አቶ አባይ ጸሀዬ በዘመዶቻቸው ስም በርካታ መሬቶች መውስዳቸው፣ ቦሌ ክፍለ ከተማ ውስጥ ባስቀመጡት ሃላፊ አማካይነት በመሬት ንግድ ከፍተኛ ጥቅም ማግኘታቸው፣ ህጋዊ ሰነድና ካርታ ያለው ቁልፍ ቦታ ከባለቤቱ ተነጥቆ ለእርሳቸው ዘመድ መሰጠቱ ሲረጋገጥ ምርመራው እንዲቆም መታዘዙ ታወቀ። በየክልሉ ተመሳሳይ ንቅዘት አለ። በህዝብና በቦሌ ክፍለ ከተማ ሰራተኞች፣ እንዲሁም ለአብነት የተጠቀሱት ንብረታቸው የተወሰደባቸው ሴት ወ/ሮ ጉዳያቸውን የትኛውም ቦታ ሲወስዱ መጀመሪያ ቀጠሮ እንደሚሰጣቸው፣ በቀጠሮዋቸው ቀን ሲሄዱ ምን ምላሽ እንደማያገኙ ጠቅሰው ባቀረቡት አቤቱታ መሰረት የተጀመረው የምርመራ ስራ ይህንን ይመስላል። ቀደም ሲል ተጠሪነቱ ለአቶ መለስ የነበረው የፌደራል ስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን መርማሪዎች አቶ አባይ ጸሃዬን “የመሬት ከበርቴው” የሚል ስም ሰጥተዋቸዋል። ስያሜውም … [Read more...] about “የመሬት ባላባቱ” ሚኒስትር!!
News
ዜና
ህወሓት የደኅንነት ሞተሩን መሪው አደረገ!
ህወሓት የድርጅቱን መሪዎች መምረጡን ይፋ አድርጓል። በዚሁ መሰረት አቶ አባይ ወልዱ ሊቀመንበር፣ ዶ/ር ደብረጽዮን ወልደ ሚካኤል ምክትል አድርጎ ሰይሟል። ምርጫው የተከናወነው መቀሌ ሳይሆን አዲስ አበባ ነበር። ሴፕቴምበር 19 ይፋ የተደረገውን የህወሓት ምርጫ አስመልክቶ ህወሓት መግለጫ አሰራጭቷል። ህወሓት በምርጫው ያልተገመቱና አዲስ አመራር ወደ ሃላፊነት አምጥቷል። እርሳቸውም ዶ/ር ደብረጽዮን ወልደ ሚካኤል ናቸው። በሚኒስትር ማዕረግ የኢንፎርሜሽንና ደህንነት ኤጀንሲ ዳይሬክተርና የኢትዮ ቴሌኮም ቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት ዶ/ር ደብረጽዮን በነባር ታጋዮች ዘንድ እይወደዱም። ደብረጽዮን ወልደ ሚካኤል በደኅንነቱ የሚከናወኑ ከፍተኛ ጉዳዮችን የሚመሩ፣ ከፍተኛ ውሳኔዎችን የሚወስኑ፣ የአገሪቱን የደኅንነት መዋቅር ከቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ጎን ለጎን የሚመሩ መሆናቸውን በቅርብ የሚያውቁ … [Read more...] about ህወሓት የደኅንነት ሞተሩን መሪው አደረገ!
ከ21 ዓመት በኋላ ህወሓት ተነፈሰ!!
የመከላከያውንና የደህንነቱን የስልጣን ርካብ ከቀድሞው ይልቅ ቆንጥጦ ለመያዝ እየተረባረበ ያለው ህወሓት በግልጽ ከሚታየው የፖለቲካ አመራር ወንበሩ ተነሳ። ለ21 ዓመታት የድርጅት፣ የጠ/ሚኒስትርነትና ቁልፍ የስልጣን መደቦችን ተቆጣጥሮ የኖረው ህወሓት ሁለቱን ግዙፍ ወንበሮች ለማስጠበቅ በድርጅትና በጎንዮሽ ትስስር ያካሄደው ዘመቻ አልተሳካለትም። ይህ ዜና እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ አቶ መለስን የሚተካ መሪ መሰየም አለመቻሉን አቶ በረከት ስምኦን ያሳበቁበት ህወሓት በቀጣዩ ምርጫም ወንበሩን እንደማያገኘው አቶ በረከት በግልጽ ተናግረዋል። ኢህአዴግ ቀጣዩን ምርጫ ካሸነፈ ሁለቱ አዲስ ተሿሚዎች በስልጣናቸው እንደሚቀጥሉ በይፋ ተናግረዋል። የኢህአዴግን የአመራር ወንበር ላለማጣት ያደረገው ሙከራ በየድርጅቶቹ በተካሄደ የተናጠል ስብሰባ ተሞክሮ ሊሳካ እንዳልቻለ ጎልጉል ምንጮቹን ጠቅሶ መዘገቡ … [Read more...] about ከ21 ዓመት በኋላ ህወሓት ተነፈሰ!!
ኢትዮጵያ ወደ ወታደራዊ አስተዳደር?!
ሰሞኑን ይፋ የተደረገው የከፍተኛ ወታደራዊ ሹመት ህወሓት የፖለቲካ የበላይነቱ ለመመናመኑ ምልክት መሆኑ ተጠቆመ። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የህግ ለውጥ ሳይደረግ በደህንነት ሹሞች የቅርብ ቁጥጥር ስር መዋሉም ተሰማ። የጎልጉል ምንጮች ያነጋገሩዋቸው ክፍሎች መለስ በህይወት እያሉ ሁሉንም ቁልፍ ይዘውት ስለነበር ህወሃት የፖለቲካ የበላይነቱ የተጠበቀና አስተማማኝ ስለነበር የጦር ኃይሉ በፖለቲካው ዘርፍ ቀጥተኛ ተሳታፊ ሲሆን አይታይም ነበር። ኢትዮጵያን ወደ ፍጹም ወታደራዊ አስተዳደር ለማሸጋገር ደፋ ቀና ሲል የጠቅላይ ሚኒስትር መለስን ህልፈት ሲያስተባብል የቆየው ኢህአዴግ፣ በሳምንቱ መጀመሪያ ለሰላሳ አራት ከፍተኛ መኮንኖች የብርጋዲዬር ጄኔራልነት፣ ለሶስት ብርጋዲየር ጄኔራሎች ደግሞ የሜጀር ጄኔራልነት ማዕረግ መስጠቱን ምንጮቹ ያስታውሳሉ። በተለይም ሃያ ሶስቱ ተሿሚ ጄኔራሎች የትግራይ … [Read more...] about ኢትዮጵያ ወደ ወታደራዊ አስተዳደር?!
የመለስ ሞትና የኤርትራ ዝምታ
የቀድሞውን ጠ/ሚኒስትር የአቶ መለስን ሞት አስመልክቶ ሕዝባዊ ግንባር ሓርነት ኤርትራም (ሻዕቢያ) ሆነ መሪው አቶ ኢሳይያስ የሚያስተዳድሩዋቸው መገናኛዎች ዝምታን መምረጣቸው እያነጋገረ መሆኑ ተገለጸ። በአገር ውስጥና በውጪ ለሚኖሩ የተለያዩ ኅብረተሰብ ክፍሎች መጠይቅ በመበተን ባሰባሰብነው መረጃ የኤርትራ ዝምታ የአቶ መለሰንና የኤርትራን ቁርኝት አደባባይ ያወጣ እንደሆነ የሚስማሙት ቁጥር አብላጫ ነው። “አቶ መለስ ቀድሞውንም ለኤርትራና ለኤርትራ ተወላጆች ሽንጣቸውን ገትረው ሲከራከሩ የነበሩ መሪ መሆናቸውን ለምንረዳ የሻእቢያ ዝምታ አያስገርምም” የሚሉት አስተያየት ሰጪ “አቶ መለስ ለኤርትራ ያሳዩትን ከልብ የመነጨ ፍቅርና የተቆርቋሪነት ስሜት ለሚመሩት ህዝብና አገር አሳይተው አያውቁም። የኤርትራ ተወላጆችም ሆኑ ፕሬዚዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ ሃዘን ቢቀመጡ ከኢትዮጵያዊያን በላይ … [Read more...] about የመለስ ሞትና የኤርትራ ዝምታ
“ሕዝብን የምጨቁን ሰው አይደለሁም”
ተጠባባቂ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ኢትዮጵያን እንዲያስተዳድሩ ከተሰየሙበት ቀን ጀምሮ መነጋገሪያ ሆነዋል። “ራሳቸውን ችለው መስራት አይችሉም” ከሚለው ድፍን አስተያየት ጀምሮ አቶ ኃይለማርያምን “ለወቅቱ አስፈላጊና ብቃት ያላቸው” በማለት የሚመሰክሩላቸው አልታጡም። እነዚህ ክፍሎች እንደሚሉት አቶ ኃይለማርያም “ህዝብን የምጨቁን ሰው አይደለሁም” በማለት በሚያመልኩት አምላካቸውና በእግዚአብሔር ህዝብ ፊት አስቀድመው ቃል መግባታቸውንና የተፈጥሮ ባህሪያቸውን በማመሳከር ይከራከራሉ። በሌላ ወገን ደግሞ “አቶ ኃይለማርያም የቀድሞው ስብዕናቸው ፈርሶ በአዲስ ተሰርቷል። አቶ መለስ በአብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ፍልስፍና አጥምቀዋቸዋል። ከእርሳቸው ምንም አይጠበቅም” በሚል የሚያጣጥሏቸውም አሉ። አቶ ኃይለማርያምን ያሳደገችው የኢትዮጵያ ሐዋሪያት ቤተ ክርስቲያን አባሎች ከዛሬ ሶስት ዓመት … [Read more...] about “ሕዝብን የምጨቁን ሰው አይደለሁም”
ህወሓት ለዳግም ሥልጣን እየሮጠ ነው
ሟቹን ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊን ለመተካት የሚደረገው የውስጥ ለውስጥ ሽኩቻ ኢህአዴግ እንደሚለው “በቀላል ሽግግር” የሚቋጭ እንዳልሆነ የሚጠቁሙ መረጃዎች እየወጡ ነው። መለስን በወኪሏ ወ/ሮ ሱዛን ራይስ አማካይነት በአስከሬን ሽኝቱ ወቅት ያቆለጳጰሰችው አሜሪካ የስልጣን ሽግግሩ ላይ ያላትን የማያወላዳ አቋም ትዕዛዙን ባለመቀበል ከሚመጣው መዘዝ ጋር ማስታወቋም ተሰምቷል። የጎልጉል የአዲስ አበባ ምንጮች ከኢህአዴግ ከፍተኛ ደጋፊዎችና የቅርብ ባለሃብቶች እንዳገኙት ገልጸው በላኩት መረጃ የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲተኩ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር የሆኑትን አቶ ደብረጽዮን ገ/ሚካኤልን በቅድሚያ እጩነት መያዛቸውን አመልክተዋል። መረጃ አቀባዮቻችን ደብረጽዮን ለሹመቱ የታጩበትን ምክንያት ሲያስረዱ መነሻ ያደረጉት በህወሓት ክፍፍል ወቅት የነበራቸውን … [Read more...] about ህወሓት ለዳግም ሥልጣን እየሮጠ ነው