እግሬ ተሰብሯል፣ ሆዴን አሞኛል፣ ቸግር ገጥሞኛል ማለት የተለመደ ነው።ጥርስ የለኝም፣ የአፌ ጠረን ተቀይሯል … ማለት ግን አይታሰብም። ምክንያቱን የጥርስ ችግር የስነልቦናም ጉዳይ ነውና። እናም ከጥርስ ጋር በተያያዝ የስነ ልቦናቸው የተጎዳ እና ሲናገሩና ሲስቁ አፋቸውን የሚሸፍኑ ሰዎችን በመርዳት ፈገግ ሲሉ ማየትና የተጫናቸውን የሃፈረት መጋረጃ መግፈፍ ከምንም በላይ አኩሪ ተግባር ነው። መንገድ ነው። ጉዞ ነው። የሚፈልጉበት ቦታ ለመድረስ በመንገዱ ላይ መጓዝ ግድ ነው። መንገዱ ሁሉ ደስ የሚያሰኝ አይሆንም። ደስ ባማያሰኝ መንገድ ላይ ሳይራመዱ የሚፈልጉት ቦታ መድረስ የሚታሰብ ነገር አይደለም … ራሄል አክሊሉ የስኬቷን ሚስጢርና የህይወቷን ፍልስፍና የምታስረዳው በዚህ መልኩ ነው። “ሰው” ትላለች ራሄል “ሰው በሃሳቡ ወይም ለመሆን የሚፈልገውን ነገር ሲያቅድ የሚሰማው እርካታና መሆን … [Read more...] about “ሥራዬን ከብር ጋር አላያይዘውም” የጥርስ ሐኪም ራሄል አክሊሉ
Interviews
እናውጋ
“ለኢህአዴግ ነገሮች እየከበዱ ነው” ኦባንግ
"እነሱ (ምዕራባውያን) ገፍተው የገደል አፋፍ ላይ ቢያስቀምጡህ እንኳ ክፉ ቃል አይጠቀሙም። በተግባር ግን ያሳያሉ። በጀት ሲቀንሱ ምልክት ነው። የጦር ካምፓቸውን ሲያነሱ ምልክት ነው። ፊት ሲነሱ ምልክት ነው። ከሶማሌ እንዳትወጣ እያሉ ሲለምኑና ዶላር ሲያፈሱ ኖረው የራስህ ጉዳይ ካሉህ ትልቅ ምልክት ነው። መከርንህ፣ ነገርንህ አሁን የራስህ ጉዳይ ነው፣ ለራስህ እወቅ፣ ሁሉም ነገር ባንተ እጅ ነው ሲሉህ ምልክት ነው። ከዚህም በላይ አሁን ኢትዮጵያ እየሄደች ያለችበት መንገድ ወዴት እንደሚያደርሳት ጠንቅቀው ያውቃሉ። ወያኔዎቹ በዘላቂነት ምስራቅ አፍሪቃ እና አካባቢው ላይ ያላቸውን ፍላጎት የማስጠበቅ አቅማቸው መዛሉን ያውቃሉ። ከውስጥ የተነሳው ችግርና አገዛዙ የገባበት የቀውስ ገደል መጨረሻ ከማንም በላይ ይታያቸዋል። ተወደደም ተጠላም አሁን ነገሮች እየከበዱ ነው። እነሱ እንዳሉት ምርጫው … [Read more...] about “ለኢህአዴግ ነገሮች እየከበዱ ነው” ኦባንግ
“ጠርጥሮ የሚይዝህ፤ የሚመረምርህ፤ ዓቃቤ ሕግ ሆኖ የሚከስህ፤ ዳኛ ሆኖ የሚፈርድብህ፤ ሽማግሌ ሆኖ ይቅርታ ጠይቅ የሚልህ፤ [በሙሉ] ህወሃት ነው” ሃብታሙ አያሌው
ሃብታሙ አያሌው ከአዲስ ድምጽ ጋር ያደረገው ቃለምልልስ … [Read more...] about “ጠርጥሮ የሚይዝህ፤ የሚመረምርህ፤ ዓቃቤ ሕግ ሆኖ የሚከስህ፤ ዳኛ ሆኖ የሚፈርድብህ፤ ሽማግሌ ሆኖ ይቅርታ ጠይቅ የሚልህ፤ [በሙሉ] ህወሃት ነው” ሃብታሙ አያሌው
“ሙዚቃ መምራትን ለዓለም ያስተዋወቀችው ኢትዮጵያ ናት”
ሙዚቃን በተለየ መንገድ በማዋሐድ ሙላቱ አስታጥቄ የሙዚቃ ሳይንቲስት መሆኑን በአምስት አሠርታት የሙዚቃ ጉዞው ውስጥ አስመስክሯል፡፡ የተለያዩ ቅላፄዎችንና ምቶችን ከተለያዩ አፍሪካ አገሮች፣ አሜሪካና አውሮፓ ሙዚቃ በመውሰድና በማጣመር አዲስ የሆነ ሙዚቃንም ለዓለም አበርክቷል፡፡ የኢትዮ ጃዝ ፈጣሪው ሙላቱ አስታጥቄ የሙዚቃ ትምህርቱን ያጠናው በለንደን፣ ኒውዮርክና ቦስተን ከተሞች ሲሆን፣ የራሱን የሆነ የሙዚቃ ስልት ከኢትዮጵያ የሙዚቃ ቅኝቶች ጋር አጣምሮ ኢትዮ ጃዝን ፈጥሯል፡፡ በቀላሉ በዓለም አቀፍ ሙዚቃ አፍቃሪዎች ዘንድ ጆሮ ማግኘት የቻለው ሙላቱ ከመቶ ሺሕ በላይ የሚሆኑ ታዳሚዎችም ኮንሠርቱን ለማየት መሽቀዳደም የተለመደ ሆኗል፡፡ ከሙዚቃ ክህሎቱም በተጨማሪ በጥንታዊ ሙዚቃዎች ላይ ፈር ቀዳጅ የሆኑ ምርምሮችንም በማካሄድ ነው፡፡ የአምስት አሠርታት የሙዚቃ ጉዞውንም በተመለከተ ከሪፖርተሩ … [Read more...] about “ሙዚቃ መምራትን ለዓለም ያስተዋወቀችው ኢትዮጵያ ናት”
“እንተያያለን አስክሬንህ ነው የሚወጣው” የህወሃት አሸባሪዎች
* "በክፉ ጊዜ የከዱን አሉ፤ ለእነሱም ፈጣሪ ልቦና ይስጣቸው" "የመጣሁት ከትግል እንጂ ከሽርሽር አይደለም" ይላሉ ዳንኤል ሺበሺ! የቀድሞው አንድት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ምክትል ኃላፊና የደቡብ ቀጠና ኃላፊ ሆነው ሲያገለግሉ የነበረ ሲሆን ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ክስ ከተመሰረተባቸው በኋላ ላለፉት 22 ወራት በእስር ላይ ቆይተው ባለፈው ማክሰኞ ከሰዓት በኋላ ከእሥር ተፈትተዋል፡፡ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ናፍቆት ዮሴፍ አየር ጤና አካባ በተለምዶ ቻይና ካምፕ በተሰኘው የአቶ ዳንኤል መኖሪያ ቤት ተገኝታ በእስር ቆይታቸው ስላሳለፏቸው ነገሮች፣ ስለወደፊት ሀሳባቸውና ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ ተከታዩን ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ እንዴትና በምን ሁኔታ ነበር የተያዙት? የተያዝኩት ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም በተለምዶ ጀርመን አደባባይ … [Read more...] about “እንተያያለን አስክሬንህ ነው የሚወጣው” የህወሃት አሸባሪዎች
“ትግራይ ወረዳ ውስጥ ያለ የመንግሥት አሰራር በኦሮሚያ ውስጥ … ይገኛል”
* "የአዲስ አበባ መሬት በማለቁ ወደ ኦሮሚያ መሬት እጃቸውን መዘርጋት ጀመሩ" * "ማስተር ፕላኑ መሰሪ ነው" በቀለ ገርባ የአዲስ አበባና የፊንፊኔ ዙሪያ ኦሮሚያ ልዩ ዞን ማስተር ፕላንን በተመለከተ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ያለውን ዝርዝር አቋም በተመለከተ የፓርቲው ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባን አዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ በፅ/ቤታቸው ተገኝቶ አነጋግሯቸዋል፡፡ መንግሥት ማስተር ፕላኑ ከተሞችን በመሰረተ ልማት በማስተሳሰር እድገትን ለማምጣት ከፍተኛ ጥቅም አለው ይላል፡፡ ፓርቲያችሁ ደግሞ ማስተር ፕላኑን አልቀበልም ብሏል፡፡ በምን ምክንያት ነው የማትቀበሉት? እኛ ማስተር ፕላኑን የማንቀበለው በትክክል የህዝቡን የልማት ጥያቄ ለመመለስ የተዘጋጀ ነው የሚል እምነት ስለሌለን ነው፡፡ መንግሥት በዚህ አሳቦ ወደ ኦሮሚያ አጎራባች ከተሞች ዘልቆ እየገባ … [Read more...] about “ትግራይ ወረዳ ውስጥ ያለ የመንግሥት አሰራር በኦሮሚያ ውስጥ … ይገኛል”
“ገበሬው ነፃነት ካላገኘ ችጋር ሁልጊዜ በኢትዮጵያ ይኖራል” ፕሮፌሰር መስፍን
* “ችጋር የሰው ልጅ እንደ ማገዶ እንጨት ተለብልቦ የሚያልቅበት የውርደት ሞት ነው” ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ (Institute of Development Research) ሥር ከ1967 ዓ.ም. ጀምሮ ለ10 ዓመታት ያህል በ102 የኢትዮጵያ አውራጃዎች ላይ ምርምር አድርገው ስለ ድርቅ በእርሳቸው አጠራር (ስለ ችጋር) (Rural vulnerability to famine in Ethiopia 1958-1977) የሚል መጽሐፍ ጽፈዋል። የእንቢልታ ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል በዛሬው እትማችን ለበርካታ ዓመታት በድርቅ ጉዳይ ያካሄዱትን የምርምር ሥራ መሠረት አድርገን በወቅታዊው የአገሪቱ የድርቅ ሁኔታ ላይ ከጽዮን ግርማ ጋር ቆይታ አድርገዋል። (ዓርብ መጋቢት 26 ቀን 2000 ዓ.ም) ድርቅን በሚመለከት በርካታ ጥናቶች አድርገዋል። ለምን ያህል ዓመት ነው በጉዳዩ ዙሪያ … [Read more...] about “ገበሬው ነፃነት ካላገኘ ችጋር ሁልጊዜ በኢትዮጵያ ይኖራል” ፕሮፌሰር መስፍን
“በዓሉ ይመጣል ብዬ አሁንም በር በሩን አያለሁ”
በኢትዮጵያ ሥነ ፅሐፍ ውስጥ ስማቸው ጎልቶ ከሚጠሩት ደራስያን መካከል አንዱ የሆነው ደራሲና ጋዜጠኛ በዓሉ ግርማ "ኦሮማይ" በሚል ርዕስ ባሳተመው መፅሐፉ ሳቢያ መስዋዕትነትን የከፈለ ደራሲ ነው፡፡ በአፃፃፍ ቴክኒኩ፤ በአጫጭር አርፍተ ነገሮቹና በድርሰት መዋቅሩ አዲስ የአፃፃፍ ብልሃትን አምጠቷል ተብሎ የሚታመነው ደራሲ በዓሉ ግርማ የካቲት 24 ቀን 1976 ዓ.ም ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ ከቤቱ እንደወጣ የደረሰበት ያልታወቀ ደራሲ ነው፡፡ የበዓሉ መጨረሻ ከዓመት ዓመት ሲያነጋግርና የቆየና ያውቃሉ የሚባሉ ሰዎችን ምስክርነት እንደሻተ እነሆ 30 ዓመት ሞላው፡፡ ይህኑ መሰረት በማድረግ የሙያ አጋሩ ደራሲና ጋዜጠኛ አበራ ለማ ባለፉት ሁለት ተከታታይ እትሞች "የማይጮሁት በዓሉን የበሉ ጅቦች" የሚል መጣጥፉን በቁም ነገር መፅሔት ላይ አስነብቦናል፡፡ ይህንኑ መነሻ በማድረግ የበዓሉ ግርማን ባለቤት … [Read more...] about “በዓሉ ይመጣል ብዬ አሁንም በር በሩን አያለሁ”
“ጎንደር ቤተ መንግስት ውስጥ ኦሮሚኛ ቋንቋ ይነገር ነበር”
በተለያዩ ድረ-ገፆች በኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ በሚያንሸራሽሩት ሃሳብ ይታወቃሉ፡፡ ስለ ኢትዮጵያኒዝም፣ ስለ ፓንአፍሪካኒዝም እንቅስቃሴዎች የተለያዩ ምልከታዎችና ምክረ ሃሳቦችን በማቅረብ ተሰሚነት ካላቸው ኢትዮጵያዊያን ምሁራን አንዱ ናቸው - ፕ/ር ማሞ ሙጬ፡፡ ሰሞኑን ጐንደር ዩኒቨርሲቲ የተመሰረተበትን 60ኛ አመት በዓል ሲያከብር “Towards Innovative Africa: The Significance of Science, Technology, Engineering and Innovation for Sustainable Development” በሚል ርዕስ ጥናታዊ ፅሁፍ አቅርበዋል፡፡ ፕሮፌሰሩ በአሁን ሰአት በደቡብ አፍሪካ ሊዋኔ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቴክኖሎጂና በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ በማስተማር ላይ ይገኛሉ፡፡ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ ባለፈው ሳምንት በጐንደር … [Read more...] about “ጎንደር ቤተ መንግስት ውስጥ ኦሮሚኛ ቋንቋ ይነገር ነበር”
“የድሮ ስርዓት ናፋቂ”?
ይህ ቃለመጠይቅ ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ ከአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ናፍቆት ተስፋዬ ጋር (19 April, 2014) ካደረጉት ቃለምልልስ ተቀንጭቦ የተወሰደ ነው፡፡ አዲስ አድማስ፤ ባለፉት ተከታታይ ሳምንታት በሬዲዮ ፋና ላይ በነፃው ፕሬስ ዙሪያ ውይይቶች ሲካሄዱ ቆይተዋል፡፡ እርስዎም በውይይቱ ላይ ተሳታፊ ነበሩ፡፡ በውይይቱ ላይ “ዶ/ር ዳኛቸው ስሜታዊ ሆነው ነበር” የሚሉ ወገኖች አሉ፡፡ “የድሮ ስርዓት ናፋቂ” የሚል ትችትም ተሰንዝሮቦታል፡፡ የእርስዎ ምላሽ ምንድን ነው? ዶ/ር ዳኛቸው፤ የስሜታዊነቱን ነገር ያመጡት እንኳን እነሱ ናቸው፡፡ ስድብና ዘለፋውን በመጀመር እነሱ ይቀድማሉ፡፡ “የድሮ ስርዓት ናፋቂ” ለሚለው በእውነቱ በናፍቆት ደረጃ ፍትህ ናፋቂ ነኝ፡፡ ዴሞክራሲና የህዝባችንን ነፃነት ናፋቂ ነኝ፡፡ የዱሮ ሥርዓት ናፋቂ የሚሉኝ “አሁን ያለንበት ወርቃማው ጊዜ ነው” የሚሉ ዜጎች … [Read more...] about “የድሮ ስርዓት ናፋቂ”?