• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ገበሬው ነጻ እስካልወጣ ችጋር ይቀጥላል”

November 3, 2012 01:21 am by Editor Leave a Comment

“የዜግነትና የሰውነት መሰረታዊ መብቶች በተከበሩ ጊዜ ሌሎች መብቶች ሁሉ ይከበራሉ” የሚል ዋና መርህ ያለው በወጣት አመራሮች የተገነባው ሰማያዊ ፓርቲ ገበሬው ነጻ እስካልወጣ ድረስ ችጋር ከኢትዮጵያ ምድር ሊጠፋ እንደማይችል አሳሰበ። የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃል ጌታነህ በፓርቲያቸው ድረገጽ ላይ ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት፣ ኢህአዴግ ታላቅ ገድል አድርጎ የወሰደውን የጠቅላይ ሚኒስትር ሹመት አስመልክቶ “ላይመለስ የሄደ ሰው ነበር፤ ባዶ ቦታ ነበር። ምክትሉ ተተኩ” ሲሉ የስልጣን ሽግግር አለመካሄዱን ጠቁመዋል። የዛሬ መቶ ዓመት የተደረገውን የስልጣን ስያሜ የተሻለ ነበር ብለዋል።

“የኢትዮጵያ ፖለቲካ ከመሰረቱ መነሳት ያለበት ከግለሰብ መብት ላይ መሆን እንዳለበት እናምናለን” በማለት ለግለሰብ መብት መከበር ያላቸውን ጽኑ እምነት ኢንጂነር ይልቃል ጌታነህ “ሰው ከመብላትና ከመጠጣት ባለፈ በሰውነቱ ሊጠይቃቸውና ሊመልሳቸው የሚገባቸው በርካታ ጉዳዮች” እንዳሉ በተለይ ለወጣቱ ትውልድ ባስተላለፉት መልዕክት ተናገረዋል።

ፓርቲያቸው ከሚያምንባቸው መሰረረታዊ ጉዳዮች መካከል የመሬት ባለቤትነት ዋናው መሆኑንን ያመለከቱት የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንብር “… ገበሬው ከካድሬና ከመንግሥት ጭሰኝነት ነፃ ከሆነ እምቅ አቅሙን አውጥቶ በመጠቀም መሬቱን የመጠበቅና የመንከባከብ፣ የማልማትና በባንክ የማስያዝ፣ እንዲሁም የማውረስ፣ የመሸጥና የመለወጥ መብት ይኖሩታል” የሚል የጸና እምነት እንዳላቸው አስረድተዋል።

ለፌዴራል አወቃቀር ኢትዮጵያ በታሪኳ እንግዳ አለመሆኗን ያመለከቱት ኢንጂነር ይልቃል አሁን እንደሚባለው በጐሣ ከረጢት ውስጥ ያሉ ጎሳዎች ተስማምተው አገሪቷን ገና እንደ አዲስ እየፈጠሯት እንደሆነ የሚያስመስለው አቀራረብ ትልቅ ስህተት እንደሆነ አመልክተዋል። “ታሪክን በመፈልሰፍ አንድ ጐሣና አንድ ጐሣ እንደተዋጉ የሚያስመስለው አቀራረብም በፍፁም የተሳሳተና አውዳሚ ነው፡፡ መንግሥት ከመንግሥት፣ የአካባቢው አገዛዝ ከአካባቢው አገዛዝ ተጣልተው ያውቃሉ እንጂ አንድ ብሔረሰብ ከሌላው ብሔረሰብ ጋር በታሪክ ለዚያውም በታቀደ ሁኔታ ጎሣን መሠረት አድርጎ የተደረገ የፖለቲካ ትግል በአገራችን ውስጥ የለም፡፡ ይሄ ከቅርብ ጊዜ በኋላ በጥራዝ ነጠቅነት ሣር-ቅጠሉ ኮሙኒስት በነበረበት ከ66ቱ አብዮት ጋር ተያይዞ እንደወረደ ስለተቀበልነው የመጣ ነገር እንጂ የአገራችንን እውነተኛ ገፅታ የሚያሳይ አይደለም ብለን እናምናለን” በማለት በብሄር ብሄረሰቦች መፈቃቀድ አዲስ ኢትዮጵያ ስለመገንባቷ አጥብቆ የሚናገረውን የኢህአዴግን ቅስቀሳና ትምህርት ነቀፈዋል።

በተወሳሰበ የሞራል ቀውስ እንዲገባ ስለተደረገው የወጣቱ ክፍል ተጠይቀው “ይሄ ከባድ ጥያቄ ነው። በራሱ በምርጫው ያደረገውም አይደል” ካሉ በኋላ ወጣቱ “… ሽንፈቱ ዘላቂ እንዳይሆን ማድረግ ይኖርበታል፡፡ ወደ አሸናፊነት ለመውጣት ሁልጊዜ ተሸንፌያለሁ በቃ! ብሎ አለመቅረት አንዱ ወሳኝ የመፍትሄ ጉዞ ነው፡፡ ከዛ ባለፈ ደግሞ የህይወት መርህ መመዘኛውን ወይም የሞራል እሴት መሠረቱን /Value-Judgment/ መቀየር ነው፡፡ ሰው አካል አለው፣ አእምሮ አለው፣ መንፈስ አለው፡፡ ለአካሉ ነው የሚመገበው፡፡ ይህ የእንስሳነት ባህሪያችን ነው፡፡ እኛን ከእንስሳት የለየን ሰውነታችን በሞራል መመዘኛ ስለሌሎች ማሰብ መቻላችን ነው፡፡ ይህም ነው የሰውነት ልዩ ባህሪያችን፡፡ ስለዚህ ስለሌሎች ማሰብ፣ ኢ-ፍትሃዊነትን አለመቀበል፣ አለመስረቅ የሞራል መርሆዎቻችንና የሰውነት መገለጫዎቻችን ናቸው፡፡ ሰው ስንባል አምላክ ሲፈጥረን ይሄ አብሮ የተሰጠን ነገር ነው፡፡ በመሆኑም አምላክ የሰጠኝን ሰውነቴን አላዋርደውም ይበል ወጣቱ! ስጋዬ ብቻውን አልተፈጠረም። አካልም፣ አእምሮም፣ መንፈስም አንድ ላይ ያለኝ ነኝ ሊል ይገባዋል፡፡ ስለዚህ የአእምሮዬን የመንፈሴንና የሰውነቴን ባህርይ ትቼ በእንስሳነቴ ብቻ አልኖርም ብሎ ቆራጥ አቋም መውሰድ ይኖርበታል፡፡ ያ በሆነ ጊዜ ከውድቀታችንም ለመቃናት ራሳችንንም ተጠያቂ ለማድረግ ዕድል ይሰጠናል” ብለዋል ሙሉው ቃለ ምልልስ እዚህ ላይ ይገኛል።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule