• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኦባንግ ለሃይለማርያም በግል ደብዳቤ ላኩ!

October 1, 2012 09:54 am by Editor 2 Comments

ለኢትዮጵያ የሚያስፈልገው እውነተኛ “ትራንስፎርሜሽን” ከሁከት ይልቅ ውይይት፣ ከጥላቻ ይልቅ ፍቅር፣ ከብቀላ ይልቅ ይቅርታ መሆኑን በማስገንዘብ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ለአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ በግል ደብዳቤ መላኩን አስታወቀ፡፡

ንቅናቄው በደብዳቤው መልካም ተግባር በመፈጸም በትውልድ ሁሉ “ታላቁና ደጉ መሪ” እንዲባሉ ምኞቱን ገልጿል። ንቅናቄው ለጻፈላቸው ደብዳቤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ መልስ ይሰጣሉ የሚል ሙሉ እምነት እንዳለው ለጎልጉል በእርግጠኝነት ተናግሯል።

ኢትዮጵያ የሁሉም አገር እንደሆነች በማስታወቅ በአቶ ኦባንግ ሜቶ የአኢጋን ዋና ዳይሬክተር ፊርማ የተላከው ደብዳቤ አቶ መለስ በተደጋጋሚ ተመሳሳይ ጥሪ ሲቀርብላቸው ባለመቀበል ለህዝብ መንገድ ንቀት ሲያሳዩ ማለፋቸውን ያስታውሳል። የአንድ ጎሣ፣ ብሔር፣ ቡድን፣ ሃይማኖት፣ ድርጅት፣ ፓርቲ፣ ብቻውን መግነን እንደሌለበት የተቆመው አኢጋን “ኢትዮጵያውያን ከፈጣሪ የተሰጣቸውን መብት እንደገና ይጎናጸፉና ይለማመዱ ዘንድ እርስዎ የሚወስዷቸው ደፋር እርምጃዎችና ቀልጣፋ አመራሮች ወሳኝነት አላቸው” ሲል አቶ ሃይለማርያምን አደራ ይላቸዋል።

“በአሁኑ ጊዜ እርስዎ የአገር መሪ ሆነዋል፤ ይህም ማለት እርስዎ መሪ የሆኑት ለወከልዎት ፓርቲ/ግንባር (ኢህአዴግ/ደኢህዴን/ህወሓት…) ወይም ከእርስዎ ጋር ለሚስማሙት ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ ለኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲሁም ከእርስዎም ሆነ ከድርጅትዎ ጋር ለማይስማሙ ኢትዮጵያውያን በሙሉ …” መሆኑን በማስገንዘብ አቶ ሃይለማርያም ሁሉንም ያካተተ እርቅ እንዲወርድ ቅድሚያ ሰጥተው እንዲሰሩ ጥሪ ያቀረበው አኢጋን፤ ቀናነት በእጅጉ አስፈላጊ መሆኑን አስምሮበታል።

“አዲሲቷ ኢትዮጵያ” እንድትመሰረት የቀደመችው ኢትዮጵያ መታደስ እንደሚኖርባት፣ ይህም ተሃድሶ እኩልነትን፣ ሰላምን፣ ከሁሉ በላይ ደግሞ ዕርቅን መሠረት በማድረግ “ከጎሣ ይልቅ ሰብዓዊነትን በማስቀደም” እንደሚገባው፣ የገለጸው ደብዳቤ ሲቀጥል “ሰብአዊነትን ማስቀደም በቀደመውም ይሁን በአሁኑ እርሳቸው በሚመሩት የኢህአዴግ አገዛዝ ሥር ለሚገኙት መብታቸው ለተነፈገ ኢትዮጵያውያን እንዲሁም እርስዎንም ጨምሮ ለእያንዳንዱ የደኢህዴን፣ የኦህዴድ፣ የህወሓት፣ የብአዴን … ኢህአዴግ አባላትም ጭምር የሚጠቅምና ዘላቂ መፍትሔ የሚያመጣ የኢትዮጵያ ፈውስ ነው። በዚህ መንፈስ የምትመሰረተው አዲሲቷ ኢትዮጵያ ዘረኝነት የመከነባትና ከፈጣሪ የተሰጡ መብቶች የተከበሩባት እንደምትሆን እንደ አቶ ሃይለማርያም አይነት መንፈሳዊ ሰው በቀላሉ የሚረዳው እውነት” እንደሆነ አመልክቷል።

“በልጅነቱ ሐኪም የመሆን ሕልም የነበረውና ከወንድሙ ጋር ወደ ትምህርት ቤት በኪሎሜትሮች የሚቆጠር ርቀት በመጓዝ ትምህርቱን የተከታተለው የቦሎሶሬው ወጣት ዛሬ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ይሆናል ብሎ ያሰበና የገመተ ማን ይሆን?” ሲል የጠየቀው ደብዳቤ፤ ከፈጣሪ ዕቅድ ውጪ ይህንን ሊያስብ የሚችል አንዳችም ፍጡር እንደሌለ ይጠቅሳል። በማያያዝም “በእንደዚህ ዓይነት ወቅት ባማረ የአበባ ስፍራ በምትመሰለውና እያንዳንዳችንም አንድ ውብ አበባ በመሆን ትልቁን የኢትዮጵያን እርሻ የምናሳምርባት አገራችን መሪ መሆንዎ እንደ ንግሥት አስቴር ፈጣሪ ለዚህ ጊዜ ለምክንያት ያደረገው ይሆን?” በማለት ፍትህና ርትዕ ለተጠሙ ህዝቦች አቶ ሃይለማርያም መልስ እንዲሆኑ ተማጽኗል።

እስረኞችን በመፍታት፣ የተለየ ሃሳብ ካላቸው ጋር ሁሉ በግንባር በመነጋገር ለኢትዮጵያና ህዝቧ ባለውለታ እንዲሆኑ ጥሪውን አስተላልፏል። “አገር በሰውነት ክፍል ይመሰላል፤ ከሰውነት ክፍል አንዱ ሲጎዳ ሁሉም ይታመማል፤ ሁሉም ይጎዳል፡፡ ይህ በሰውነት ክፍል የመሰልነው የሁላችንም መኖርያና መመኪያ የሆነችው አገራችን ኢትዮጵያ ናት፡፡ በዚህች አገራችን ውስጥ የታመሙ የሰውነት ክፍሎች አሉ፡፡ እነዚህን ክፍሎች በጥቅሉ “አሸባሪ፣ ለሕግ የማይገዙ፣ ባለ ሁለት ባርኔጣ ለባሾች፣ …” ከማለት በፊት ህመማቸው ምን እንደሆነና ለዚህም ህመማቸው ዘላቂ መፍትሔ መፈለግ ተገቢው መንገድ ነው፡፡ ይህንን ሲያደርጉ ፈጣሪ ከእርስዎ ጋር ይሆናል፤ ሕዝብም ከጎንዎ ይቆማል፡፡ እምቢ በማለት ግን የታመመውን ክፍል ከማከም ይልቅ “ማስወገድ ነው፤ እርምጃ መውሰድ ነው” የሚል ግትረኛ መንገድ የሚከተሉ ከሆነ በጥቂቱ የተጎዳው የሰውነት ክፍል አመርቅዞ መላውን ሰውነት ከጥቅም ውጪ ያደርገዋል፤ እርስዎም ለብቻዎ የሚቆሙ ይሆናሉ፡፡ ስለሆነም በአሁኑ ወቅት የደቡብ ክልል ወይም የድርጅትዎ ተወካይ ብቻ ሳይሆኑ የመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ መሪ እንደመሆንዎ ሕዝብን ለማዳመጥ ጊዜ መስጠት” እንደሚሻላቸው የመከረው ደብዳቤ በቀጥታ የተጻፈው በአድራሻ ለራሳቸው እንደሆነ ንቅናቄው አስታውቋል። ንቅናቄው አዲሱ ጠ/ሚኒስትር እንደ አቶ መለስ የእርቅና የሰላምን መንገድ ወደ ጎን ይተዋሉ የሚል እምነት እንደሌለውም ለጎልጉል አስታውቋል። የደብዳቤውን ሙሉ ቃል እዚህ ላይ ይገኛል፡፡

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ ለሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Ta says

    October 3, 2012 03:45 pm at 3:45 pm

    what a wonderful message in deed! I love it and if PM HMD read this article, he will definitely respond to the letter.

    keep on doing good always!

    Reply
  2. Sergute Selassie says

    October 15, 2012 12:53 pm at 12:53 pm

    የእንጀራ እናት።
    የእንጀራ እናት የሚለው ቃል በተለምዶው — እንደ እኔ ቃሉ እራሱ እንጀራ ከመሰለ ዘንከታ፤ ለረሃብ ደራሽ ከሆነው የባህል ማእከል ጋር ተገናኝቶ ድርጊቱ ግን በአመዛኙ የሳጥናኤል መሆኑ ሁልጊዜም የማዝንበት ነው። እኔ እንኳን ዛሬ እንጀራ እናት የሚለውን ያነሳሁት ያቺ ለልጆች ጡት ፍለጋ ማስታገሻ የምተሰጠውን በባዶ አዬር ብቻ የተሞላችውን ጡጦ ማለቴ ነው። ሰው ሰራሿን ፕላስቲክ …። አዎን የጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ ራዕይም ይህው ነው። አንድ ሰዓሊ እሷን ከአፋቸው አስገብቶ ቢስልልኝ እንዴት የልቤን ባደረሰ … ሄሮድስ ጠ/ሚር መለስ ዜናዊ ልባቸውን አስገብተውላቸው ከሄዱት ተዋናዮች አንዱ አዲሱ ጠ/ሚር አቶ ኃይለማርያም ደስአለኝ ናቸው። አማኝነታቸውማ ትናንትም ነበር ደምን እያዬ … አሁንም በእግር ብረት የታሰረውን ሰባዕዊ መብት እዬተሳለቀ …
    ሟቹ ጠ/ሚር በጡረታ የመገለልን ህግ ሲያጸድቁ የደረደሩት ያ … ሁላ ጥቅማጥቅም እራሳቸውን አስበው ነበር። እንደ ታመሙ ስለሚያውቁ። ይህም ብቻ አይደለም እሳቸው ከሥልጣን ሲለቁም ልባቸውን ያሰገቡላቸው ወ/ ሮ አዜብን አስበው ነበር። በጡሩታ እሳቸው ሲገለሉ ከሙሉ ጥቅም ጋር፤ ባለቤታቸውን ደግሞ በቀጣይ ጠ/ሚርነት ድርብ ተጠቃሚ ለመሆን ነበር ህልሙ። እንጂ … ለአቶ ኃይለማርያም አስበው ፤ ዕምነትም ኑሯቸው አይደለም። ያው … ከተጠቀሙ በኋላ እንደ ሌሎቹ … ነበር የታሰበው። ባይሆን ሞት ቀደማቸው እንጂ …
    ለማንኛውም ሰው ያልደረሰበት የሄሮድስ መለስ ዜናዊ ፍልስፍና በሸፍጥ የተቀመመ ነበር። ማንነትን ከውስጥ በስደት መሰንጠቅ። የሚያሰጠጓቸው ሰዎች ሁሉ ማንነታቸው መንታ መንገድ ላይ የተገተሩትን ብቻ ናቸው። ለዚህ ሁለት ናሙና ልስጥ ..
    ካህዲዋ – እትብትን ለማጫነት ለታላቋ ትግራይ ራዕይ የሸለሙት ወ/ሮ አዜብ የትግሬ ዝርያ ፈጽሞ የለባቸውም። ዘረ መሰረታቸው ጎንደር ወልቃይት ልዩ ስሙ የቃብቲያ ተወላጅ ናቸው። ወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ሁመራን ጨምሮ የሥራ፤ የትምህርት የለቅሶ፤ የማህበራዊ ቋንቋው አማርኛ ነው። ትግረኛ ቤት ውስጥ የሚጠቀሙበት ነው። እንዲያውም አማርኛ ቋንቋ ልጆች ተኮላፍተው ሲናገሩት እንኳን የአማርኛ ክብሩ ተናካ ዬልጆች መጫወቻ ሆነ ብለው ይቆጡ ከነበሩት ውስጥ … ጎንደሬ በጋሻው ላይ ታሪካቸው የተጻፈው ጀግና አባ ሻንቆ መለሰ ኃይሉ ይገኙበታል። ለአማረነቱና ትውፊቱ የቀደሙት የተለዬ አክብሮትን ትህትና የነበረው ትውልድ ነበር።
    በሌላ በኩል አሁንም አንድም የወልቃይትና የጠገዴ ሰው ወደ ከተማ ለመኖር ቢያስብ ጎንደር እንጂ ትግራይን ፈጽሞ በህልሙ እንኳን አያስበውም። አብዳችኋል እንደሚሉ ነው የሚደመጡት። ምን ለማለት ነው … የአቶ መለስ ዜናዊ ፍልስፍና ማንነት ያለውን ውስጥ አውጥተው አርቲፊሻል መለስ የሆነ ሰው ሰራሽ ማንነት አስገብተው ይገጥማሉ። ጥሩ የጋራጅ ሰው ነበሩና … ፍልስፍናቸውም ያለ ተቀናቃኝ አቆይቷቸዋል። ይገርማል ሞተው እንኳን እዬጠቡት ነው በደመነፍስ … አገሮቻቸው ….
    ስለዚህ ወ/ሮ አዜብ እንደ ትግሬ መሆን አይችሉም። ልሁን ቢሉም አያምርባቸውም። እነሱም አይቀበሏቸውም፤ አያስጠጓቸውም፤ ተቆርቋሪ ነኝ ለማለት ቢሞክሩ ያድጣቸዋል … ላጥ ያለ ገደል ይጠብቃቸዋል። እንደ አማራ ነኝ ማለትም አይችሉም በሰላም ያረፉትን አጽሞች ሁሉ ትግሬ ነበራችሁ በማለት ያሳወጁ፤ የመቃብር አጽምን የረገጡ፤ በዘር ማጥፍት ወንጀል በክልሉ እዬተፈጸማ አጋፋሪ የነበሩ …ናቸው። ስለምን ማንነታው አልነበርም ተስዷል … ሁለት ያጣ ጎመን። መጠጊያ ግን ነበር የሄሮድስ ኢትዮጵያን የማጥፍትና የታላቋ ትግራይ ራዕይ … እሱም አፈር ቅሟል። ሃፍረት – ውርዴት – መሸማቀቅ፤ ጥግ አልባነት – ከታሪክ መሰረዝ የወ/ሮዋ ዕጣ ፈንታ ነው … ዘመን ይቅር የማይለው … ስርዛትን ተከናንበው … እንደ አጎነበሱ ይኖራሉ። ቀና ማለት ፈጽሞ አይችሉም። የተሰበረ ቅስም።
    ሁለተኛው አቶ በረከት ስሞኦን ጎንደር ከተማ ሰፈረ አንባጅኔ ከአቶ ገ/ሕይውትና ከወ/ ሮ ብሬ የተፈጠሩ ኤርትራዊ መሆናቸው አደባባይ የዋለ ጉዳይ ነው።። አባታቸው አባ ገ/ሕይወት የህንጻ ሥራ ባለሙያ ነበሩ። እማም ብሬ ደግሞ ሱቅ ነበራቸው። ሁለቱም በሰላም ተስማምተው፤ ተጎራብተው፤ አበልጅነት ተናስተው ይነሩ ነበር። በልጅነት ትውስታዬ ውጪያቸውን በዚህ መልክ አውቀዋለሁ። ውስጣቸውን ግን እንኳንስ እኔ በዛ ዕድሜዬ ወላጆቼም ዬሚያውቁት አይመስለኝም። ሱቃቸው ግን ደንበኛ ነበርኩ። ስላክ ከጨዋ ሰፍር አንባጅኔ እራቅ ቢልም እሄዳለሁ። ስለምን የእማማ ብሬ ምርቃት ከረሚላ ስለ ነበር። ዘይትም ተገዛ ሱካር ያው ድንቡልቡሏ ነጭ የአረቂ ከረሚላ አይቀሬ ነበረች። ለጉንፋንም ትረዳ ነበረች። …
    አሁን ይህን ነጥብ ያነሳሁት ወ/ሮ አዜብ ጎንደሬ ግን የትግሬነት ሰብዕና ተገጠመላቸውና ተገቡ። ጎንደርን ለመጠቅለል የታላቋ ትግራይን ራዕይ ለማሳከት፤ በተሟላ ዕቅድ የተከናወነ ጋብቻ ነበር። አቶ በረከተም ኤርትራዊ ለዛውም የአማራ ሰብዕና ተገጠመላቸው። ሁለቱም የራሳቸው ሰብዕና የሌላቸው ናቸው። አሁን እስኪ እሰቡት በዛ የሥልጣን ቦታ ያን ያህል ውሸት … የአቶ መለስ ዜናዊ ህመም እስከ ህልፍት የሰጡት መግላጫ ውጥንቅጥ አስቡት። የኔ የሚሉት የውስጥ ማንነት ሆነ በራስ የመቆም አቅም የላቸውምና። ተብልቷል፤ ተመልምሏል። ዝም ብለው ቀፏቸውን አቁመው ነበር እኮ ሲጫወቱባቸው የኖሩት። እንዳይደፍሩ ኤርትራዊ ተብለው ይጠረጣራሉ። እንዳይዘልቁ ደግሞ የተነደለና የተንጠለጠለ መሬት ያልያዘ ማንነትን አግብተዋል።
    አቶ መለስ በሥልጣን በነበሩባቸው ዘመናት ሁሉ በዙሪያቸው የነበሩት ሁሉ ስታሥሱት ሃቁ ቁልጭ ብሎ ይታያችኋል። ትክክለኛ ኦሮሞ ያለሆኑትን በቃ የኦሮማ መሪ ያደርጓቸዋል። ማህል ላይ የሚገትር ሰው ሰራሽ ሰብእና ይገጥሙላቸዋል። አቶ አዲሱ ለገሰንም በሚመለከት እጅግ በሚገርም ሁኔታ ነው ውልቅልቃቸውን አውጥተው አማረነትን የገጠሙላቸው። እንጂ አቶ አዲሱ እማ …
    ስለሆነም በረቀቀ ስልትና ዘዴ ማንነቱን ያጣ፤ መንፈሱ የተሰረቀ – ሽብሽብ፤ ያዳጠው – ህሊና ፤ ለመወሰን የተሳነው -ጥገኛና አቅመ ቢስ ማንነት ፤ አገጣጠመውና ልብስ አልበሰው በፕሮቶኮል ቀፎውን ኮፈሰው አኖራቸው። ስለሆነም — ወኔው ሁሉ መቅኖ ቢስ፤ በራስ የመተማመን መንፈሱ ሁሉ ስደተኛ ሆነ። በዚህ ስልት ነው ሞት አስኪወስዳቸው ድረስ በሰብዕና ላይ ልክ እንደ ጥንቸል ሙከራ ሲያድረጉ የቆዩት … . የአቶ መለስ ታሪክ ለእኔ የጨላማ ድርሰት ነው።
    ይህም ማለት አቶ ኃይለማርያም ደስአለኝ የራሳቸው ማንንት ፍርፋሪ የላቸውም። በፍጹም። ያን የእንጀራ እናት የፕላስቲክ ጡጦ እዬጠቡ ሰብእና ያለው ራዕይን ጨርሶ አላሰቡትም። ታውሬያለሁ ። ዓይን የለኝም። ከፊትም ከኋላ ምሩኝ ነው ያሉት። እንደ ሰው እንኳን ለመቆም ከአሁኑ ደክሟቸዋል። መቅኗቸው ከድቷቸዋል። አላዝንም። አቅመ ቢስ ከሆኑ አልችልም በማለት ወያኔንን ማፈረጥ ሲቻል … ይተበሰባሳሉ። … ይሄ ወንድነት የሚሉት ሰብዕናም እኔ እንጃ …
    ያው አቶ መለስ ነው ማንታቸውን ቀብረውት የሄዱት። እርግጠኛ ሆነው፤ ወሳኝ አቋም ይዞ ለመውጣ በእሳቸው ዙሪያ ያለው የማንነት ጉዳይ ፍለስት ይታይበታል። የቲ.ፒ.ኤል.ኤፍ መስራች አባል አለመሆናቸው፤ ይህ በእራሱ ትልቅ ተራራ ነው። ትግሬነትም – የክትንት ነው፤ የጫካ ተመክሮ ሌላው መስፈርት ነው፤ ሁሉም በዬፍርጃቸው ወጥረው፤ መተንፈሻ ነስተው እያፋጠጧቸው ነበር እስካሁን የቆዩት … ለዛውም እየተወዛወዙ … ልዝዝ ብለው ወይን አይነዱ ወይ አያነዱ ዕዳ ነው። ይህም ይቀጥላል።
    አሁን ወደ መነሻዬ … አዎን እኔ ዶ/ ኦባንግ ኢትዮጵያ ነው አምለው አቶ ኦባንግ ሜቶን … የላከው የመልካም ምኞት መልእከት እና ተማእጽኖም ደግግሜ አንብቤዋለሁ። አቶ ኦባንግ ከሚመራው ንቅናቄ የምጠብቀው ስለነበር አልደነቀኝም። ውስጡን ማዬት ይቻላል። የአዲስቱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ፖለቲካዊ አቋም – ፍጹም ለስላሳ ነው። የሚመቻቸውም ወገኖች ግን ይኖራሉ።
    የሆነ ሆኖ መጠዬቁም ቢሆን ንቅናቄው መብቱ ነው። መልስ መጠበቁም መብቱ ነው። እነዚህን እርምጃዎች እኛ ባለን ጽኑዑ አቋም ላይ ሊለውጥ የሚችለው ምንም ነገር የለም። ለአቶ ኃይለማርያም ግን ቢያንስ ለህሊናቸው ይህን መሰሉ ለስላሳ አቀራረብ እረፍት የሚሰጣቸው አይመስለኝም። በተለይ የቃለ ወንጌል ተገዢ ናቸው እንደሚባሉት ከሆኑ። ህሊናቸው ደግሞ ያው መሪና ምርኩዝ ካልተዋሰ ወይንም የፕላስቲኳን ጡጦ ካልተማጠነ። ሌላው ደግሞ ለወያኔ ውጪ ላሉ ደጋፊዎቻቸው ብድርንና እረዳታ ሲያጎርፉላቸው ለኖሩትም ሀገሮችም ከተቃዋሚው ጎራ አንድ ለእናቱ ዬአዲስቱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ መገኘቱ ለዓለም ዓቀፉ ሚዲያ ፍጆታ መልካም ነው።
    አሁን ማንይሙት አማራ ሆኖ ኦሮሞ ነህና ምራ ቢባል … ይሆናል። አይቻልም። አለማቻል የሚለው ቃሉ እራሱ አይገለጽልኝም። እንደ ኦረሞ ደፍሮ አቋም ይዞ መታገል ፤ ለኦረሞ ህዝብ አይችልም። ብዙ ነገር የማያውቃቸው ረቂቅ ተፈጥሮዎች አሉና። በሌላ በኩል አማራ ሲጓዳ ሲዳፋ፣ ሲንግለታ፣ ሲታሰር ደግሞ ሁለመናው በመሆኑ ቢወቀውም አማራ ነኝ ብሎ የውስጥ ስቃዬን ይፋ አድርጎ አይታገልም። ስለምን የእሱ የሆነውን ማንነት ተቀምቶ የእሱ የሆነ መለያ ተነጥቆ ሌላ አርቲፊሻል ሰብዕና ተስክቶለታል። ኢትዮጵያዊነትንማ እርሱት …. የአቶ መለስ የግልቢያ ጨዋታ … ለዘመናት ውስጥን ህምም ላይ ይጥላል። ዕዳው መጠነ ሰፊ ነው … ቁስለት! የህሊና ቁስለት ታውቃለችሁ ለዛውም የመረቀዘ …?
    ለዚህ ሁሉ መካራ ጆሮ እያላቸው የማይሰሙት፤ ዓይን እያላቸው የማያዩት፤ ህሊና እያላቸው የማያስተውሉት የወያኔ ባለስልጣኖች ዬችግር መንስኤ ይህው ነው። ሀገር ለባእድ ከመቸብቸብ ወዲያ ምን ረመጥ ጉድ አለ … ትናንትን የረገጠ፤ ዛሬን የጨፈለቀ፤ ነገ ሳይመጣ ገና … አድረቆ – ያሳረረ … ያኮማተረ … ይህንን በጸጋ ተቀብለው ሲያስተናግዱ ከነበሩ የዳመና ተዋናዩች መፍትሄ – እእ!
    እንደ ማጠቃለያ …….
    የአቶ ኦባንግን ኢትዮጵያ መልእክት በመብት፤ በነፃነት ደረጃ የድርጅቱና የሚሰማውን በመጻፉ ሆነ በመላኩ አልረበሸኝም። እንዲያውም ሰሞኑን በኢሰአት ጋሼ ሙሉጌታ ሉሌ ከአቶ ኤፍሬም ማንዴቦና ከአቶ ፈቃደ ጋር ባደረገው ውይይት አባይን አስመልክቶ አቶ ፈቃደ ላላቸው አዎንታዊ ዕይታ ሳይጨርሱት ሲያቋርጣቸውና የእራሱን አቋም ሲገልጽ ድብን ነው ያልኩት።
    ስለምን ማስጨረስ ያስፈልጋል። ሌላው የተለያዩ ሰዎች በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ልዩነት አውቆ ወጥ ዕይታ ለመፍጠር ምቹ ነበር። ጋሼ ሙሉጌታ ሳያቋርጥ አቶ ፈቃደን አስጨረሶ እሱ እንደ አወያይነቱ እንደ ተክሌ ጫር አድርጎ ወይንም ምንም ሳይተነፍስ ዕድሉን ለአቶ አፍሬም ሰጥቷቸው ቢሆን ኖሮ ….ኖሮ … ፤ አቶ ኤፍሬም የብዙኃኑን ዕይታ የሚወክል ሃሳብ ያመነጩ ነበር ። ባያመነጩ እንኳን ማጠቃለያ ላይ እሱ እልባት ቢሰጥበት መልካም ሆኖ ሳላ — ? አሁን ለምሳሌ የህንድን ግሪን ሪቮሌሽን አቶ ኤፍሬም ያለነሱትና አቶ ፈቃደ ጣልቃ ገብተው በጥልቀት አንስተው ያላሰተዋልናቸውን ነገሮች ሁሉ እንድንፈትሽ የቤት ሥራ ሰጡን …
    ምን ለማለት ነው — ዴሞክራሲ ፅንሰ-ሓሰቡና ተግባሩን መለማመድ አለብን። መማር አለብን። አንድ የጎንደር አባባል አለች „ሲወዱ እስከ ንፍጥ ልጋጉ“ ዴሞክራሲን እንወደዋለን። ስንወደው ግን እስከ ንፍጥ ልጋጉ መሆን አለበት። ሁሉንም መሆን ይኖርበታልና። የማይመቹነንም በአክበሮትና በትእግስት ተከታትሎ ሃስብን በሃስብ፤ ተግባርና በተግባር አታግሎ የነጠረውን መውሰድ። አባዛሁት መስል …. ስለ ትእግስታችሁ አመሰግናለሁ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule