካባቢው፣ ጋሸናና አካባቢው በትህነግ የሽብር ቡድን ላይ በተወሰደ ወታደራዊ እርምጃ ታላላቅ ጀብዱዎች መፈጸማቸውን ተናግረዋል፡፡

በዚህም የሽብር ቡድኑ የደረሰበት ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ ከባድ መሆኑንም ነው አቶ ሙሉነህ የገለፁት፡፡

ይህ ሆኖ ሳለ የማህበረሰብ አንቂዎች በማወቅም ይሁን ባለማወቅ በማህበራዊ ተስስር ገፆች የትህነግ የሽብር ቡድንን ለመደምሰስ የሚደረገውን ጥረት የሚያደናቅፉ መረጃዎችን ከማሰራጨት እንዲታቀቡ አቶ ግዛቸው አሳስበዋል፡፡

በጦርነቱ ምክንያት ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ዜጎች ተፈናቅለዋል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ ለዜጎች ሰብዓዊ እርዳታ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

አሁን ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ እንደመልካም አጋጣሚ በመጠቀም ኢኮኖሚያዊ ምክንያት ሳይኖር የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ ነጋዴዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ዋና ዳይሬክተሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በሌላ በኩል አሸባሪው ትህነግ ወረራ በፈፀመባቸው የአማራ ክልል አካባቢዎች እያደረሰ ካለው ሰብዓዊና ቁሳዊ ጥፋት ባሻገር የአርሶ አደሩን የግብርና ምርት እንቅስቃሴ እያደናቀፈ መሆኑን የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡

በሰሜን ወሎ፣ ዋግ ኽምራ፣ ሰሜን እና ምእራብ ጎንደር ዞኖች በአሸባሪው ትህነግ ወረራ ምክንያት በዚህ ክረምት ለማከናወን በታሰበው ልክ የእርሻ ስራን መፈፀም እንዳልተቻለ ቢሮው ገልጿል፡፡

በአማራ ክልል በዚህ የመኽር ወቅት 4.5 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ የነበረ ቢሆንም እስከአሁን በዘር የተሸፈነው 3.8 ሚሊዮን ሄክታር ብቻ መሆኑን የቢሮው ኃላፊ ዶክተር መለስ መኮንን ገልፀዋል፡፡

ይህም በአሸባሪው የትህነግ ቡድን የወረራ እንቅስቃሴ ምክንያት መሆኑን ነው ኃላፊው የገለጹት፡፡

በሌላ በኩል በ12 ዞኖችና 112 ወረዳዎች ከ10 ሺህ ሄክታር በላይ የዘማች አርሶ አደሮች ማሳ በህብረተሰቡ ትብብር በዘር እንዲሸፈን ተደርጓል ብለዋል፡፡

ከ5ሺ ሄክታር መሬት በላይ የዘማች እርስ አደሮች ሰብል የማረም ስራ መከናወኑንም አክለዋል፡፡ የግብርና ስራው ለተራዘመ ጊዜ ተስተጓጉሎ እንዳይቆይ አርሶ አደሩ በተባበረ ክንዱ አሸባሪው ትህነግን ለመደምሰስ እያደረገው ያለውን ተጋድሎ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪ ቀርቧል፡፡ ©አማራ ኮሚዩኒኬሽን እና ኢብኮ

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Left Column, News, Politics, Slider Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • ሰብዓዊ እርዳታ ወደ መቀሌ መግባት መቀጠሉ ተገለጸ May 16, 2022 03:07 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule