• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ታላቅ ዕድል ነው!”

September 21, 2012 02:02 pm by Editor 4 Comments

ዛሬ አርብ ልክ ከጠዋቱ 3፡38 ላይ 374 የኢህአዴግ ወኪሎችና ኢህአዴግን እንደሚደግፉ በግልጽ የሚናገሩት አንድ በግል ያሸነፉ የፓርላማ አባል የሚገኙበት የተወካዮች ምክር ቤት አጨበጨበ። ጭብጨባውን ተከትሎ ኢቲቪ የቦሎ ሶሬውን ሰው አመላከተ። ከሃያ አንድ ዓመት በኋላ በሟቹ አቶ መለስ የፓርላማ መቀመጫ ላይ የተሰየሙት አቶ ኃይለማርያም ፈገግታ አሳዩ። አስቀድሞ የተነገረው በትረ ሹመት ስርዓቱን አሟላ። አቶ ኃይለማርያም የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር መሆናቸው ታወጀ።

ቀልጠፍ ቀልጠፍ እያደረጉ ስርዓቱን የመሩት አፈ ጉባኤ አባ ዱላ ገመዳ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት የሆኑትን አቶ ተገኔ ጌታነህን ጋበዙ። በሳቸው ትዕዛዝ ኃይለማርያም ቃለ መሃላ ለመፈጸም ቀኝ እጃቸውን አነሱ። ስማቸውን ጠርተው ማሉ።“…ከአገርና ከህዝብ የተጣለብኝን ሃላፊነት በቅንነት፣ በታታሪነት፣ እንዲሁም ህግንና ስርዓትን ለመፈጸም ቃል እገባለሁ” ሲሉ ሲናገሩት ቀላል የሚመስለውን መሃላ በመልካም አስተዳደር፣ በሙስና፣ በድህነት፣ በዴሞክራሲ እጦት፣ በፍትህ ጥማት፣ ቀና መሪ በራበው፣ እስርና ስቃይ ባንገፈገፈው፣ የመሰብሰብና የመናገር መብት በተገፈፈ፣…… ህዝብ አቀረቡ።

3፡38 ላይ ሙሉ ጠ/ሚኒስትር የሆኑት አቶ ኃይለማርያም ከአንድ ደቂቃ በኋላ “ ክቡር ጠ/ሚኒስትር” ተብለው ንግግር እንዲያቀርቡ ተጋበዙ። “የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ህዝቦች” በማለት በጠቅላይ ሚኒስትርነት ሙሉ ማዕረግ ንግግራቸውን የጀመሩት አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ አስራ ስድስት ደቂቃ በፈጀው ዲስኩራቸው ቅድሚያ የወሰዱት ሹመታቸውን “ታላቅ ዕድል” በማለት ነበር።

አቶ መለስን በማሞካሸት የታጀበው የአዲሱ ጠ/ሚኒስትር ንግግር “… የኔ ድርሻ የአቶ መለስን ሌጋሲ/ውርስ/ ሳይበረዝ ማስቀጠል ነው” በማለት ወ/ሮ አዜብ ባለቤታቸውን በመስቀል አደባባይ ሲሸኙ የተናገሩትን ቃል በቃል አጣቅሷል። እያንዳንዱን ዘርፍ በመዳሰስ መልዕክታቸውን ያስተላለፉት አቶ ኃይለማርያም በእርሻና በመስኖ ልማት የአገር ውስጥ ባለሃብቶችን ለመደገፍ ትልቅ ትኩረት እንደሚሰጡ ባሰመሩበት ንግግራቸው በጥንቀቄ ተዛልፈዋል።

ሹመታቸውን “ታላቅ ዕድል ነው” ያሉት አቶ ኃይለማርያም፤ ሙስናን አስመልክቶ ሲናገሩ በከፍተኛ ደረጃ ኪራይ ሰብሳቢነትና የሙስና ወንጀል የሚፈጸምባቸውን ዘርፎች ዘርዝረዋል። የመሬት አስተዳደር፣ የታክስና ቀረጥ አሰባሰብ፣ የመንግስት ግዢ አሰባሰብናና የፍትህ አሰጣጥ ዘርፍን በዋናነት ነቅሰው በመጥራት “በሙስናና በስነ ምግባር ጉድለት የተለከፉ ሰዎችን በአግባቡ መስመር ማስያዝ ይገባል” ሲሉ አሳስበዋል። ህዝብ ያለማቅማማት ተባባሪ እንዲሆንም ጠይቀዋል።

ፖሊስ፣ አቃቤ ህግ፣ ፍርድ ቤቶች፣ ህዝቡን በማርካት ማገልገል እንደሚኖርባቸው ያሳሰቡት አቶ ኃይለማርይም፤ ምርጫ ቦርድን ጨምሮ ከተለያዩ ተቋማትና ህግን አክብረው ከሚሰሩ ካሉዋቸው የተቃዋሚ ፓርቲዋች ጋር አብረው እንደሚሰሩ ቃል ከመግባት ውጪ መንግስታቸው ተቋማዊ ለውጥ ለማድረግ ስለማሰቡ የተነፈሱት ነገር የለም።

በነጻነት እጦት ስለታፈነው የነጻው ፕሬስ በደምሳሳው አብረን እንሰራለን ከማለት ውጪ በበጎም ሆነ በመልካም ጎኑ ምንም ሳይናገሩ አልፈውታል። የመልካም አስተዳደር ችግር ሮሮ እንዳለ በማውሳት ህዝብን በቀናነት ማገልገል እንደሚገባ ያመለከቱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ መንግስት የሃይማኖት ነጻነትን እንደሚያከብርና ጣልቃ እንደማይገባ አውስተው ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።

አቶ መለስን መስለው ባስተላለፉት ማሳሰቢያ በሃይማኖት ስም የሚደረግን ማናቸውም ዓይነት የሽብር ተግባር እንደማይታገሱ በግልጽ አስቀምጠዋል። ተግባሩንም “በቀጥታ ከህገ መንግስት ጋር የሚያላትም ነው” ብለውታል። በማንኛውም ሽብር ነክ ጉዳዮች ላይ መንግስታቸው ህጋዊ ርምጃ እንደሚወስድ ያሳሰቡት አቶ ኃይለማርያም ሽብር ነክ ስላሉዋቸው እንቅስቃሴዎች አላብራሩም። ይልቁኑም ኢትዮጵያን ከማንኛውም አይነት ጥቃት የሚከላከል የመከላከያ ሃይል መገንባቱን በማውሳት “ከህዝባችን ጋር በመሆን ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ሰላማዊና የተረጋጋች አገር መሆኗን አስመስክረን እንቀጥላለን” በማለት የመከላከያ ተቋማት ይበልጥ ሳይንሳዊ የሚሆኑበት አቅጣጫ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው ያስገነዘቡት።

አዲስ ካቢኔ ስለማቋቋማቸው ዝምታን የመረጡት ጠ/ሚ/ሩ “የባንዲራ ፕሮጀክት” በሚል ስያሜ የሚጠራውን የአባይ ግድብ ከተያዘለት እቅድ አስቀድሞ ለመጨረስ ርብርብ እንደሚደረግ ተናግረዋል። ፕሮጀክቱ እንዲቆም ጫና ስለመኖሩና ፕሮጀክቱን ለማስፈጸም ስላጋጠመው የገንዘብ እጥረት ግን ያወሱት ነገር የለም።

የዋጋ ግሽበትን ለማርገብ ከዘንድሮው የምርት ዓመት የተሻለ ምርት እንደሚገኝ በማመልከት መልካም ምኞት ከማስተላለፍ ውጪ ግሽበቱን ለማቃለል በተለይ ስለሚተገበር ጉዳይ ያላብራሩት አቶ ኃይለማርያም በሌላ መልኩ በአገሪቱ ኢንዱስትሪ እንዲስፋፋ ለማድረግና የአገር ውስጥ ባለሃብቶች በእርሻ ስራ እንዲሳተፉ እገዛ እንደሚደረግ አጽንኦት ሰጥተው መናገራቸው በዛሬው ንግግራቸው ውስጥ ታላቁ ቁም ነገር ተብሎላቸል።

የመስኖ እርሻን ስለማስፋፋትና ሰፋፊ እርሳዎች በአገር ተወላጆች እንዲጎለብት ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩ የተናገሩት አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ለውጪ ባለሃብቶች በሳንቲም እየተቸረቸረ ስላለው አገሪቱ ለም መሬት ጉዳይ አቋማቸውን አላሳወቁም። በርካቶችን እያፈናቀለ ያለው የመሬት ወረራ የደም ዋጋ እያስከፈለ ያለ ከመሆኑም በላይ ምርቱ አገር ውስጥ እንዲውል የሚደረግ አለመሆኑ ከፍተኛ ተቃውሞ ሲሰነዘርበት የቆየና አሁን ድረስ መልስ ያላገኘ ጉዳይ ነው።

ጠ/ሚ/ር ኃይለማርያም ደሳለኝ የብአዴን ሊቀመንበርና የኢህአዴግ ምክትል ሊቀመንበር የሆኑትን አቶ ደመቀ መኮንን ለምክትል ጠ/ሚኒስትርነት አቅርበው አሹመዋል። አቶ ደመቀ ልክ እንደ አቶ ኃይለማርያም ቃለ መህላ ፈጽመው ሹመታቸውን አጽንተዋል። በቀጣይ ከሁለት ወር በኋላ ትግራይ የሚካሄደው የኢህአዴግ ጠቅላላ ጉባኤ ተለዋጭ መሪዎችን ካልመረጠ በስተቀር አቶ ኃይለማርያም በአሁኑ ሰዓት የደህኢዴን ሊቀመንበር፣ የኢህአዴግ ሊቀመንበር፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ የጦርሃይሎች ጠቅላይ አዛዥ፣ የሚኒስትሮች ምክርቤት ሰብሳቢና የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን ባለትልቁ ማዕረግ ናቸው። ህወሓት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነቱን ስልጣን ለኦህዴድ በመስጠት የፖለቲካውን ክፍተት ቢሞላው የተሻለ እንደሚሆን አስተያየት እየተሰነዘረ ነው፡፡

(በጎልጉል ሪፖርተር )

የጎልጉል ኤዲቶሪያል ቦርድ ኃይለማርያም ደሳለኝ – እንደ ዳንኤል፤ እንደ አክሊሉ ወይስ እንደ መለስ? በሚል ርዕስ ለአዲሱ ጠ/ሚኒስትር ያስተላለፈውን መልዕክት በርዕሰ አንቀጽ ገጻችን ላይ  ይመልከቱ። በመልዕክታችን “የእኛ ምክር መጀመሪያ እንደራሳቸው እንዲሆኑ፤ ቀጥሎም እንደ ፖለቲከኛ እንደ አክሊሉ እንደ ሃይማኖተኛ ደግሞ እንደ ዳንኤል እንዲሆኑ ነው፡፡ እርሳቸው ግን እንዴት እንደሚሆኑት ዛሬ ጀምረውታል፡፡ ሕዝብ ማስተዋል፤ ታሪክም መመዝገብ ጀምሯል” ብለናል።

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በግለሰብ ስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. micheal says

    September 21, 2012 05:15 pm at 5:15 pm

    sewuchu agendachewu lay wutate teteki tewulede ena addis hasabe yemibale neger ayfelgum megdel maser masadede morale ena tesfa maskorite yeker feker en aybtekrestiya yebandira fekre masetelate hobiyachewu adergewu hzebun tekam metekemiya bemaderg wodefite meketel chebechebawu
    yeketelale wutatenehe 21 setetagel +21 berbahulet kelhun endensu teyte kelchohe mesari kaletetkose lewute mamtate ayechalem yalewu manewu gezen lemitekem sewu and dekiga enkon tekem alate yehen mederge yemtechelewu tekmun selawuke becha sehone kawkute gga seterameden abre setesera becha newu GOD BLS

    Reply
  2. Zienamarqos says

    September 21, 2012 06:50 pm at 6:50 pm

    <<>>:- “ፍየል:ከመድረሷ:ቅጠል:መቀንጠሷ”::”የኔ ድርሻ የአቶ መለስን ሌጋሲ/ውርስ/ ሳይበረዝ ማስቀጠል ነው”::ብለው:የከሃዲዋን:ዓዜን:መስፍንን:ንግግር:ደገሙት:አይደል?::ለኢትዮጵያና:ሕዝቧ:እግዚአብሔር:ይሁናቸው::

    Reply
  3. fikir says

    September 21, 2012 10:30 pm at 10:30 pm

    ፍየል:ከመድረሷ:ቅጠል:መቀንጠሷ

    Reply
  4. Wore says

    September 21, 2012 11:06 pm at 11:06 pm

    ፍየል ከመድረሷ ጫት ቃመች
    ፍየል ከመድረሷ ጫት ቃመች
    ፍየል ከመድረሷ ጫት ቃመች

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule