• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ገበሬው ነጻ እስካልወጣ ችጋር ይቀጥላል”

November 3, 2012 01:21 am by Editor Leave a Comment

“የዜግነትና የሰውነት መሰረታዊ መብቶች በተከበሩ ጊዜ ሌሎች መብቶች ሁሉ ይከበራሉ” የሚል ዋና መርህ ያለው በወጣት አመራሮች የተገነባው ሰማያዊ ፓርቲ ገበሬው ነጻ እስካልወጣ ድረስ ችጋር ከኢትዮጵያ ምድር ሊጠፋ እንደማይችል አሳሰበ። የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃል ጌታነህ በፓርቲያቸው ድረገጽ ላይ ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት፣ ኢህአዴግ ታላቅ ገድል አድርጎ የወሰደውን የጠቅላይ ሚኒስትር ሹመት አስመልክቶ “ላይመለስ የሄደ ሰው ነበር፤ ባዶ ቦታ ነበር። ምክትሉ ተተኩ” ሲሉ የስልጣን ሽግግር አለመካሄዱን ጠቁመዋል። የዛሬ መቶ ዓመት የተደረገውን የስልጣን ስያሜ የተሻለ ነበር ብለዋል።

“የኢትዮጵያ ፖለቲካ ከመሰረቱ መነሳት ያለበት ከግለሰብ መብት ላይ መሆን እንዳለበት እናምናለን” በማለት ለግለሰብ መብት መከበር ያላቸውን ጽኑ እምነት ኢንጂነር ይልቃል ጌታነህ “ሰው ከመብላትና ከመጠጣት ባለፈ በሰውነቱ ሊጠይቃቸውና ሊመልሳቸው የሚገባቸው በርካታ ጉዳዮች” እንዳሉ በተለይ ለወጣቱ ትውልድ ባስተላለፉት መልዕክት ተናገረዋል።

ፓርቲያቸው ከሚያምንባቸው መሰረረታዊ ጉዳዮች መካከል የመሬት ባለቤትነት ዋናው መሆኑንን ያመለከቱት የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንብር “… ገበሬው ከካድሬና ከመንግሥት ጭሰኝነት ነፃ ከሆነ እምቅ አቅሙን አውጥቶ በመጠቀም መሬቱን የመጠበቅና የመንከባከብ፣ የማልማትና በባንክ የማስያዝ፣ እንዲሁም የማውረስ፣ የመሸጥና የመለወጥ መብት ይኖሩታል” የሚል የጸና እምነት እንዳላቸው አስረድተዋል።

ለፌዴራል አወቃቀር ኢትዮጵያ በታሪኳ እንግዳ አለመሆኗን ያመለከቱት ኢንጂነር ይልቃል አሁን እንደሚባለው በጐሣ ከረጢት ውስጥ ያሉ ጎሳዎች ተስማምተው አገሪቷን ገና እንደ አዲስ እየፈጠሯት እንደሆነ የሚያስመስለው አቀራረብ ትልቅ ስህተት እንደሆነ አመልክተዋል። “ታሪክን በመፈልሰፍ አንድ ጐሣና አንድ ጐሣ እንደተዋጉ የሚያስመስለው አቀራረብም በፍፁም የተሳሳተና አውዳሚ ነው፡፡ መንግሥት ከመንግሥት፣ የአካባቢው አገዛዝ ከአካባቢው አገዛዝ ተጣልተው ያውቃሉ እንጂ አንድ ብሔረሰብ ከሌላው ብሔረሰብ ጋር በታሪክ ለዚያውም በታቀደ ሁኔታ ጎሣን መሠረት አድርጎ የተደረገ የፖለቲካ ትግል በአገራችን ውስጥ የለም፡፡ ይሄ ከቅርብ ጊዜ በኋላ በጥራዝ ነጠቅነት ሣር-ቅጠሉ ኮሙኒስት በነበረበት ከ66ቱ አብዮት ጋር ተያይዞ እንደወረደ ስለተቀበልነው የመጣ ነገር እንጂ የአገራችንን እውነተኛ ገፅታ የሚያሳይ አይደለም ብለን እናምናለን” በማለት በብሄር ብሄረሰቦች መፈቃቀድ አዲስ ኢትዮጵያ ስለመገንባቷ አጥብቆ የሚናገረውን የኢህአዴግን ቅስቀሳና ትምህርት ነቀፈዋል።

በተወሳሰበ የሞራል ቀውስ እንዲገባ ስለተደረገው የወጣቱ ክፍል ተጠይቀው “ይሄ ከባድ ጥያቄ ነው። በራሱ በምርጫው ያደረገውም አይደል” ካሉ በኋላ ወጣቱ “… ሽንፈቱ ዘላቂ እንዳይሆን ማድረግ ይኖርበታል፡፡ ወደ አሸናፊነት ለመውጣት ሁልጊዜ ተሸንፌያለሁ በቃ! ብሎ አለመቅረት አንዱ ወሳኝ የመፍትሄ ጉዞ ነው፡፡ ከዛ ባለፈ ደግሞ የህይወት መርህ መመዘኛውን ወይም የሞራል እሴት መሠረቱን /Value-Judgment/ መቀየር ነው፡፡ ሰው አካል አለው፣ አእምሮ አለው፣ መንፈስ አለው፡፡ ለአካሉ ነው የሚመገበው፡፡ ይህ የእንስሳነት ባህሪያችን ነው፡፡ እኛን ከእንስሳት የለየን ሰውነታችን በሞራል መመዘኛ ስለሌሎች ማሰብ መቻላችን ነው፡፡ ይህም ነው የሰውነት ልዩ ባህሪያችን፡፡ ስለዚህ ስለሌሎች ማሰብ፣ ኢ-ፍትሃዊነትን አለመቀበል፣ አለመስረቅ የሞራል መርሆዎቻችንና የሰውነት መገለጫዎቻችን ናቸው፡፡ ሰው ስንባል አምላክ ሲፈጥረን ይሄ አብሮ የተሰጠን ነገር ነው፡፡ በመሆኑም አምላክ የሰጠኝን ሰውነቴን አላዋርደውም ይበል ወጣቱ! ስጋዬ ብቻውን አልተፈጠረም። አካልም፣ አእምሮም፣ መንፈስም አንድ ላይ ያለኝ ነኝ ሊል ይገባዋል፡፡ ስለዚህ የአእምሮዬን የመንፈሴንና የሰውነቴን ባህርይ ትቼ በእንስሳነቴ ብቻ አልኖርም ብሎ ቆራጥ አቋም መውሰድ ይኖርበታል፡፡ ያ በሆነ ጊዜ ከውድቀታችንም ለመቃናት ራሳችንንም ተጠያቂ ለማድረግ ዕድል ይሰጠናል” ብለዋል ሙሉው ቃለ ምልልስ እዚህ ላይ ይገኛል።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule