ተጠባባቂ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ኢትዮጵያን እንዲያስተዳድሩ ከተሰየሙበት ቀን ጀምሮ መነጋገሪያ ሆነዋል። “ራሳቸውን ችለው መስራት አይችሉም” ከሚለው ድፍን አስተያየት ጀምሮ አቶ ኃይለማርያምን “ለወቅቱ አስፈላጊና ብቃት ያላቸው” በማለት የሚመሰክሩላቸው አልታጡም። እነዚህ ክፍሎች እንደሚሉት አቶ ኃይለማርያም “ህዝብን የምጨቁን ሰው አይደለሁም” በማለት በሚያመልኩት አምላካቸውና በእግዚአብሔር ህዝብ ፊት አስቀድመው ቃል መግባታቸውንና የተፈጥሮ ባህሪያቸውን በማመሳከር ይከራከራሉ። በሌላ ወገን ደግሞ “አቶ ኃይለማርያም የቀድሞው ስብዕናቸው ፈርሶ በአዲስ ተሰርቷል። አቶ መለስ በአብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ፍልስፍና አጥምቀዋቸዋል። ከእርሳቸው ምንም አይጠበቅም” በሚል የሚያጣጥሏቸውም አሉ። አቶ ኃይለማርያምን ያሳደገችው የኢትዮጵያ ሐዋሪያት ቤተ ክርስቲያን አባሎች ከዛሬ ሶስት ዓመት … [Read more...] about “ሕዝብን የምጨቁን ሰው አይደለሁም”
News
ዜና
ህወሓት ለዳግም ሥልጣን እየሮጠ ነው
ሟቹን ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊን ለመተካት የሚደረገው የውስጥ ለውስጥ ሽኩቻ ኢህአዴግ እንደሚለው “በቀላል ሽግግር” የሚቋጭ እንዳልሆነ የሚጠቁሙ መረጃዎች እየወጡ ነው። መለስን በወኪሏ ወ/ሮ ሱዛን ራይስ አማካይነት በአስከሬን ሽኝቱ ወቅት ያቆለጳጰሰችው አሜሪካ የስልጣን ሽግግሩ ላይ ያላትን የማያወላዳ አቋም ትዕዛዙን ባለመቀበል ከሚመጣው መዘዝ ጋር ማስታወቋም ተሰምቷል። የጎልጉል የአዲስ አበባ ምንጮች ከኢህአዴግ ከፍተኛ ደጋፊዎችና የቅርብ ባለሃብቶች እንዳገኙት ገልጸው በላኩት መረጃ የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲተኩ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር የሆኑትን አቶ ደብረጽዮን ገ/ሚካኤልን በቅድሚያ እጩነት መያዛቸውን አመልክተዋል። መረጃ አቀባዮቻችን ደብረጽዮን ለሹመቱ የታጩበትን ምክንያት ሲያስረዱ መነሻ ያደረጉት በህወሓት ክፍፍል ወቅት የነበራቸውን … [Read more...] about ህወሓት ለዳግም ሥልጣን እየሮጠ ነው


