• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ባለፉት 24 ሰዓታት የትህነግ የሽብር ቡድን ላይ በተወሰደ እርምጃ ጀብዱ ተፈጽሟል፡- የአማራ ክልል

August 19, 2021 09:45 am by Editor Leave a Comment

አሸባሪው የትህነግ ቡድን በኃይል በወረራቸው አካባቢዎች ላይ በተሰወሰደ ወታደራዊ እርምጃ ታላላቅ ጀብዱዎች መፈጸማቸውን የአማራ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ገለፁ፡፡

ዋና ዳይሬክተሩ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ባለፉት 24 ሰዓታት በወልድያና አካባቢው፣ ጋይትና አካባቢው፣ ዛሬማና አካባቢው፣ ሰቆጣና አካባቢው፣ ጋሸናና አካባቢው በትህነግ የሽብር ቡድን ላይ በተወሰደ ወታደራዊ እርምጃ ታላላቅ ጀብዱዎች መፈጸማቸውን ተናግረዋል፡፡

በዚህም የሽብር ቡድኑ የደረሰበት ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ ከባድ መሆኑንም ነው አቶ ሙሉነህ የገለፁት፡፡

ይህ ሆኖ ሳለ የማህበረሰብ አንቂዎች በማወቅም ይሁን ባለማወቅ በማህበራዊ ተስስር ገፆች የትህነግ የሽብር ቡድንን ለመደምሰስ የሚደረገውን ጥረት የሚያደናቅፉ መረጃዎችን ከማሰራጨት እንዲታቀቡ አቶ ግዛቸው አሳስበዋል፡፡

በጦርነቱ ምክንያት ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ዜጎች ተፈናቅለዋል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ ለዜጎች ሰብዓዊ እርዳታ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

አሁን ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ እንደመልካም አጋጣሚ በመጠቀም ኢኮኖሚያዊ ምክንያት ሳይኖር የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ ነጋዴዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ዋና ዳይሬክተሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በሌላ በኩል አሸባሪው ትህነግ ወረራ በፈፀመባቸው የአማራ ክልል አካባቢዎች እያደረሰ ካለው ሰብዓዊና ቁሳዊ ጥፋት ባሻገር የአርሶ አደሩን የግብርና ምርት እንቅስቃሴ እያደናቀፈ መሆኑን የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡

በሰሜን ወሎ፣ ዋግ ኽምራ፣ ሰሜን እና ምእራብ ጎንደር ዞኖች በአሸባሪው ትህነግ ወረራ ምክንያት በዚህ ክረምት ለማከናወን በታሰበው ልክ የእርሻ ስራን መፈፀም እንዳልተቻለ ቢሮው ገልጿል፡፡

በአማራ ክልል በዚህ የመኽር ወቅት 4.5 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ የነበረ ቢሆንም እስከአሁን በዘር የተሸፈነው 3.8 ሚሊዮን ሄክታር ብቻ መሆኑን የቢሮው ኃላፊ ዶክተር መለስ መኮንን ገልፀዋል፡፡

ይህም በአሸባሪው የትህነግ ቡድን የወረራ እንቅስቃሴ ምክንያት መሆኑን ነው ኃላፊው የገለጹት፡፡

በሌላ በኩል በ12 ዞኖችና 112 ወረዳዎች ከ10 ሺህ ሄክታር በላይ የዘማች አርሶ አደሮች ማሳ በህብረተሰቡ ትብብር በዘር እንዲሸፈን ተደርጓል ብለዋል፡፡

ከ5ሺ ሄክታር መሬት በላይ የዘማች እርስ አደሮች ሰብል የማረም ስራ መከናወኑንም አክለዋል፡፡ የግብርና ስራው ለተራዘመ ጊዜ ተስተጓጉሎ እንዳይቆይ አርሶ አደሩ በተባበረ ክንዱ አሸባሪው ትህነግን ለመደምሰስ እያደረገው ያለውን ተጋድሎ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪ ቀርቧል፡፡ ©አማራ ኮሚዩኒኬሽን እና ኢብኮ

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Left Column, News, Politics, Slider Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule